ምስለ አድባራት ወገዳማት


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን" "ስለ ቅዱሳን እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል" ሊቁ ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri




'https://t.me/addlist/2CQ3e4ZJYT9hZGNk' rel='nofollow'>📌ሰው ሲወለድ ሙስሊም ነበር ይላሉ ሙስሊሞች በተጨማሪ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ«እኔ ጌታ ነኝ አምልኩኝ አላለም ፣ መጽሐፍ ቅዱስ ተበርዞዋል ይላሉ» 'https://t.me/addlist/2CQ3e4ZJYT9hZGNk' rel='nofollow'>እንግዲህ ለእያንዳንዱ ከሙስሊም ለሚመጣ ጥያቄ አጥጋቢ መልስ ለማግኘት ከፈለጉ ይህን ቻናል ይቀላቀሉ።
የተበረዘው መፅሐፍ ቅዱስ ነው ወይ  ቁርአን ? አንድ ቅጂ ብቻ አለው ፍፁም ከፈጣሪ ነው ተብሎ በሙስሊሞች የሚታመነው በዚ በኛ ዘመን 4 ዓይነት ቅጂዎች አሉት'https://t.me/addlist/2CQ3e4ZJYT9hZGNk' rel='nofollow'>.....READ MORE


📡 በዝህ ቻናል የተለያዩ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙሮች የሚያገኙበት ቻናል ነው።
       'https://t.me/addlist/2CQ3e4ZJYT9hZGNk' rel='nofollow'> ◤◢◤◢◤◢◣◥◣◥◣◥
               ይ🀄️ላ🀄️ሉ
        ◤◢◤◢◤◢◣◥◣◥◣◥

🔑 የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ዘማሪዎች ውስጥ የማንን 'https://t.me/addlist/2CQ3e4ZJYT9hZGNk' rel='nofollow'>ዝማሬ ማግኘት ይፈልጋሉ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
🔴የቴዎድሮስ ዮሴፍ መዝሙር
⚫️የዳግማዊ ደርቤ መዝሙር
ዝ?የቀዳሜጸጋ መዝሙር
⚫️የዘማሪት ለምለም ከበደ መዝሙር
🔴የኪነጥበብ መዝሙር
⚫️የይልማ ኃይሉ መዝሙር
🔴የዘማሪ አቤል መክብብ መዝሙር
⚫️የዘማሪት ትንቢት ቦጋለ እና      ወ.ዘ.ተ......
        ◤◢◤◢◤◢◣◥◣◥◣◥
               ይ🀄️ላ🀄️ሉ
        ◤◢◤◢◤◢◣◥◣◥◣◥
🛑እነሆ አዲስ ቻናል ይዘንሎት መጣን🛑
በማርያም ይህን ቻናል ሳይቀላቀሉ እንዳያልፉ ይደሰቱበታል መርጠን ለናንተ አቀረብንሎ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
'https://t.me/addlist/2CQ3e4ZJYT9hZGNk' rel='nofollow'>▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

        ◤◢◤◢◤◢◣◥◣◥◣◥


         █   𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒 ➲      █       

 
         ◣◥◣◥◣◥◤◢◤◢◤◢

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


🎤✨ድምፀ ተዋህዶ✨🎤 dan repost
“ወእምግርማሁ ተሀውኩ ወኰኑ ከመ አብድንት እለ የአቅቡ መቃብረ [ እርሱን ከመፍራት የተነሣ መቃብሩን የሚጠብቁት ታወኩ እንደ በድንም ሆኑ] ” (ማቴ 28፥4)

🌿 ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን፤

                በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን፤ 🌿

🌿 አሰሮ ለሰይጣን፤

                   አግዐዞ ለአዳም፤🌿

🌿ሠላም፤

                   እምይዕዜሰ፤ 🌿

🌿ኮነ፤

             ፍስሐ ወሠላም፡🌿



እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤ በሰላም አደረሳችሁ !! ✝️🌿


🎤✨ድምፀ ተዋህዶ✨🎤 dan repost
"በስመ #አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"።

📣 እንኳን
#ለዐቢይ_ጾም_ሰባተኛ_ሳምንት_ለኒቆዲሞስ #እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰ።


