✍️ .................ትዝብት ..........✍️.።
።...ዓለም እንደዚህ ናት...።
ጎል ባስቆጠርክ ጊዜ ቁማ ታጨበጭብልሃለች።ሪከርድ በሰበርክ ጊዜ በስምህ ቲሸርት ታሳትምልሃለች።በስምህ ድርጅት ትከፍትልሃለች። ለክርስቶስ ያልገለጠችውን ፍቅሯን ላንተ ትገልጥልሃለች። ነገር ግን ይህንን ያህል የወደደችህ ዓለም! ለጎል የተቃረበ ኳስን ተሳስተህ ብታበላሽ በስምህ ያሳተመችውን ቲሸርት ወዲያው ትቀደዋለች። የድርጅቷን ስምም በሌላ ትለውጣለች። ሰው ነው እና ይሳሳታል ማለቷን ትታ ለምን ተሳሳተ እያለች ታማታሃለች። የተሳሳተ ቢሠራ ነው። ያልተራመደ እንቅፋት አይመታውም።
ምክንያቱም ተኝቷል" በማለት አትረዳልህምም።
በዚህ ውስጥ ዓለም የዘነጋችው ቢኖር ? ለስሂት መኑ ይሌብዋ ያለውን የመዝሙር ጥቅስ ነው።
✍️ በዚህ ሰሞን የታዘብኳቸው ጉዳዮች ብዙዎች ናቸው ።በዋናነት ሶስት መሠራታዊ ነጥቦችን
በአክሊል ዙሪያ በኋላ አነሳለሁ። በሶሻል ምድያው ላይ በርካታ ትምህርቶች እየተሰጡ ነው።ሰውም ከዐውደ ምሕረቱ ይልቅ ሶሻል ምድያው ላይ ሰፍሯል። የምድያው አላማ አማኙን ምድያው ላይ ማስቀረት ሳይሆን ምድያው ላይ የሰፈረውን ምእመን ወደ ዐውደ ምሕረቱ መሳብ ነው። ንቦችን ዛፍ ላይ ፤ አጥር ላይ ልናሰፍራቸው እንችላለን። ኋላ ግን አውራቸውን ይዘን መዓር ወደ ሚሠሩበት ቀፎ እናስገባቸዋለን ።ምክንያቱም አሳ የሚጠመደው ባሕር ላይ ነው። ቆቅም የምታያዘው ዱር ላይ ነው ። የሚከሸኑት ግን ከቤት ውስጥ ነው።
✍️ ምእመናንንም ከሀገር ከሀገሪት ፤ ከሀቃል ከሮቢት፤ ከዱር ከገደሉ ከሶሻል ምድያው የወንጌል መረብን በመጣል ልናጠምዳቸው እንችላለን።የክርስቶስ አካል ብልት የሚሆኑት ግን የጸጋ ግምጃ ቤት በሆነችው በቤተ ክርስቲያኗ ነው።ይህንን ሥራ ደግሞ አሁን በምድያው ውስጥ ያሉ ወጣቶቻችን እየሠሩት ነው ። ይህንን ማበረታታት ግድ ነው ።
✍️ከጥቂት ዓመታት በፊት ምድያው ላይ ሙስሊሞች ንጽጽር ሠራን እያሉ መጽሐፍ ቅዱስን እያጋጩ የእኛ መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚጣላ እንደሚጋጭ አስመስለው ያሠራጩ ነበር። እኛ ደግሞ እንደ ከዋክብት የበዙ ሊቃውንት ቢኖሩንም ምድያው ላይ እንደ አሁኑ የሚሞግቱ የሚከራከሩ ወጣቶች ግን ብዙም አልነበሩንም ። ምድያው ላይ ማለቴ ነው ።
...........✍️ ፕሮቴስታንቶችም ".......
