ጭንቀትህ የለም!
ሰውነት ማሰብ መገለጫው ነው፤ ማሰላሰል፣ ማመዛዘን መለያው ነው፤ ማስተዋል፣ መወሰንና በተግባር መግለፅ የማንነቱ መለኪያ ነው። በሰው አምሳል ምድር ላይ መመላለስ ብቻውን ሰው ሊያስብል ቢችልም እውነተኛውን ትክክለኛ ተፈላጊ ሰው ግን ሊያስብል አይችልም። ሰውነት ውስጡ ጥበብ አለ፣ ሰውነት በጉያው የአምላክን ድንቅ ሃይል ይዟል፣ ሰውነት በትንሹም በትልቁም የሚደነግጥና እንቅልፍ የሚያጣ፣ በተጨበጠውም ባልተጨበጠውም በጭንቀት የሚባክን አይነት አይደለም። የሰውነትን ምንነት ስትረዳ እራስህን በሚገባ ማክበር ትጀምራለህ፣ ማንነትህን ስታውቅ የምርም በጊዜያዊ ሀሳብና ጭንቀቶች መሸበርህን ታቆማለህ። ለማን ብለህ ነው ውሎህን በሚያውክ ሃሳብ ተጠምደህ የምትውለው? ማንን ደስ እንዲለው ነው ባልተጨበጠ ወሬ ምክንያት የውስጥ ሰላምሽን የምታጪው?
አዎ! ጀግናዬ..! ጭንቀትህ የለም! ስራህን በአግባቡ እንዳትሰራ ያደረገህ፣ ትምህርትን እንዳታጠና የከለከለህ፣ በሰዎች ፊት ሃሳብህን እንዳትገልፅ ያደረገህ፣ የእራስህን አዲስ ስራ እንዳትጀምር አስሮ የያዘህ፣ ከሱስህ እንዳትላቀቅ ፋታ የነሳህ የገዛ ጭንቀትና ስጋትህ ነፍስ የለውም፣ ምንም ሊያመጣብህ አይችልም። ያላንተ ይሁንታ ብቻውን ምንም ሊያደርግህ አይችልም፤ በውስጥህ የተፈጠረው አለመረጋጋት፣ ዘወትር የሚያውክህ አሉታዊ ስሜት፣ ሰላምህን የሚነሳህ የሰዎች ሃሳብና አስተያየት ካንተ ፍቃድ በቀር ምንም ሊያስከትልብህ አይችልም። አምነህ የተቀበልከው ስጋት መረጋጋት ይነሳሃል፤ እውነት የመሰለህ የሰዎች አስተያየት ውስጥህን ይረብሸዋል፤ ይሉኝታ ዘመንህን ሙሉ በጭንቀትና በፍረሃት አንድ ቦታ ላይ እንድታሳልፍ ያደርግሃል።
አዎ! ማንም ያስባል፣ ማንም በውስጡ ነገሮችን ያሰላስላል፣ ግፋ ሲልም ይጨነቃል፣ ይሸበራል። ከልክ በላይ ማሰብን ትርጉም ብነሰጠው በአጭር አማርኛ ጭንቀት ማለት እችላለን። ሃሳብ ሃሳብን ሲወልድ፣ በሂደትም በመላምቶችና መሰረት አልባ ትርክቶች ሲታገዝ መዳረሻውን እንቅልፍ ነሺ ጭንቀት ሆኖ እናገኘዋለን። አብዝተን እናስባለን ነገር ግን ምንም ተጨባጭ ነገር አናመጣም፤ እናወጣለን እናወርዳለን ነገር ግን ምንም አይነት እርምጃ አንወስድም። በገዛ ፍቃዳችን አዕምሮችን ላይ ሸክም እናበዛለን፣ ህሊናችንን በሌለ ነገር ደጋግመን እንፈትናለን። ጭንቀት አዲስህ አይደለምና ከዚህ በፊት ተጨንቀህ ምን እንዳመጣህ አስታውስ፤ አብዝተህ ስላሰብክ ምን እንዳተረፍክ ተረዳ። ስለጭንቀትህ መጨነቅ አቁምና እርምጃ መውሰድ ባለብህ ልክ እርምጃ ውሰድበት። ባልተጨበጠ ሃሳብ ውስጣዊ ሰላምህን እንዳታጣ ሃሳቦችህን ጠብቃቸው።
