እቀጥላለሁ!
ከራስ ጋር ንግግር፦ "ላሸንፈው የማልችለውን፣ ከፊቱ እንኳን መቆም የሚከብደኝን፣ በፍፁም የማልችለውን ሰው እስካገኘው ድረስ መስራቴን እቀጥላለሁ፣ መጓዜን እቀጥላለሁ፣ መድከም መታገሌን እቀጥላለሁ። ሁሌም ጉዞ ላይ ነኝ፣ ሁሌም መንገድ ላይ ነኝ፣ ሁሌም እየታተረኩ ነው። ፍላጎቴ አንድና አንድ ብቻ ነው። እርሱም አይበገሬውን ጠንካራ ሰው መፍጠር። እስካሁን ያንን ሰው ስለመሆኔ እርግጠኛ አይደለውምና አሁንም ጥረት ላይ ነኝ፣ በረፍት አልባው መንገድ እየተጓዝኩ ነው። እርግጥ ነው ድካም አለው፣ እውነት ነው ይሰለቻል፣ ይታክታል ነገር ግን ሌላ ምርጫ የለውም፣ ነገር ግን ከዚህ ውጪ ቀላል መንገድ የለውም። ከማየው ሰው ጋር ሁሉ እየተወዳደርኩ ራሴን ዝቅ ማድረግ አልፈልግም፣ የሰማውትን ሁሉ እያመንኩ መከተል አልፈልግም። ማንም ሰው ያለውን የፈለገውን ሰው የመሆን ምርጫ ተጠቅሜ ራሴን እሆናለሁ የተሻለውን ግሩም ማንነትም እፈጥራለሁ። ለራሴ የመታመን ምርጫ ሳይሆን ግዴታ አለብኝ፣ ራሴን የማክበር ምርጫ ሳይሆን ግዴታ አለብኝ።
አዎ! እቀጥላለሁ! ደክሞኛል ግን አላቆምም እቀጥላለሁ፣ ደብሮኛል ነገር ግን አላቆምም እቀጥላለሁ፣ የማየው የምሰማው ነገር ደስ አይልም ቢሆንም አሁንም ጉዞዬ ላይ ነኝ። ወደፊት ስጓዝ ምን እንደሚገጥመኝ አላውቅም የመጣብኝን ለመቀበል ግን ዝግጁ ነኝ፣ በህይወት እስካለሁ ድረስ ከፈጣሪ ጋር መቀየር ማደግ እንዳለብኝ አምናለሁ ስለዚህ በፈተናዎች መሃልም ቢሆን ጎልቶ መውጣት የሚችል ብርቱ ማንነት መገንባት እንዳለብኝ አውቃለሁ። ያለሁት ቀላል ወይም አጭር መንገድ ላይ አይደለም፣ የጀመርኩት በአጭሩ የሚቋጭ፣ በትንሽ ጥረትም የሚሳካ እቅድ አይደለም። መሆን ያለብኝን ሰው የምሆነው ራሴን ሰጥቼው ነው፣ መድረስ የምፈልገው ስፍራ የምደርሰው መክፈል ያለብኝ ዋጋ ከፍዬ ነው። ብዙ ወዳጅ አለኝ ከራሴ የሚበልጥ ወዳጅ ግን የለኝም፣ ብዙ የሚያስብልኝ ሰው አለ ከራሴ በላይ የሚያስብልኝ ሰው ግን የለም እንዲኖርም አልፈልግም። ለራሴ መሆን ሳልችል ዓለም በእኔ ላይ ብታብር ምንም አይገርመኝም። ምርጥ ነገር እንደሚገባኝ አስባለሁና ምርጥ ሆኖ መገኘቱ የእኔ ስራ ነው። ራስን በመሆን ውስጥ ቀላል የሚባል እርምጃ የለምና ሁሌም ራሴን እያበረታው እጓዛለሁ፣ የምመኘውን ብርቱ ሰውም እፈጥረዋለሁ።"