ኦርቶዶክስ ? ሥዕል ታመልካለች፥
☝️ታቦት ታመልካለች ፤
☝️ድንግል ማርያምን ታመልካለች፤
☝️ቅዱሳንን ታመልካለች እያሉ አንድ አምላክ ማምላኳን ክደው በሀሰት ሲኮንኗት ፤ ሲጽፉባት ፦በየምድያው ሲያቀረሹባት እንደ ኮከብ ተወርውረው እንደ አድማሱ ጀምበሬ፤ እንደ ዲ/ን ያረጋል አበጋዝ የመሳሰሉት ውሃ በእሳት ላይ እንደሚነሳሳ ሁሉ እነርሱም በቅናት ተነስተው የመናፍቃንን ምንፍቅና እልም ድርግም የሚያደርጉ ጽሑፎችን ሲጽፉ አይተናል ።ይሁን እንጅ ምድያው ላይ ግን ብዙም አልተራመድንም ነበር ።ታላላቁ ምድያዎች እንኳን እስከ አሁን ሁለት ናቸው ። ይህ ስንፍናችን አሳዛኝ ቢሆንም እንኳን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ በርካታ ወጣቶች በምድያው ላይ ተሠራጭተዋል ።
እኔ እንኳን በመጠኑ የማያቸው ወጣቶች ብዙዎቹ ዲ/ን እንኳን አይደሉም።ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱሱን እንደ ውሃ ይጠጡታል ። ከላይ የጠቀስኳቸው የሙስሊም ኡስታዞች እና የፕሮቼስታንት ፓስተሮች ሊከራከሩ ቀርበው ላብ በላብ ሲሆኑ መልስ አጥተው ሲያቃትቱ አይቼ ተደንቄያለሁ ።የሳቁባቸው እና የተሳለቁባቸው የገድላትን፥ የቅዱሣት ሥዕላትን፤ የታቦትን ፤የቅዱሳን ምልጃን በተመለከተም ብዙዎች እንዲህ ነው እንዴ ? ብለው ሲመለሱ ታይተዋል።ብዙዎች ደግሞ ደንግጠው ከመንቀፍ አፋቸውን ሲቆጥቡ ተመላክቷል። ሌሎች ደግሞ በዚህ ተበሳጭተው በወጣቶቹ ላይ ፖለቲካ ሠርተዋል። በዋናነት ወጣቶቹን እኔ በግሌ የቤ/ክርስቲያኗ የደስታ ፍሬዎች ናቸው ብየ አምናለሁ ።በጣም ይቅር በሉኝ እና? እኔ በትርጓሜ ጉባኤ ቤት ብዙ ዓመታትን ደክሜያለሁ።ሰባኬ ወንጌል ሁኜም በማገልገል 10 ዓመት ሞላኝ። አሁንም የመጨረሻው ትምህርቴ መጽሐፈ ሊቃውንትን እየጨረስኩ ነው ። ግን ስንት መናፍቃን አሳመንክ ብትሉኝ ከነአኬ ጋራ ሲነጻጸር መልስ የለኝም ። ቀጥታ ሲከራከሩ ሲወያዩ ባይገጥመኝም። የተወያዩትን በፌስቡክም በሌላም ተለቆ ሳያው ግን በእጅጉ ደስተኛ ነው የሆንኩት። ሂደት ላይ ሊሳሳቱ ይችላሉ። በየቀኑ ማስተማርና በየ ቀኑ መከራከር ይለያያሉ። ወጣቶቹ ብዙ ጊዜ ከኢአማንያን ጋራ ከመከራከራቸው የተነሳ ዳኅጸ ልሳንም ዳኅጸ ልቡናም ሊገጥማቸው ይችላል። ዳጥ ደግሞ አንገዳግዶ ይጥላል። ወጣቶቹ እንዳይወድቁባት ቤ/ክርስቲያኗ ልትደግፋቸው ይገባል። ምድያ ደግሞ የዳጥ መንገድ ነው።ብዙ ሰዎች በርሱ እየተራመዱ ወድቀዋል። ምናልባትም ለመውደቅ ሲንገዳገዱ በመደገፍ ፈንታ ከገፋናቸው መውደቅ ብቻ ሳይሆን አወዳደቃቸው የከፋ ይሆናል ። ይህ እንዳይሆን ቤ/ክርስቲያኗ፤ ሊቃውንቱ ከጎናቸው ቁመው በምሥጢር በምክር እና በሀሳብ በሞራልም ጭምር መርዳት አለባቸው ፥
