የተባረከች ድንግል ማርያም፣ የእግዚአብሔር እናት፣ ምስጋና
ቸር አምላክ፣ በርህን ለክፉዎችና ለኃጢአተኞች የከፈትክ፣ ውበትህን አይቼ እንድደነቅ ግባ በልኝ።
የምሕረት መጋዘን፣ ፍትሕ የሌላቸው እንኳን ከአንተ የሚጠግቡበት፣ከአንተ ልመገብ፣ ምክንያቱም አንተ ለሚካፈልህ ሙሉ ሕይወት ነህና።
የነፍስን ሐዘን የሚያረሳ ጽዋ፣ ጠጥቼ ከአንተ ጥበብን ላገኝና ታሪክህን ልተርክ።
ያለጸጸት ለሰው ዘር ክብረትን የምትሰጥ፣ በመዝሙርህ ውብ ነገሮችን ልዘምር።
የልዑል ልጅ፣ ትሕትናን የመረጥክ፣ ስለ ታላቅነትህ ልናገር እርዳኝ።
ከሰማይ የወረድክ፣ ከእኛ ጋር መኖርን የወደድክ፣ ቃሌ ወደ ላይ ከፍ ይበልና ይማጸንህ።
ጌታችን ሆይ፣ ሕያው ቃልና ጥልቅ ንግግር ነህ፣ ለሚሰማህም ጸጋን የምትሰጥ።
ስለ አንተ የሚናገር ሁሉ ከአንተ በተነሳ ነው የሚናገረው፣ ቃል፣ አእምሮና ሕሊናም አንተ ነህና።
ያለ አንተ ሐሳብ አይመላለስም፣ ያለ ፈቃድህም ከንፈር አይንቀሳቀስም።
ያለ ትእዛዝህ ድምፅ አይሰማም፣ ያለ ቸርነትህም መስማት አይቻልም። እነሆ፣ ጸጋህ በሩቅም በቅርብም ሞልቷል፤
በርህ ለጻድቅም ለኃጢአተኛም ወደ አንተ ክፍት ነው።
ሁሉም በአንተ ባለጸጋ ነው፣
አንተም በልግስና ትሰጣለህ፤
ንግግር ከአንተ በውበት ይበልጽግና ለአንተ ይናገር።
የድንግል ልጅ ሆይ፣ ስለ እናትህ እንድናገር ፍቀድልኝ፣
ስለ እርሷ የሚነገረው ነገር ከእኛ በላይ መሆኑን እያወቅሁ።
(ቅዱስ ያዕቆብ ዘስሩግ: on the mother of God )
ቸር አምላክ፣ በርህን ለክፉዎችና ለኃጢአተኞች የከፈትክ፣ ውበትህን አይቼ እንድደነቅ ግባ በልኝ።
የምሕረት መጋዘን፣ ፍትሕ የሌላቸው እንኳን ከአንተ የሚጠግቡበት፣ከአንተ ልመገብ፣ ምክንያቱም አንተ ለሚካፈልህ ሙሉ ሕይወት ነህና።
የነፍስን ሐዘን የሚያረሳ ጽዋ፣ ጠጥቼ ከአንተ ጥበብን ላገኝና ታሪክህን ልተርክ።
ያለጸጸት ለሰው ዘር ክብረትን የምትሰጥ፣ በመዝሙርህ ውብ ነገሮችን ልዘምር።
የልዑል ልጅ፣ ትሕትናን የመረጥክ፣ ስለ ታላቅነትህ ልናገር እርዳኝ።
ከሰማይ የወረድክ፣ ከእኛ ጋር መኖርን የወደድክ፣ ቃሌ ወደ ላይ ከፍ ይበልና ይማጸንህ።
ጌታችን ሆይ፣ ሕያው ቃልና ጥልቅ ንግግር ነህ፣ ለሚሰማህም ጸጋን የምትሰጥ።
ስለ አንተ የሚናገር ሁሉ ከአንተ በተነሳ ነው የሚናገረው፣ ቃል፣ አእምሮና ሕሊናም አንተ ነህና።
ያለ አንተ ሐሳብ አይመላለስም፣ ያለ ፈቃድህም ከንፈር አይንቀሳቀስም።
ያለ ትእዛዝህ ድምፅ አይሰማም፣ ያለ ቸርነትህም መስማት አይቻልም። እነሆ፣ ጸጋህ በሩቅም በቅርብም ሞልቷል፤
በርህ ለጻድቅም ለኃጢአተኛም ወደ አንተ ክፍት ነው።
ሁሉም በአንተ ባለጸጋ ነው፣
አንተም በልግስና ትሰጣለህ፤
ንግግር ከአንተ በውበት ይበልጽግና ለአንተ ይናገር።
የድንግል ልጅ ሆይ፣ ስለ እናትህ እንድናገር ፍቀድልኝ፣
ስለ እርሷ የሚነገረው ነገር ከእኛ በላይ መሆኑን እያወቅሁ።
(ቅዱስ ያዕቆብ ዘስሩግ: on the mother of God )