አዎ! ጀግናዬ..! ሰው እንዲመክርህ አትጠብቅ። ማንም ሳይሰማ ማንም ሳያይ ራስህን በሚገባ ምከረው። ከፍ ማለት እንዳለብህ ካመንክ ከፍ የሚያደርግህ ሰው ሳይሆን አንተ ነህ፣ መቀየር ከፈለክ የሚቀይርህ ሰው ሳይሆን አንተ ራስህ ነህ። የትኛውም ራስን የማብቃት፣ በአስተሳሰብ፣ በስሜትና በገንዘብ ብቁ ሆኖ ለመገኘት የመጣር መንገድ አልጋ በአልጋ አይደለም። ታጣለህ ታገኛለህ፣ ይሳካልሃል አይሳካልህም፣ ትወድቃለህ ትነሳለህ፣ ታተርፋለህ ትከስራለህ። ተመሳሳይ ገቢ ሲኖርህ ተመሳሳይ ህይወት እንደምትኖረው ሁሉ ገቢህም የተለያየ ሲሆን ህይወትህም በብዙ መንገድ የተለያየ ሊሆን ይችላል። ሁሉም ነገር ሊሰለችህ ይችላል ነገር ግን እንድታቆም ሊያደርግህ አይገባም፣ ብዙ ሰው ላይረዳህ ይችላል ነገር ግን ወደኋላ ሊመልስህ አይገባም። ምንም አደረክ ምንም ገጠመህ ምርጫህ አንድ ነው። የተሻለ ሰው መሆንና መሆን ብቻ ነው። የመረጥከውን ሰው ለመሆን ከማንም ጋር አትደራደር፣ የፈለከው ስፍራ ለመገኘት የማንንም ይሁኝታ አትጠብቅ። ሁሌም ራስህን መስራትህን ቀጥል፣ የምትመኘውን ማንነትም መገንባትህን ግፋበት።
ከራስ ጋር ንግግር፦ "ላሸንፈው የማልችለውን፣ ከፊቱ እንኳን መቆም የሚከብደኝን፣ በፍፁም የማልችለውን ሰው እስካገኘው ድረስ መስራቴን እቀጥላለሁ፣ መጓዜን እቀጥላለሁ፣ መድከም መታገሌን እቀጥላለሁ። ሁሌም ጉዞ ላይ ነኝ፣ ሁሌም መንገድ ላይ ነኝ፣ ሁሌም እየታተረኩ ነው። ፍላጎቴ አንድና አንድ ብቻ ነው። እርሱም አይበገሬውን ጠንካራ ሰው መፍጠር። እስካሁን ያንን ሰው ስለመሆኔ እርግጠኛ አይደለውምና አሁንም ጥረት ላይ ነኝ፣ በረፍት አልባው መንገድ እየተጓዝኩ ነው። እርግጥ ነው ድካም አለው፣ እውነት ነው ይሰለቻል፣ ይታክታል ነገር ግን ሌላ ምርጫ የለውም፣ ነገር ግን ከዚህ ውጪ ቀላል መንገድ የለውም። ከማየው ሰው ጋር ሁሉ እየተወዳደርኩ ራሴን ዝቅ ማድረግ አልፈልግም፣ የሰማውትን ሁሉ እያመንኩ መከተል አልፈልግም። ማንም ሰው ያለውን የፈለገውን ሰው የመሆን ምርጫ ተጠቅሜ ራሴን እሆናለሁ የተሻለውን ግሩም ማንነትም እፈጥራለሁ። ለራሴ የመታመን ምርጫ ሳይሆን ግዴታ አለብኝ፣ ራሴን የማክበር ምርጫ ሳይሆን ግዴታ አለብኝ።