✍️አኬ ስለ ተባለው ወንድማችንም ባለፈው አንድ ነገር ጽፌ ነበር። አሁንም ልጁ ብዙ ጊዜ ከካቶሊኮች ጋራ፤ ከፕሮቴስታንቶች ጋራ፤ ከተሀድሶዎች ጋራ ሁልጊዜ የሚከራከር ከሆነ የቋንቋ የሀሳብ የምልከታ የእይታ ግጭት ሊፈጠር ይችላል ። በእስክንድርያ ከተነሱ ሊቃውንት እንደ ኦሪገን (አርጌንስ) ለመናፍቃን መልስ የሰጠ ፦ከመናፍቃን ጋራ የጨበጣ ውጊያ ያደረገ የለም። ለሌሎች መልስ እየሰጠ ሲሰቃይ ኑሮ እርሱ ግን የአስተምህሮ ግጭት ተገኘበት። ብዙ ሊቃውንት ለመናፍቃን መልስ ለመስጠት ሲታገሉ ከጥረታቸው ብዛት የተነሳ በትምህርታቸው ላይ እንከን ሊመጣ ይችላል ።
ይሄ ደግሞ በሁሉም ቤተ እምነት ባሉ መምህራን ዘንድ ያለ ነው ። ልጁ በርካታ አድማጮች ስለነበሩት የልጁ እንዲህ መባል ለብዙ ምእመናን በተለይ ለወጣኒዎች ጭንቀት ይሆናል። አንድ ነገር ግን እንመን። ልጁ ላይ ያሉት ሀሳቦች" እይታዎች ፤ ምልከታዎች ናቸው እንጅ በፍጹም ምንፍቅናዎች አይደሉም። እነዚህን የመሰሉ ሀሳቦች ደግሞ በጉባኤ ቤት ሁልጊዜ ይነሳሉ።ሁልጊዜ ግን መልስ ይሰጣል።ሀሳቡ ምድያ ላይ ስለተነሳ ክርክሩም ምድያ ላይ ሆነ እንጅ በጉባኤ ቤት አኬ ካነሳቸው የበለጡ የሚያስደነግጡ ሀሳቦች ሁልጊዜ ይነሳሉ።ሁልጊዜ ያከራክራሉ።ወዲያው ምላሽ ያገኛሉ። የአኬ ሀሳብም እንደዚሁ ነው ብየ ተስፋ አደርጋለሁ ።ስለሆነም .....።
🥡 ፅጌ አስተራይ
@Sewsinor
@Sewsinor
።...ዓለም እንደዚህ ናት...።
ጎል ባስቆጠርክ ጊዜ ቁማ ታጨበጭብልሃለች።ሪከርድ በሰበርክ ጊዜ በስምህ ቲሸርት ታሳትምልሃለች።በስምህ ድርጅት ትከፍትልሃለች። ለክርስቶስ ያልገለጠችውን ፍቅሯን ላንተ ትገልጥልሃለች። ነገር ግን ይህንን ያህል የወደደችህ ዓለም! ለጎል የተቃረበ ኳስን ተሳስተህ ብታበላሽ በስምህ ያሳተመችውን ቲሸርት ወዲያው ትቀደዋለች። የድርጅቷን ስምም በሌላ ትለውጣለች። ሰው ነው እና ይሳሳታል ማለቷን ትታ ለምን ተሳሳተ እያለች ታማታሃለች። የተሳሳተ ቢሠራ ነው። ያልተራመደ እንቅፋት አይመታውም።
ምክንያቱም ተኝቷል" በማለት አትረዳልህምም።
በዚህ ውስጥ ዓለም የዘነጋችው ቢኖር ? ለስሂት መኑ ይሌብዋ ያለውን የመዝሙር ጥቅስ ነው።
✍️ በዚህ ሰሞን የታዘብኳቸው ጉዳዮች ብዙዎች ናቸው ።በዋናነት ሶስት መሠራታዊ ነጥቦችን
በአክሊል ዙሪያ በኋላ አነሳለሁ። በሶሻል ምድያው ላይ በርካታ ትምህርቶች እየተሰጡ ነው።ሰውም ከዐውደ ምሕረቱ ይልቅ ሶሻል ምድያው ላይ ሰፍሯል። የምድያው አላማ አማኙን ምድያው ላይ ማስቀረት ሳይሆን ምድያው ላይ የሰፈረውን ምእመን ወደ ዐውደ ምሕረቱ መሳብ ነው። ንቦችን ዛፍ ላይ ፤ አጥር ላይ ልናሰፍራቸው እንችላለን። ኋላ ግን አውራቸውን ይዘን መዓር ወደ ሚሠሩበት ቀፎ እናስገባቸዋለን ።ምክንያቱም አሳ የሚጠመደው ባሕር ላይ ነው። ቆቅም የምታያዘው ዱር ላይ ነው ። የሚከሸኑት ግን ከቤት ውስጥ ነው።
