አሜሪካንን ለምን እንዲህ አሰብሽ ብለን መጠየቅ የዋህነት ነው፤ ኢምፕሪያሊስቶች የሚያስቡት እንዲህ ነው፡፡ ለሀገራት ሲያስቡ እስከመጨረሻው ነው፤ ስለሊቢያ አስበዋል፤ ስለአፍጋኒስታን አስበዋል፤ ስለኢራቅ እንቅልፍ አጥተዋል፤ ስለየመን አስበዋል፤ . . . .
.
ልብ እንበል! ስለሀገራችን- ስለአማራ፣ ስለኦሮምያ፣ ስለትግራይ፣ ስለአፋር፣ ስለሱማሌ፣ ስለሀረሪ፣ ስለጋምቤላ፣ ስለቤንሻንጉል፣ ስለሲዳማ፣ ስለደቡብ ህዝቦች፣ ስለደቡብ ምእራብ፣ ስለአዲስ አበባ፣ ስለድሬዳዋ ማሰብ ያለብን እኛ ኢትዮጵያውያን ነን፡፡ እንጠይቅ! ባህር አቋርጦ አሜሪካና አውሮፓ ስለእኛ ስለምን ያስባል? ምን ፈልጎ? . . . ከሰሜን ጫፍ እስከ ደቡብ ጫፍ፣ ከምእራብ እስከ ምስራቅ ጫፍ ስለኢትዮጵያ ማሰቢያው፣ በአንድነት መነሻው ጊዜ ዛሬ ነው፡፡ . . . .በህብረት ለሀገራችን እናስብ፤ እንስራ፤ እንድናለን፡፡