ሰውነት ማሰብ መገለጫው ነው፤ ማሰላሰል፣ ማመዛዘን መለያው ነው፤ ማስተዋል፣ መወሰንና በተግባር መግለፅ የማንነቱ መለኪያ ነው። በሰው አምሳል ምድር ላይ መመላለስ ብቻውን ሰው ሊያስብል ቢችልም እውነተኛውን ትክክለኛ ተፈላጊ ሰው ግን ሊያስብል አይችልም። ሰውነት ውስጡ ጥበብ አለ፣ ሰውነት በጉያው የአምላክን ድንቅ ሃይል ይዟል፣ ሰውነት በትንሹም በትልቁም የሚደነግጥና እንቅልፍ የሚያጣ፣ በተጨበጠውም ባልተጨበጠውም በጭንቀት የሚባክን አይነት አይደለም። የሰውነትን ምንነት ስትረዳ እራስህን በሚገባ ማክበር ትጀምራለህ፣ ማንነትህን ስታውቅ የምርም በጊዜያዊ ሀሳብና ጭንቀቶች መሸበርህን ታቆማለህ። ለማን ብለህ ነው ውሎህን በሚያውክ ሃሳብ ተጠምደህ የምትውለው? ማንን ደስ እንዲለው ነው ባልተጨበጠ ወሬ ምክንያት የውስጥ ሰላምሽን የምታጪው?
አዎ! ጀግናዬ..! ጭንቀትህ የለም! ስራህን በአግባቡ እንዳትሰራ ያደረገህ፣ ትምህርትን እንዳታጠና የከለከለህ፣ በሰዎች ፊት ሃሳብህን እንዳትገልፅ ያደረገህ፣ የእራስህን አዲስ ስራ እንዳትጀምር አስሮ የያዘህ፣ ከሱስህ እንዳትላቀቅ ፋታ የነሳህ የገዛ ጭንቀትና ስጋትህ ነፍስ የለውም፣ ምንም ሊያመጣብህ አይችልም። ያላንተ ይሁንታ ብቻውን ምንም ሊያደርግህ አይችልም፤ በውስጥህ የተፈጠረው አለመረጋጋት፣ ዘወትር የሚያውክህ አሉታዊ ስሜት፣ ሰላምህን የሚነሳህ የሰዎች ሃሳብና አስተያየት ካንተ ፍቃድ በቀር ምንም ሊያስከትልብህ አይችልም። አምነህ የተቀበልከው ስጋት መረጋጋት ይነሳሃል፤ እውነት የመሰለህ የሰዎች አስተያየት ውስጥህን ይረብሸዋል፤ ይሉኝታ ዘመንህን ሙሉ በጭንቀትና በፍረሃት አንድ ቦታ ላይ እንድታሳልፍ ያደርግሃል።
አዎ! ማንም ያስባል፣ ማንም በውስጡ ነገሮችን ያሰላስላል፣ ግፋ ሲልም ይጨነቃል፣ ይሸበራል። ከልክ በላይ ማሰብን ትርጉም ብነሰጠው በአጭር አማርኛ ጭንቀት ማለት እችላለን። ሃሳብ ሃሳብን ሲወልድ፣ በሂደትም በመላምቶችና መሰረት አልባ ትርክቶች ሲታገዝ መዳረሻውን እንቅልፍ ነሺ ጭንቀት ሆኖ እናገኘዋለን። አብዝተን እናስባለን ነገር ግን ምንም ተጨባጭ ነገር አናመጣም፤ እናወጣለን እናወርዳለን ነገር ግን ምንም አይነት እርምጃ አንወስድም። በገዛ ፍቃዳችን አዕምሮችን ላይ ሸክም እናበዛለን፣ ህሊናችንን በሌለ ነገር ደጋግመን እንፈትናለን። ጭንቀት አዲስህ አይደለምና ከዚህ በፊት ተጨንቀህ ምን እንዳመጣህ አስታውስ፤ አብዝተህ ስላሰብክ ምን እንዳተረፍክ ተረዳ። ስለጭንቀትህ መጨነቅ አቁምና እርምጃ መውሰድ ባለብህ ልክ እርምጃ ውሰድበት። ባልተጨበጠ ሃሳብ ውስጣዊ ሰላምህን እንዳታጣ ሃሳቦችህን ጠብቃቸው።