✍️ ምእመናንንም ከሀገር ከሀገሪት ፤ ከሀቃል ከሮቢት፤ ከዱር ከገደሉ ከሶሻል ምድያው የወንጌል መረብን በመጣል ልናጠምዳቸው እንችላለን።የክርስቶስ አካል ብልት የሚሆኑት ግን የጸጋ ግምጃ ቤት በሆነችው በቤተ ክርስቲያኗ ነው።ይህንን ሥራ ደግሞ አሁን በምድያው ውስጥ ያሉ ወጣቶቻችን እየሠሩት ነው ። ይህንን ማበረታታት ግድ ነው ።
✍️ከጥቂት ዓመታት በፊት ምድያው ላይ ሙስሊሞች ንጽጽር ሠራን እያሉ መጽሐፍ ቅዱስን እያጋጩ የእኛ መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚጣላ እንደሚጋጭ አስመስለው ያሠራጩ ነበር። እኛ ደግሞ እንደ ከዋክብት የበዙ ሊቃውንት ቢኖሩንም ምድያው ላይ እንደ አሁኑ የሚሞግቱ የሚከራከሩ ወጣቶች ግን ብዙም አልነበሩንም ። ምድያው ላይ ማለቴ ነው ።
...........✍️ ፕሮቴስታንቶችም ".......
ኦርቶዶክስ ? ሥዕል ታመልካለች፥
☝️ታቦት ታመልካለች ፤
☝️ድንግል ማርያምን ታመልካለች፤
☝️ቅዱሳንን ታመልካለች እያሉ አንድ አምላክ ማምላኳን ክደው በሀሰት ሲኮንኗት ፤ ሲጽፉባት ፦በየምድያው ሲያቀረሹባት እንደ ኮከብ ተወርውረው እንደ አድማሱ ጀምበሬ፤ እንደ ዲ/ን ያረጋል አበጋዝ የመሳሰሉት ውሃ በእሳት ላይ እንደሚነሳሳ ሁሉ እነርሱም በቅናት ተነስተው የመናፍቃንን ምንፍቅና እልም ድርግም የሚያደርጉ ጽሑፎችን ሲጽፉ አይተናል ።ይሁን እንጅ ምድያው ላይ ግን ብዙም አልተራመድንም ነበር ።ታላላቁ ምድያዎች እንኳን እስከ አሁን ሁለት ናቸው ። ይህ ስንፍናችን አሳዛኝ ቢሆንም እንኳን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ በርካታ ወጣቶች በምድያው ላይ ተሠራጭተዋል ።
እኔ እንኳን በመጠኑ የማያቸው ወጣቶች ብዙዎቹ ዲ/ን እንኳን አይደሉም።ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱሱን እንደ ውሃ ይጠጡታል ። ከላይ የጠቀስኳቸው የሙስሊም ኡስታዞች እና የፕሮቼስታንት ፓስተሮች ሊከራከሩ ቀርበው ላብ በላብ ሲሆኑ መልስ አጥተው ሲያቃትቱ አይቼ ተደንቄያለሁ ።የሳቁባቸው እና የተሳለቁባቸው የገድላትን፥ የቅዱሣት ሥዕላትን፤ የታቦትን ፤የቅዱሳን ምልጃን በተመለከተም ብዙዎች እንዲህ ነው እንዴ ? ብለው ሲመለሱ ታይተዋል።