ሃልወተ እግዚአብሔር & The problem of evil
አምላክ እንደ ሆንክ አስብ፡፡ አለማትን ሁሉ ፈጠርክ። እናም ፈጥረህ ስትጨርስ የእጅህን አቧራ አራግፈህ ገሸሽ አልክ፤ ሁሉንም ፍትህን ለመመልከት በሚያስችልህም ሰባተኛ ሰማይ ላይ መኖሪያህን አዘጋጀህ። የፈጠርከው ዓለም ውብ ነው፤ እልፍ አእላፍ ከዋክብቶችንም በውስጡ ይዟል፤ ከፈጠርካቸው አለማትም በአንዷ ላይ፣ ላባ እና መንቁር አልባ የሆነ በሁለት እግር የሚጓዝ ፍጡር አለባት... ነገር ሁሉ መልካም እንደሆነም አየህ፡፡
ጎንህን ለማሳረፍም ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ውስጥ ገባህ። ሆኖም በመሃል የፈጠርካቸው ፍጡራን በጫጫታቸው ቀሰቀሱህ። አስታወስክ እነዚያ በሁለት እግር ሂያጅ ፍጡራን... እርስ በእርስ እየተገዳደሉ ነው፤ ከፊሎቹም ምግብ እያሉ ወዳንተ ያለቅሳሉ፤ ሌሎች በህመም ይሰቃያሉ...
አሁን ላይ አንተ ምን ታደርግላቸዋለህ? ማንስ ነው ለዚህ ሁሉ መከራ ተጠያቂ የሚሆነው?
ይህ ጥያቄ “problem of evil” ተብሎ ይጠራል፡፡ በዓለም ሁሉ ስለምን መጥፎ ነገሮች ኖሩ?
ስኮትላንዳዊው ፈላስፋ ዴቪድ ሂዩም
በአምላኩ ላይ ጥያቄን ያነሳል ፦
አምላክ ሁሉን ቻይ (omnipotent)፣
ሁሉን አዋቂ (omniscient) እና
ፍጹም መልካም(omnibenevolent) ነውን?
ስለምንስ መከራችንን ሳያይ ቀረ፣ ይህ ሁሉ ስቃይስ በእኛ ላይ ሲሆን እርሱ የት ነበር? ሲል ይጠይቃል።
ፍጹም መልካም፣ ሁሉን ወዳጅ የሆነ አምላክ እንዴት አይሁዶች በእሳት እንዲጠበሱ ፈቀደ? ስለምን ህጻናት በርሃብ እንዲሞቱ ሆኑ? ደካማው ሚዳቋ ስለምን ለበረታው አንበሳ ምግብ እንዲሆን ተፈረደበት?
ምናልባት ሁሉን ቻይ ሳይሆን ቀርቶ ይሆን? መርዳት እየፈለገ ሆኖም አቅሙ ስለሌለው ነው እጁን ያልዘረጋው?
ምናልባትም አላወቀም ይሆናል? ሁሉን አዋቂ ካልሆነ ልንፈርድበት አይገባም፡፡
ሆኖም ግን ይህን አምላክ ፍጹም መልካም፣ ሁሉን ቻይ እና ፍጹም አዋቂ ነው ብለን ማለት አንችልም፡፡
በተመሳሳይ ጊዜ ሶስቱንም መሆን አይችልም፡፡ ከሶስቱ ባህርያቱ ቢያንስ አንዱን ልንቀማው ይገባል፡፡
በመከራችን አልረዳንምና ለመከራችን ተጠያቂውም እርሱ ይሆናል። የሚጠብቀን አንቀላፍቶ ይሆን?