#የዚህ_ሳምንት_የኒቆዲሞስ_መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ በ፭ "ሖረ ኀቤሁ #ዘስሙ_ኒቆዲሞስ ወይቤሎ #ለኢየሱስ_ረቢ_ንህነ_ነአምን ብከ ከመ እምኀበ #አብ_መጻእከ መራሔ ሕይወትነ ወሠራየ ኀጢአትነ ከመ #እምኀበ_አብ_መጻእከ ከመ ትኩን መምህረ ዕጓለ አንበሳ ሰከብከ ወኖምከ አንሥአኒ በትንሣኤከ። ትርጉም፦ አስቀድሞ ሌሊት ወደ እርሱ ይሄድ የነበረ #ስሙ_ኒቆዲሞስ የሚባል መምህር ሆይ #ከአብ_አካል_ዘእምአካል ባሕርይ ዘእምባሕርይ ተወልደህ ወደዚህ ዓለም እንደ መጣህ ፈጽሞ እናምንብሃለን፤ የሕይወታችን መሪ ኀጢአታችንን ይቅር የምትል ነህ አለው"። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በጾመ_ድጓው_ላይ።

#ቅዱስ_ኒቆዲሞስ፦ ከፈሪሳውያን ወገን የአይሁድ አለቃ የነበረው ሰው ነው፡፡ የአይሁድ አለቆች #አምላካችንኢየሱስ_ክርስቶስን "ምልክት አሳየን" እያሉ ይፈታተኑት ነበር፡፡ #ጌታችን ስለ ሞቱና ትንሣኤው በምሳሌ እያስረዳ ቢያስተምራቸውም እነርሱ ግን አልገባቸውም ነበር፡፡ ከዚህም አልፎ #ጌታችን በተአምራቱ የታመሙትን ሲፈውስ "ሕጋችን ተሻረ" ይሉ ነበር፡፡ በዚህ ዅሉ ተአምራትና ትምህርት የአይሁድ አለቆች #ክርስቶስን ለመክሰስ በሚፈልጉበት ወቅት ከአይሁድ አለቆች አንዱ ኒቆዲሞስ በቀን እንዳያደርገው አይሁድን ቢፈራ፣ አንድም ጊዜ ባያደርሰው እንደ ባልንጀሮቹ #ክርስቶስን ሳይቃወም በሌሊት ወደ #ጌታችን ዘንድ እየሔደ ወንጌልን ይማር ነበር፡፡

#አምላካችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ በነፍስ የታመሙትን በቃሉ፣ በሥጋ የታመሙትን በተአምራቱ ሲፈውስ ኒቆዲሞስ ሰምቶ፣ ተመልክቶ በመምህርነቱ ሳይኮራ አለቅነቱን መመኪያ ሳያደርግ በልቦናው የተሳለውን እውነትን የመፈለግ ስሜት አንግቦ ከ #ጌታው፣ ከመምህሩ ከ #ክርስቶስ ዘንድ በሌሊት ይገሰግስ ነበር (ዮሐ. ፫፥፩)፡፡ ምስክርነቱንም እንዲህ ሲል መስጠት ጀመረ፤ "መምህር ልታስተምር ከ #እግዚአብሔር ዘንድ እንደ መጣህ እናውቃለን፡፡ #እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ከኾነ በቀር አንተ የምታደርገውን ተአምራት ሊያደርግ የሚችል የለምና" (ዮሐ. ፱፥፳፬፤ ሐዋ. ፲፥፴፰)፡፡

ይህን ምስክርነቱን በሚሰጥበት ጊዜም ጎዶሎን የሚሞላ፤ አላዋቂነት በአዋቂነት የሚለውጥ፤ ከምድራዊ ዕውቀት ወደ ሰማያዊው ምሥጢር የሚያሸጋግር አምላክ "ዳግመኛ ያልተወለደ የ #እግዚአብሔርን መንግሥት ለማየት አይችልም"። በማለት የአይሁድ መምህር ለኾነው ኒቆዲሞስ ቢያስተምረው ምሥጢሩ አልተገለጠለትም ነበርና "ሰው ከሸመገለ በኋላ ዳግመኛ መወለድ እንደምን ይቻላል? ዳግመኛ ይወለድ ዘንድወደ እናቱ ማኅፀን ተመልሶ መግባት ይችላልን?" በማለት ጥያቄ አቅርቧል (ዮሐ. ፫፥፮፤ ፩ኛጴጥ. ፩፥፳፫)፡፡ "እውነት እውነት እልሃለሁ፤ ዳግመኛ ከውኃና ከ #መንፈስ_ቅዱስ ያልተወለደ ወደ #እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም፡፡ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው፡፡ ከመንፈስም የተወለደ መንፈስነውና"። (ኤፌ. ፭፥፳፮) በማለት #አምላካችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ ለኒቆዲሞስ ቢያስረዳውም ምሥጢሩ ከአቅሙ በላይ ስለ ኾነበት እንደምን ይቻላል? በማለት ጠይቋል፡፡