አዎ! እቀጥላለሁ! ደክሞኛል ግን አላቆምም እቀጥላለሁ፣ ደብሮኛል ነገር ግን አላቆምም እቀጥላለሁ፣ የማየው የምሰማው ነገር ደስ አይልም ቢሆንም አሁንም ጉዞዬ ላይ ነኝ። ወደፊት ስጓዝ ምን እንደሚገጥመኝ አላውቅም የመጣብኝን ለመቀበል ግን ዝግጁ ነኝ፣ በህይወት እስካለሁ ድረስ ከፈጣሪ ጋር መቀየር ማደግ እንዳለብኝ አምናለሁ ስለዚህ በፈተናዎች መሃልም ቢሆን ጎልቶ መውጣት የሚችል ብርቱ ማንነት መገንባት እንዳለብኝ አውቃለሁ። ያለሁት ቀላል ወይም አጭር መንገድ ላይ አይደለም፣ የጀመርኩት በአጭሩ የሚቋጭ፣ በትንሽ ጥረትም የሚሳካ እቅድ አይደለም። መሆን ያለብኝን ሰው የምሆነው ራሴን ሰጥቼው ነው፣ መድረስ የምፈልገው ስፍራ የምደርሰው መክፈል ያለብኝ ዋጋ ከፍዬ ነው። ብዙ ወዳጅ አለኝ ከራሴ የሚበልጥ ወዳጅ ግን የለኝም፣ ብዙ የሚያስብልኝ ሰው አለ ከራሴ በላይ የሚያስብልኝ ሰው ግን የለም እንዲኖርም አልፈልግም። ለራሴ መሆን ሳልችል ዓለም በእኔ ላይ ብታብር ምንም አይገርመኝም። ምርጥ ነገር እንደሚገባኝ አስባለሁና ምርጥ ሆኖ መገኘቱ የእኔ ስራ ነው። ራስን በመሆን ውስጥ ቀላል የሚባል እርምጃ የለምና ሁሌም ራሴን እያበረታው እጓዛለሁ፣ የምመኘውን ብርቱ ሰውም እፈጥረዋለሁ።"
አዎ! ጀግናዬ..! ሰው እንዲመክርህ አትጠብቅ። ማንም ሳይሰማ ማንም ሳያይ ራስህን በሚገባ ምከረው። ከፍ ማለት እንዳለብህ ካመንክ ከፍ የሚያደርግህ ሰው ሳይሆን አንተ ነህ፣ መቀየር ከፈለክ የሚቀይርህ ሰው ሳይሆን አንተ ራስህ ነህ። የትኛውም ራስን የማብቃት፣ በአስተሳሰብ፣ በስሜትና በገንዘብ ብቁ ሆኖ ለመገኘት የመጣር መንገድ አልጋ በአልጋ አይደለም። ታጣለህ ታገኛለህ፣ ይሳካልሃል አይሳካልህም፣ ትወድቃለህ ትነሳለህ፣ ታተርፋለህ ትከስራለህ። ተመሳሳይ ገቢ ሲኖርህ ተመሳሳይ ህይወት እንደምትኖረው ሁሉ ገቢህም የተለያየ ሲሆን ህይወትህም በብዙ መንገድ የተለያየ ሊሆን ይችላል። ሁሉም ነገር ሊሰለችህ ይችላል ነገር ግን እንድታቆም ሊያደርግህ አይገባም፣ ብዙ ሰው ላይረዳህ ይችላል ነገር ግን ወደኋላ ሊመልስህ አይገባም። ምንም አደረክ ምንም ገጠመህ ምርጫህ አንድ ነው። የተሻለ ሰው መሆንና መሆን ብቻ ነው። የመረጥከውን ሰው ለመሆን ከማንም ጋር አትደራደር፣ የፈለከው ስፍራ ለመገኘት የማንንም ይሁኝታ አትጠብቅ። ሁሌም ራስህን መስራትህን ቀጥል፣ የምትመኘውን ማንነትም መገንባትህን ግፋበት።