ሁለት አይነት ክፋቶች በዓለም ላይ አሉ - ምድራዊ እና ተፈጥሯዊ (ለምሳሌ፤ የመሬት መንቀጥቀጥ፣ ድርቅ፣ ወረርሽኝ እና ወዘተ) እና ሰዋዊ (መገዳደል፣ ውሸት፣ መስረቅ እና ወዘተ)
ሁለቱም ክፋቶች ጥያቄን ያስነሳሉ፡፡
የመጀመሪያው ማን ነው ዓለምን ከነችግሮቿ የፈጠራት የሚል ጥያቄን ያስነሳል። ሁለተኛው ሰዎች ክፋት እንዲያደርጉ የፈቀደላቸው ማን ነው? የሚል ጥያቄን ያስነሳል፡፡
ለዚህ ጥያቄ መልስ ለመስጠት አስቸጋሪ የሚያደርገው በኃይማኖተኞች ዘንድ የተሳለው አምላክ ሃያል መሆኑ ነው። አምላክ የፈለገውን እንደፈለገው ቢፈጽም የሚጠይቀው አካል መኖር የለበትም ምክንያቱም እርሱ ሃያል ነው።
በኃይማኖተኞች ዘንድ ለ “problem of evil” የተሰጡ ምላሾች አሉ። ምላሾቹም ቲዮዲሲ ተብለው ይጠራሉ።
ሶስት አይነት መልሶችንም ያቀርቡልናል፡፡
⭐️የመጀመሪያው የሰው ልጅ ክፋትን እንዲሰራ ነጻ ፍቃድ አለው የሚል ይሆናል። ሰው እሳት እና ፍትፍት ከፊቱ ቀርቦለታል፤ መልካሙን ወይም መጥፎውን የመምረጥ ድርሻውም የእርሱ ነው ይሉናል፡፡
⭐️ሁለተኛው፤ እኛ ማን ነን ይህ ክፉ ነው፣ ይህ ደግሞ መጥፎ ነው ብለን የምንሰይመው? ለምሳሌ እሳተ ገሞራ በተፈጥሮው መጥፎ ይመስላል፤ የብዙ አራዊቶችንም ሕይወት ሊቀጥፍ ይችላል፤ ሆኖም እሳተ ገሞራ በመኖሩ ምክንያት ነው ተራራዎች የተፈጠሩት ተራሮችም ለደኖች፣ ወንዞች እና ሌሎችም መፈጠር ምክንያት ናቸው፡፡ እናም መልካም እና መጥፎ የሆነውን የሚለይልን አምላካችን እንጂ እኛ አይደለንም፡፡
⭐️ሶስተኛው ሁሉም ነገር የፈጣሪ እቅድ አካል ነው፡፡ ለምሳሌ አንድ ህጻን በርሃብ ሲሞት ምናልባትም ወደ ዘላለማዊ ማር እና ወተት ወደሚፈስባት ዓለም እየተጓዘ ይሆናል። የእርሱንም እቅድ መጨረሻ አናውቅምና ይህ መልካም ነው፣ ይህ መጥፎ ነው ማለት አንችልም፡ በሕይወትህ መጥፎ አጋጣሚዎች ተከስተውብህ የሆኑት ለበጎ ነው እንኳንም ሆኑ ብለህ አታውቅም? ምናልባትም ይህም የእርሱ
እቅድ አካል ይሆናል፡፡
ምንጭ -ፍልስፍና ከዘርዓ ያዕቆብ-ሶቅራጠስ
ፁሁፍ -ፍሉይ አለም
በኃይማኖተኞች ዘንድ ለ “problem of evil” የተሰጡ ምላሾች በቂ ናቸው ብላችሁ ታስባለችሁ ?ከነዚህ ውጪስ ሌሎች ምላሾች የሉም ይሁን?
ግሩፕ ላይ ተወያዩበት
👇👇👇
https://t.me/+XgPfefgVVvRhZjk0
አምላክ እንደ ሆንክ አስብ፡፡ አለማትን ሁሉ ፈጠርክ። እናም ፈጥረህ ስትጨርስ የእጅህን አቧራ አራግፈህ ገሸሽ አልክ፤ ሁሉንም ፍትህን ለመመልከት በሚያስችልህም ሰባተኛ ሰማይ ላይ መኖሪያህን አዘጋጀህ። የፈጠርከው ዓለም ውብ ነው፤ እልፍ አእላፍ ከዋክብቶችንም በውስጡ ይዟል፤ ከፈጠርካቸው አለማትም በአንዷ ላይ፣ ላባ እና መንቁር አልባ የሆነ በሁለት እግር የሚጓዝ ፍጡር አለባት... ነገር ሁሉ መልካም እንደሆነም አየህ፡፡
ጎንህን ለማሳረፍም ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ውስጥ ገባህ። ሆኖም በመሃል የፈጠርካቸው ፍጡራን በጫጫታቸው ቀሰቀሱህ። አስታወስክ እነዚያ በሁለት እግር ሂያጅ ፍጡራን... እርስ በእርስ እየተገዳደሉ ነው፤ ከፊሎቹም ምግብ እያሉ ወዳንተ ያለቅሳሉ፤ ሌሎች በህመም ይሰቃያሉ...
አሁን ላይ አንተ ምን ታደርግላቸዋለህ? ማንስ ነው ለዚህ ሁሉ መከራ ተጠያቂ የሚሆነው?
ይህ ጥያቄ “problem of evil” ተብሎ ይጠራል፡፡ በዓለም ሁሉ ስለምን መጥፎ ነገሮች ኖሩ?
ስኮትላንዳዊው ፈላስፋ ዴቪድ ሂዩም
በአምላኩ ላይ ጥያቄን ያነሳል ፦
አምላክ ሁሉን ቻይ (omnipotent)፣
ሁሉን አዋቂ (omniscient) እና
ፍጹም መልካም(omnibenevolent) ነውን?
ስለምንስ መከራችንን ሳያይ ቀረ፣ ይህ ሁሉ ስቃይስ በእኛ ላይ ሲሆን እርሱ የት ነበር? ሲል ይጠይቃል።
ፍጹም መልካም፣ ሁሉን ወዳጅ የሆነ አምላክ እንዴት አይሁዶች በእሳት እንዲጠበሱ ፈቀደ? ስለምን ህጻናት በርሃብ እንዲሞቱ ሆኑ? ደካማው ሚዳቋ ስለምን ለበረታው አንበሳ ምግብ እንዲሆን ተፈረደበት?
