አታቆመውም!
ያልተመቸህ ነገር ይኖራል የህይወትን ፍሰት ግን ማዘግየት አይችለም። ህይወትም ስላልተመቸህ ነገር የምትሰማበት ጊዜ የላትም። ለሰበብ አስባቡ፣ ምክንያት ለመደርደሩ፣ አጀንዳ ለማብዛቱ ያባከንከው ጊዜ የሚመለስ ከመሰለህ እንዳትሳሳት የሰራህበት፣ ያልሰራህበት፤ ያመሰገንክበት ያማረርክበት፤ የወደክበት የተነሳህበት ጊዜ በፍፁም የሚመለስ አይደለም። ዛሬ ዛሬ ነው፤ አሁንም አሁን ብቻ ነው። ህይወትም በዛሬና በአሁን ውስጥ ብቻ ነች። ምንም ነገር ሊያሳስብህና ሊያስጨንቅህ ይችላል፣ ከአሁን ቅፅበት ውጪ ከሆነ ግን የማስጨነቅና ሰላምህን የመንሳት ስልጣን የለውም። ሁሉም እንደምታስበው ቢሆንልህ የት ነበርክ? ፍራቻህ ቢጠፋ፣ ጭንቀትህ ቢወገድ፣ ስጋት ቢርቅህ፣ የምትፈልገው ሁሉ ቢሟላልህ ህይወትህ ምን ይመስል ነበር? በውስጠ ህሊናህ ልትኖረው የምትችለውን ህይወት ተመልከተው፤ የሚሰማህን ስሜት አዳምጠው፤ ደስታህንም አጣጥመው።
አዎ! ጀግናዬ..! አታቆመውም! እያማረርክ ጊዜውን አታቆመውም፤ ሰበብ እያበዛህ ኑሮ ውድነቱን አታቀለውም፤ እየተጨነክ የሆነውን እንዳልሆነ አታደርገውም፤ በስጋት እየኖርክ ፍራቻህን መሻገር አትችልም። ዋጋቸው የበዛ የድል ፅዋዎች ወዳንተ ይመጣሉ፤ ልፋት የሚጠይቁ ስራዎች ለውጤት ያበቁሃል። ስለለፋህ ሳይሆን ስላሸነፍክ ይጨበጨብልሃል፤ ጥረትህ ሳይሆን ውጤትህ ያሸልምሃል። ምንም ብታደርግ የሚቆም የህይወት ፍሰት፣ የጊዜ ሂደት አይኖርም። በአንድ ህይወት ብዙ ነገር ታያለህ፤ በአንድ አለም ለስንት ነገር ትበቃለህ። የቻልከውን ችሎ መገኘት ተዓምረኛ ወይም አስደናቂ ላያስብልህ ይችላል፤ ነገር ግን ስሜት በሚሰጥህ ምልልስ ውስጥህ እያደክ ከሆነ ግን ማስገረምህና ማስደነቅህ አይቀርም። ብዙዎች የሚያውቁህ በጭምትነትህ ይሆናል፤ ጥረትህ ግን ደፋርና አይበገሬ ያደርግሃል። ጥረትህን ባያዩም ውጤትህን ተመልክተው መደመማቸውም አይቀርም።
አዎ! ሰበብ ማብዛት የምትፈልገውን ሃይል አይሰጥህም፤ ምክንያት መደርደር ያለህን ጊዜ አያስረዝምም፤ ጣት መቀሰር የሚገባህን ህይወት አያጎናፅፍህም። በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ ብትሆን ላንተ አዝኖ የሚቆም የጊዜ ሰሌዳ የለም። ማድረግ ያለብህን ካላደረክ፣ እንደምትፈልገው ካልኖርክ ጊዜ ጥሩ ትምህርት ሊሰጥህ ዝግጁ ነው። ጊዜ ከማስተማሩ በፊት ግን አንተ እራስህን አስተምር። እድገትን ከፈለክ ለእራስህ ማዘን ጀምር፤ ለውጥን ከተመኘህ የህይወትን አጭርነት በሚገባ ተረዳ። ምንም ዋጋ ያለው ነገር ሳታደርግ የሚያልፉ ቀናት በበዙ ቁጥር እድሜህን እየቀስክ አጭሯን ህይወት ይባስ እያሳጠርካት ወደፊት ትጓዛለህ። በእርግጥም ብዙ የቀሩህ ጊዜያት ሊኖሩ ይችላሉ፣ ሃሳብህን ለመተግበር፣ ህልምህን ለመኖር፣ ግብህን ለመምታት፣ እቅድህን ለማሳካት ግን ጊዜ የለህምና በቻልከው ፍጥነት፣ በላህ ግብዓት ወደ እርምጃ ግባ።