ብዙዎች ደግሞ ደንግጠው ከመንቀፍ አፋቸውን ሲቆጥቡ ተመላክቷል። ሌሎች ደግሞ በዚህ ተበሳጭተው በወጣቶቹ ላይ ፖለቲካ ሠርተዋል። በዋናነት ወጣቶቹን እኔ በግሌ የቤ/ክርስቲያኗ የደስታ ፍሬዎች ናቸው ብየ አምናለሁ ።በጣም ይቅር በሉኝ እና? እኔ በትርጓሜ ጉባኤ ቤት ብዙ ዓመታትን ደክሜያለሁ።ሰባኬ ወንጌል ሁኜም በማገልገል 10 ዓመት ሞላኝ። አሁንም የመጨረሻው ትምህርቴ መጽሐፈ ሊቃውንትን እየጨረስኩ ነው ። ግን ስንት መናፍቃን አሳመንክ ብትሉኝ ከነአኬ ጋራ ሲነጻጸር መልስ የለኝም ። ቀጥታ ሲከራከሩ ሲወያዩ ባይገጥመኝም። የተወያዩትን በፌስቡክም በሌላም ተለቆ ሳያው ግን በእጅጉ ደስተኛ ነው የሆንኩት። ሂደት ላይ ሊሳሳቱ ይችላሉ። በየቀኑ ማስተማርና በየ ቀኑ መከራከር ይለያያሉ። ወጣቶቹ ብዙ ጊዜ ከኢአማንያን ጋራ ከመከራከራቸው የተነሳ ዳኅጸ ልሳንም ዳኅጸ ልቡናም ሊገጥማቸው ይችላል። ዳጥ ደግሞ አንገዳግዶ ይጥላል። ወጣቶቹ እንዳይወድቁባት ቤ/ክርስቲያኗ ልትደግፋቸው ይገባል። ምድያ ደግሞ የዳጥ መንገድ ነው።ብዙ ሰዎች በርሱ እየተራመዱ ወድቀዋል። ምናልባትም ለመውደቅ ሲንገዳገዱ በመደገፍ ፈንታ ከገፋናቸው መውደቅ ብቻ ሳይሆን አወዳደቃቸው የከፋ ይሆናል ። ይህ እንዳይሆን ቤ/ክርስቲያኗ፤ ሊቃውንቱ ከጎናቸው ቁመው በምሥጢር በምክር እና በሀሳብ በሞራልም ጭምር መርዳት አለባቸው ፥
✍️አኬ ስለ ተባለው ወንድማችንም ባለፈው አንድ ነገር ጽፌ ነበር። አሁንም ልጁ ብዙ ጊዜ ከካቶሊኮች ጋራ፤ ከፕሮቴስታንቶች ጋራ፤ ከተሀድሶዎች ጋራ ሁልጊዜ የሚከራከር ከሆነ የቋንቋ የሀሳብ የምልከታ የእይታ ግጭት ሊፈጠር ይችላል ። በእስክንድርያ ከተነሱ ሊቃውንት እንደ ኦሪገን (አርጌንስ) ለመናፍቃን መልስ የሰጠ ፦ከመናፍቃን ጋራ የጨበጣ ውጊያ ያደረገ የለም። ለሌሎች መልስ እየሰጠ ሲሰቃይ ኑሮ እርሱ ግን የአስተምህሮ ግጭት ተገኘበት። ብዙ ሊቃውንት ለመናፍቃን መልስ ለመስጠት ሲታገሉ ከጥረታቸው ብዛት የተነሳ በትምህርታቸው ላይ እንከን ሊመጣ ይችላል ።
ይሄ ደግሞ በሁሉም ቤተ እምነት ባሉ መምህራን ዘንድ ያለ ነው ። ልጁ በርካታ አድማጮች ስለነበሩት የልጁ እንዲህ መባል ለብዙ ምእመናን በተለይ ለወጣኒዎች ጭንቀት ይሆናል። አንድ ነገር ግን እንመን። ልጁ ላይ ያሉት ሀሳቦች" እይታዎች ፤ ምልከታዎች ናቸው እንጅ በፍጹም ምንፍቅናዎች አይደሉም። እነዚህን የመሰሉ ሀሳቦች ደግሞ በጉባኤ ቤት ሁልጊዜ ይነሳሉ።ሁልጊዜ ግን መልስ ይሰጣል።ሀሳቡ ምድያ ላይ ስለተነሳ ክርክሩም ምድያ ላይ ሆነ እንጅ በጉባኤ ቤት አኬ ካነሳቸው የበለጡ የሚያስደነግጡ ሀሳቦች ሁልጊዜ ይነሳሉ።ሁልጊዜ ያከራክራሉ።ወዲያው ምላሽ ያገኛሉ። የአኬ ሀሳብም እንደዚሁ ነው ብየ ተስፋ አደርጋለሁ ።ስለሆነም .....።
🥡 ፅጌ አስተራይ
@Sewsinor
@Sewsinor