ምናልባት ሁሉን ቻይ ሳይሆን ቀርቶ ይሆን? መርዳት እየፈለገ ሆኖም አቅሙ ስለሌለው ነው እጁን ያልዘረጋው?
ምናልባትም አላወቀም ይሆናል? ሁሉን አዋቂ ካልሆነ ልንፈርድበት አይገባም፡፡
ሆኖም ግን ይህን አምላክ ፍጹም መልካም፣ ሁሉን ቻይ እና ፍጹም አዋቂ ነው ብለን ማለት አንችልም፡፡
በተመሳሳይ ጊዜ ሶስቱንም መሆን አይችልም፡፡ ከሶስቱ ባህርያቱ ቢያንስ አንዱን ልንቀማው ይገባል፡፡
በመከራችን አልረዳንምና ለመከራችን ተጠያቂውም እርሱ ይሆናል። የሚጠብቀን አንቀላፍቶ ይሆን?
ሁለት አይነት ክፋቶች በዓለም ላይ አሉ - ምድራዊ እና ተፈጥሯዊ (ለምሳሌ፤ የመሬት መንቀጥቀጥ፣ ድርቅ፣ ወረርሽኝ እና ወዘተ) እና ሰዋዊ (መገዳደል፣ ውሸት፣ መስረቅ እና ወዘተ)
ሁለቱም ክፋቶች ጥያቄን ያስነሳሉ፡፡
የመጀመሪያው ማን ነው ዓለምን ከነችግሮቿ የፈጠራት የሚል ጥያቄን ያስነሳል። ሁለተኛው ሰዎች ክፋት እንዲያደርጉ የፈቀደላቸው ማን ነው? የሚል ጥያቄን ያስነሳል፡፡
ለዚህ ጥያቄ መልስ ለመስጠት አስቸጋሪ የሚያደርገው በኃይማኖተኞች ዘንድ የተሳለው አምላክ ሃያል መሆኑ ነው። አምላክ የፈለገውን እንደፈለገው ቢፈጽም የሚጠይቀው አካል መኖር የለበትም ምክንያቱም እርሱ ሃያል ነው።
በኃይማኖተኞች ዘንድ ለ “problem of evil” የተሰጡ ምላሾች አሉ። ምላሾቹም ቲዮዲሲ ተብለው ይጠራሉ።
ሶስት አይነት መልሶችንም ያቀርቡልናል፡፡
⭐️የመጀመሪያው የሰው ልጅ ክፋትን እንዲሰራ ነጻ ፍቃድ አለው የሚል ይሆናል። ሰው እሳት እና ፍትፍት ከፊቱ ቀርቦለታል፤ መልካሙን ወይም መጥፎውን የመምረጥ ድርሻውም የእርሱ ነው ይሉናል፡፡
⭐️ሁለተኛው፤ እኛ ማን ነን ይህ ክፉ ነው፣ ይህ ደግሞ መጥፎ ነው ብለን የምንሰይመው? ለምሳሌ እሳተ ገሞራ በተፈጥሮው መጥፎ ይመስላል፤ የብዙ አራዊቶችንም ሕይወት ሊቀጥፍ ይችላል፤ ሆኖም እሳተ ገሞራ በመኖሩ ምክንያት ነው ተራራዎች የተፈጠሩት ተራሮችም ለደኖች፣ ወንዞች እና ሌሎችም መፈጠር ምክንያት ናቸው፡፡ እናም መልካም እና መጥፎ የሆነውን የሚለይልን አምላካችን እንጂ እኛ አይደለንም፡፡
⭐️ሶስተኛው ሁሉም ነገር የፈጣሪ እቅድ አካል ነው፡፡ ለምሳሌ አንድ ህጻን በርሃብ ሲሞት ምናልባትም ወደ ዘላለማዊ ማር እና ወተት ወደሚፈስባት ዓለም እየተጓዘ ይሆናል። የእርሱንም እቅድ መጨረሻ አናውቅምና ይህ መልካም ነው፣ ይህ መጥፎ ነው ማለት አንችልም፡ በሕይወትህ መጥፎ አጋጣሚዎች ተከስተውብህ የሆኑት ለበጎ ነው እንኳንም ሆኑ ብለህ አታውቅም? ምናልባትም ይህም የእርሱ
እቅድ አካል ይሆናል፡፡
ምንጭ -ፍልስፍና ከዘርዓ ያዕቆብ-ሶቅራጠስ
ፁሁፍ -ፍሉይ አለም
በኃይማኖተኞች ዘንድ ለ “problem of evil” የተሰጡ ምላሾች በቂ ናቸው ብላችሁ ታስባለችሁ ?ከነዚህ ውጪስ ሌሎች ምላሾች የሉም ይሁን?
ግሩፕ ላይ ተወያዩበት
👇👇👇
https://t.me/+XgPfefgVVvRhZjk0