ያልተመቸህ ነገር ይኖራል የህይወትን ፍሰት ግን ማዘግየት አይችለም። ህይወትም ስላልተመቸህ ነገር የምትሰማበት ጊዜ የላትም። ለሰበብ አስባቡ፣ ምክንያት ለመደርደሩ፣ አጀንዳ ለማብዛቱ ያባከንከው ጊዜ የሚመለስ ከመሰለህ እንዳትሳሳት የሰራህበት፣ ያልሰራህበት፤ ያመሰገንክበት ያማረርክበት፤ የወደክበት የተነሳህበት ጊዜ በፍፁም የሚመለስ አይደለም። ዛሬ ዛሬ ነው፤ አሁንም አሁን ብቻ ነው። ህይወትም በዛሬና በአሁን ውስጥ ብቻ ነች። ምንም ነገር ሊያሳስብህና ሊያስጨንቅህ ይችላል፣ ከአሁን ቅፅበት ውጪ ከሆነ ግን የማስጨነቅና ሰላምህን የመንሳት ስልጣን የለውም። ሁሉም እንደምታስበው ቢሆንልህ የት ነበርክ? ፍራቻህ ቢጠፋ፣ ጭንቀትህ ቢወገድ፣ ስጋት ቢርቅህ፣ የምትፈልገው ሁሉ ቢሟላልህ ህይወትህ ምን ይመስል ነበር? በውስጠ ህሊናህ ልትኖረው የምትችለውን ህይወት ተመልከተው፤ የሚሰማህን ስሜት አዳምጠው፤ ደስታህንም አጣጥመው።
አዎ! ጀግናዬ..! አታቆመውም! እያማረርክ ጊዜውን አታቆመውም፤ ሰበብ እያበዛህ ኑሮ ውድነቱን አታቀለውም፤ እየተጨነክ የሆነውን እንዳልሆነ አታደርገውም፤ በስጋት እየኖርክ ፍራቻህን መሻገር አትችልም። ዋጋቸው የበዛ የድል ፅዋዎች ወዳንተ ይመጣሉ፤ ልፋት የሚጠይቁ ስራዎች ለውጤት ያበቁሃል። ስለለፋህ ሳይሆን ስላሸነፍክ ይጨበጨብልሃል፤ ጥረትህ ሳይሆን ውጤትህ ያሸልምሃል። ምንም ብታደርግ የሚቆም የህይወት ፍሰት፣ የጊዜ ሂደት አይኖርም። በአንድ ህይወት ብዙ ነገር ታያለህ፤ በአንድ አለም ለስንት ነገር ትበቃለህ። የቻልከውን ችሎ መገኘት ተዓምረኛ ወይም አስደናቂ ላያስብልህ ይችላል፤ ነገር ግን ስሜት በሚሰጥህ ምልልስ ውስጥህ እያደክ ከሆነ ግን ማስገረምህና ማስደነቅህ አይቀርም። ብዙዎች የሚያውቁህ በጭምትነትህ ይሆናል፤ ጥረትህ ግን ደፋርና አይበገሬ ያደርግሃል። ጥረትህን ባያዩም ውጤትህን ተመልክተው መደመማቸውም አይቀርም።
አዎ! ሰበብ ማብዛት የምትፈልገውን ሃይል አይሰጥህም፤ ምክንያት መደርደር ያለህን ጊዜ አያስረዝምም፤ ጣት መቀሰር የሚገባህን ህይወት አያጎናፅፍህም። በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ ብትሆን ላንተ አዝኖ የሚቆም የጊዜ ሰሌዳ የለም። ማድረግ ያለብህን ካላደረክ፣ እንደምትፈልገው ካልኖርክ ጊዜ ጥሩ ትምህርት ሊሰጥህ ዝግጁ ነው። ጊዜ ከማስተማሩ በፊት ግን አንተ እራስህን አስተምር። እድገትን ከፈለክ ለእራስህ ማዘን ጀምር፤ ለውጥን ከተመኘህ የህይወትን አጭርነት በሚገባ ተረዳ። ምንም ዋጋ ያለው ነገር ሳታደርግ የሚያልፉ ቀናት በበዙ ቁጥር እድሜህን እየቀስክ አጭሯን ህይወት ይባስ እያሳጠርካት ወደፊት ትጓዛለህ። በእርግጥም ብዙ የቀሩህ ጊዜያት ሊኖሩ ይችላሉ፣ ሃሳብህን ለመተግበር፣ ህልምህን ለመኖር፣ ግብህን ለመምታት፣ እቅድህን ለማሳካት ግን ጊዜ የለህምና በቻልከው ፍጥነት፣ በላህ ግብዓት ወደ እርምጃ ግባ።