በምክንያትህ ተመራ!
ህመሙን እለፈው፣ ስቃዩን ተሻገረው፣ ውድቀትህን ተጠቀም፣ በመገፋትህ እራስህን ስራው፣ በመከዳትህ ለእራስህ ታመን፣ በኋሊት ጉዞህ እራስህን መርምር፣ በውጤት አልባው ጥረትህ እራስህን ገንባ፣ በተለተለት የግል ጦርነትህ ብቁ ሆነህ ተገኝ። ሽንፈትህ ተስፋህን እንዳይገድለው፣ ስህተትህ ዋጋህን እንዳያሳንስ አስቀድመህ ለሽንፈትና ለስህተት ያለህን አመለካከት አስተካክል። ውድድሩ ውስጥ ስለገባህ ልትሸነፍ ትችላለህ፣ ስለሞከርክ ልትሳሳት ትችላለህ፣ በመጣርህ ብቻ ልትሰበር ትችላለህ አመለካከትህ ግን ይህን ሁሉ ድካምና ውጤት ሊያስታርቅልህ ይችላል። እራስህን ስለሰጠሀው ብዙ ነገር ፈጥኖ ፍሬ እንደሚያፈራ ልትጠብቅ ትችላለህ ነገር ግን አንዳንድ አካሔዶች ገና ከጅምራቸው ስህተት ነበሩና ምንም እንኳን አጥብቀህ ብትታገልላቸው፣ ዋጋ ብትከፍልላቸው፣ እራስህን አሳልፈህ ብትሰጥላቸው እንኳን ውጤት አይኖራቸውም።
አዎ! ጀግናዬ..! የጉዞ አቅጣጫህን፣ የትግልህን ምክንያት፣ የጥረትህን የኋላ መነሻ በሚገባ እወቀው። ለምን እየታገልክ ነው? ምን እንዲፈጠር እየጣርክ ነው? ለምንስ ይህን እልህ አስጨራሽ ጉዞ ጀመርክ? ስሜትህን ወደጎን በለው፣ የሚወራብህን ወሬ ከቁብ አትቁጠረው፣ በቀደመ ስህተትህ አትሸበር፣ ውድቀትን አትፍራ፣ በሌሎች ኪሳራ እራስህን አታስፈራራ። በምክንያትህ ተመራ፤ በጥበብ ተራመድ፣ በእውቀት ወደፊት ተጓዝ፣ በምርጫህ ፅና፣ በውሳኔህ ተማመን። ማንም በአመለካከትህ ላይ ስልጣን የለውም፣ ማንም በግል አቋምህ፣ በግል ውሳኔህ ላይ ጣልቃ የመግባት መብት የለውም፣ ማንም በምርጫህ ምክንያት ጫና ውስጥ ሊከትህ አይችልም። በመረጥከው፣ ባመንከውና በወደድከው ፅንፍ ከማንም በላይ እስከ ጥግ መጓዝን ብትፈልግ ማን ሊያስቆምህ ይችላል? ማንም! እምነትህ ወደፊት ይመራሃል፤ ደጋግመህ በአይነ ህሊናህ በምናብህ የምትመለከተው መዳረሻህ መንገዱን ሁሉ ያቀናልሃል።
አዎ! ወደፊት ስትጓዝ፣ በፅናት ስትራመድ፣ እራስህን ብቁ ለማድረግ ስትጥር የተዘጉ የሚመስሉ እድሎች ሁሉ እየተከፈቱ ይመጣሉ፣ በፊት በጨለማ የተሞሉት መንገዶችህ የብረሃን ጭላንጭል እየታየባቸው ይመጣል፣ ተስፋ የቆረጥክባቸው፣ "ዋጋ የላቸውም፣ አይጠቅሙም" ያልክባቸው የግልና የሃገርህ ጉዳዮች የምርም የለውጥና የእድገትህ ምክንያቶች ሲሆኑ ትመለከታለህ። ይህን የቻይኖች አባባል አስታስ፦ "አንድ ችግር ስትፈታ ብዙ መቶ ችግሮችን ታርቃለህ።" ችግር ሁሉም ቦታ አለ፣ ካንተም ይሁን ከሌላ አካል መፍትሔ የሚፈልግ ጉዳይ በየቦታው፣ በየደረጃው የትም አለ። አንተ ግን የእራስህን ሃላፊነት ብቻ ተወጣ፣ ወደፊት እየተራመድክ የእራስህን ችግር ብቻ ፍታ፣ እራስህን ለውጥ፣ እራስህን አሳድግ። የእድገት ጉዞህ በእራሱ የብዙዎችን ችግር እንድትፈታ ያደርግሃል፤ የለውጥ መንገድህ አይነተኛ ተመረጫ የመፍትሔ ሰው ያደርግሃል። በምክንያትህ ተመራ፣ በውጤትህም አሸብርቅ።
