በትምህርት ቤቶች አካባቢ አዋኪ ድርጊት በፈጸሙ የንግድ ድርጅቶች ላይ ህጋዊ እና አስተዳደራዊ እርምጃ ተወሰደ::
በአዲስ አበባ ከተማ በትምህርት ቤቶች አካባቢ አዋኪ ድርጊት በፈጸሙ የንግድ ድርጅቶች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱን የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ኃላፊ ወይዘሮ ሊዲያ ግርማ በሰጡት መግለጫ፥ የፔንሲዮን ቤቶችን ጨምሮ በትምህርት ቤቶች አካባቢ አዋኪ ድርጊት በፈጸሙ 879 የንግድ ድርጅቶች ላይ ህጋዊ እርምጃ መውሰዱን ተናግረዋል።
በዚህም አዋኪ ድርጊት በፈፈሙ በ184 ጫትና ሺሻ ቤቶች፣ 112 አረቄ ቤቶች፣ ግሮሰሪ መጠጥ ቤቶች 48፣ 12 ፔንሲዮን ቤቶች፣ 120 ፑል ቤቶች፣ የድምፅ ብክለት ያለባቸው ሙዚቃ ቤቶችና ቪዲዮ ቤቶች 122 እንዲሁም 171 ሌሎች የንግድ ቤቶች ላይ እርምጃ መወሰዱን ነው የተገለፀው።
እርምጃ የተወሰደው በሁሉም ትምህርት ቤቶች ያለውን የመማር ማስተማር ሂደት ሰላማዊ ለማድረግ እንደሆነምየአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ ተናግረዋል ።
እርምጃ የተወሰደው በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ በሁሉም ክፍለ ከተሞች ሲሆን የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ከትምህርት ቢሮ፣ ንግድ ቢሮ፣ ፓሊስና ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ጋር የጋራ ግብረ ሃይል በማቋቋም በጥናትን ላይ መሠረት በማድረግ የተወሰደ እርምጃ እንደሆነም ተገልፃል።
@subitime
በአዲስ አበባ ከተማ በትምህርት ቤቶች አካባቢ አዋኪ ድርጊት በፈጸሙ የንግድ ድርጅቶች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱን የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ኃላፊ ወይዘሮ ሊዲያ ግርማ በሰጡት መግለጫ፥ የፔንሲዮን ቤቶችን ጨምሮ በትምህርት ቤቶች አካባቢ አዋኪ ድርጊት በፈጸሙ 879 የንግድ ድርጅቶች ላይ ህጋዊ እርምጃ መውሰዱን ተናግረዋል።
በዚህም አዋኪ ድርጊት በፈፈሙ በ184 ጫትና ሺሻ ቤቶች፣ 112 አረቄ ቤቶች፣ ግሮሰሪ መጠጥ ቤቶች 48፣ 12 ፔንሲዮን ቤቶች፣ 120 ፑል ቤቶች፣ የድምፅ ብክለት ያለባቸው ሙዚቃ ቤቶችና ቪዲዮ ቤቶች 122 እንዲሁም 171 ሌሎች የንግድ ቤቶች ላይ እርምጃ መወሰዱን ነው የተገለፀው።
እርምጃ የተወሰደው በሁሉም ትምህርት ቤቶች ያለውን የመማር ማስተማር ሂደት ሰላማዊ ለማድረግ እንደሆነምየአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ ተናግረዋል ።
እርምጃ የተወሰደው በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ በሁሉም ክፍለ ከተሞች ሲሆን የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ከትምህርት ቢሮ፣ ንግድ ቢሮ፣ ፓሊስና ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ጋር የጋራ ግብረ ሃይል በማቋቋም በጥናትን ላይ መሠረት በማድረግ የተወሰደ እርምጃ እንደሆነም ተገልፃል።
@subitime