በምድር በላይ በደል ፥ በተንሰራፋበት፣
የጣዖት አምልኮ ፥ ጫፍ በደረሰበት፣
ጎሳ ከጎሳ ጋ ፥ በሚጋደልበት፣
ባለሃብት ደሃውን ፥ በሚጨቁንበት፣
ሴት ልጆችን መውለድ ፥ ወንጀል በሆነበት፣
ደጋግ የአላህ ባሮች ፥ መጠጊያ ባጡበት፣
የባርነት ቀንበር ፥ ድካ ባለፈበት፣
ምድር አልችል ብላ ፥ የፈሳዱን ብዛት፣
በድቅድቅ ጨለማ ፥ በተሞላችበት፣
ውዱን ነቢይ ሰጠን ፥ ለዓለማት እዝነት።
በእርሳቸው መላክ ፥ ጨለማው ተገፏል፣
የተውሒዱ ፋኖስ ፥ እስከ ጥግ አብርቷል፣
የተጋጨ ጎሳ ፥ ወንድማማች ሆኗል፣
የባርነት ቀንበር ፥ ቀስ በቀስ አክትሟል፣
የተውሒዱ ጮራ ፥ ዓለምን አዳርሷል፣
የኡማው አንድ አካል ፥ ክብሯ ተመልሷል።
የጣዖት አምልኮ ፥ ጫፍ በደረሰበት፣
ጎሳ ከጎሳ ጋ ፥ በሚጋደልበት፣
ባለሃብት ደሃውን ፥ በሚጨቁንበት፣
ሴት ልጆችን መውለድ ፥ ወንጀል በሆነበት፣
ደጋግ የአላህ ባሮች ፥ መጠጊያ ባጡበት፣
የባርነት ቀንበር ፥ ድካ ባለፈበት፣
ምድር አልችል ብላ ፥ የፈሳዱን ብዛት፣
በድቅድቅ ጨለማ ፥ በተሞላችበት፣
ውዱን ነቢይ ሰጠን ፥ ለዓለማት እዝነት።
በእርሳቸው መላክ ፥ ጨለማው ተገፏል፣
የተውሒዱ ፋኖስ ፥ እስከ ጥግ አብርቷል፣
የተጋጨ ጎሳ ፥ ወንድማማች ሆኗል፣
የባርነት ቀንበር ፥ ቀስ በቀስ አክትሟል፣
የተውሒዱ ጮራ ፥ ዓለምን አዳርሷል፣
የኡማው አንድ አካል ፥ ክብሯ ተመልሷል።