ህመሙን እለፈው፣ ስቃዩን ተሻገረው፣ ውድቀትህን ተጠቀም፣ በመገፋትህ እራስህን ስራው፣ በመከዳትህ ለእራስህ ታመን፣ በኋሊት ጉዞህ እራስህን መርምር፣ በውጤት አልባው ጥረትህ እራስህን ገንባ፣ በተለተለት የግል ጦርነትህ ብቁ ሆነህ ተገኝ። ሽንፈትህ ተስፋህን እንዳይገድለው፣ ስህተትህ ዋጋህን እንዳያሳንስ አስቀድመህ ለሽንፈትና ለስህተት ያለህን አመለካከት አስተካክል። ውድድሩ ውስጥ ስለገባህ ልትሸነፍ ትችላለህ፣ ስለሞከርክ ልትሳሳት ትችላለህ፣ በመጣርህ ብቻ ልትሰበር ትችላለህ አመለካከትህ ግን ይህን ሁሉ ድካምና ውጤት ሊያስታርቅልህ ይችላል። እራስህን ስለሰጠሀው ብዙ ነገር ፈጥኖ ፍሬ እንደሚያፈራ ልትጠብቅ ትችላለህ ነገር ግን አንዳንድ አካሔዶች ገና ከጅምራቸው ስህተት ነበሩና ምንም እንኳን አጥብቀህ ብትታገልላቸው፣ ዋጋ ብትከፍልላቸው፣ እራስህን አሳልፈህ ብትሰጥላቸው እንኳን ውጤት አይኖራቸውም።
አዎ! ጀግናዬ..! የጉዞ አቅጣጫህን፣ የትግልህን ምክንያት፣ የጥረትህን የኋላ መነሻ በሚገባ እወቀው። ለምን እየታገልክ ነው? ምን እንዲፈጠር እየጣርክ ነው? ለምንስ ይህን እልህ አስጨራሽ ጉዞ ጀመርክ? ስሜትህን ወደጎን በለው፣ የሚወራብህን ወሬ ከቁብ አትቁጠረው፣ በቀደመ ስህተትህ አትሸበር፣ ውድቀትን አትፍራ፣ በሌሎች ኪሳራ እራስህን አታስፈራራ። በምክንያትህ ተመራ፤ በጥበብ ተራመድ፣ በእውቀት ወደፊት ተጓዝ፣ በምርጫህ ፅና፣ በውሳኔህ ተማመን። ማንም በአመለካከትህ ላይ ስልጣን የለውም፣ ማንም በግል አቋምህ፣ በግል ውሳኔህ ላይ ጣልቃ የመግባት መብት የለውም፣ ማንም በምርጫህ ምክንያት ጫና ውስጥ ሊከትህ አይችልም። በመረጥከው፣ ባመንከውና በወደድከው ፅንፍ ከማንም በላይ እስከ ጥግ መጓዝን ብትፈልግ ማን ሊያስቆምህ ይችላል? ማንም! እምነትህ ወደፊት ይመራሃል፤ ደጋግመህ በአይነ ህሊናህ በምናብህ የምትመለከተው መዳረሻህ መንገዱን ሁሉ ያቀናልሃል።
አዎ! ወደፊት ስትጓዝ፣ በፅናት ስትራመድ፣ እራስህን ብቁ ለማድረግ ስትጥር የተዘጉ የሚመስሉ እድሎች ሁሉ እየተከፈቱ ይመጣሉ፣ በፊት በጨለማ የተሞሉት መንገዶችህ የብረሃን ጭላንጭል እየታየባቸው ይመጣል፣ ተስፋ የቆረጥክባቸው፣ "ዋጋ የላቸውም፣ አይጠቅሙም" ያልክባቸው የግልና የሃገርህ ጉዳዮች የምርም የለውጥና የእድገትህ ምክንያቶች ሲሆኑ ትመለከታለህ። ይህን የቻይኖች አባባል አስታስ፦ "አንድ ችግር ስትፈታ ብዙ መቶ ችግሮችን ታርቃለህ።" ችግር ሁሉም ቦታ አለ፣ ካንተም ይሁን ከሌላ አካል መፍትሔ የሚፈልግ ጉዳይ በየቦታው፣ በየደረጃው የትም አለ። አንተ ግን የእራስህን ሃላፊነት ብቻ ተወጣ፣ ወደፊት እየተራመድክ የእራስህን ችግር ብቻ ፍታ፣ እራስህን ለውጥ፣ እራስህን አሳድግ። የእድገት ጉዞህ በእራሱ የብዙዎችን ችግር እንድትፈታ ያደርግሃል፤ የለውጥ መንገድህ አይነተኛ ተመረጫ የመፍትሔ ሰው ያደርግሃል። በምክንያትህ ተመራ፣ በውጤትህም አሸብርቅ።