አበ ብዙኃን አብርሃም ከአምላኩ ሞገስን አግኝቶ የሰዶምና ገሞራ ጥፋት እንዳይደርስ ለመማለድ ከ #እግዚአብሔር ጋር ሲነጋገር እንደ ነበረ፤ ኒቆዲሞስም አላዋቂነቱን አምኖ ያልገባውን ምሥጢር ከአምላኩ በጠየቀ ጊዜ #ኢየሱስ_ክርስቶስም፡- "አንተ የእስራኤል መምህራቸው ኾነህ ሳለ ይህን ነገር አታውቅምን? በምድር ያለውን ስንነግራችሁ ካላመናችሁ በሰማይ ያለውን ብንነግራችሁ እንደምን ታምናላችሁ? ከሰማይ ከወረደው ከሰው ልጅ በቀር ወደ ሰማይየወጣ የለም … ሙሴ በምድረ በዳ እባቡን እንደ ሰቀለ የሰውልጅ እንዲሁ ይሰቀላል፡፡ ያመነበት ዅሉ ለዘለዓለም ሕያው ኾኖ እንዲኖር እንጂ እንዲጠፋ አይደለም ..." እያለ ሰው በመብል ምክንያት የአምላኩን ትእዛዝ አፍርሶ ከ #እግዚአብሔር ቢለይም የሰው ልጅ ያጣውን ልጅነት ለመመለስ፣ ስመ ክርስትናን፣ ሀብተ ወልድን ለመስጠት #ጌታችን መምጣቱን አስረዳው (ዮሐ. ፫፥፲፬)፡፡ ይህን የ #ክርስቶስን የማዳን ሥራና በሥጋ መገለጥም "ሐወጽከኒ ሌሊተ ወፈተንኮ ለልብየ አመከርከኒ ወኢተረክበ ዐመፃ በላዕሌየ ከመ ኢይንብብ አፉየ ግብረ እጓለ እመሕያው፤ ልቤን ፈተንኸው፡፡ በሌሊትም ጐበኘኸኝ፤ ፈተንከኝም፡፡ ምንም አላገኘህብኝም፡፡ የሰውን ሥራ አፌ እንዳይናገር ፈቃዴ ነው" (መዝ. ፲፮፥፫) በማለት ቅዱስ ዳዊት ከኒቆዲሞስ ሕይወት ጋር በማዛመድ አመሥጥሮታል፡፡

በሌሊት ከአምላኩ ተምሮ ምሥጢሩ የተገለጸለት ኒቆዲሞስ ቀድሞ በአደባባይ ሔዶ መማርን ይፈራ እንዳልነበረ ምሥጢሩ ሲገለጽለት ግን አይሁድ #ጌታችንን በሰቀሉት ዕለት ፍርኃት ርቆለት ከአርማትያሱ ዮሴፍ ጋር ቅዱስ ሥጋውን ገንዞ ለመቅበር በቃ፡፡ "ወአልቦ ፍርኃት ውስተ ተፋቅሮትነ፤ ፍጹም ፍቅር ፍርኃትን አውጥቶ ይጥላል" ተብሎ እንደ ተጻፈ (ማቴ. ፳፯፥፶፰፤ ፩ኛዮሐ. ፬፥፲፰)፡፡

                                
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

#ድምፀ_ተዋህዶ

✨✨✨✨✨✨
✝️#ድምፀ_ተዋህዶ✝️
✨✨✨✨✨✨




'https://t.me/addlist/2CQ3e4ZJYT9hZGNk' rel='nofollow'>♥️🌹ጋብቻ ምን ማለት ነው⁉️🌹
ጋብቻ እና የዘር ሐረግ ምን ያገናኛቸዋል⁉️
ጋብቻ የሚፈቀደው ከስንት ዓመት ጀምሮ ነው⁉️
ሴት ሙሽራ ከወንድ ሙሽራ ቀኝ ለምን ትሆናለች⁉️
🌹ሙሽሮች በጫጉላ ጊዜያቸው ለምን አይጾሙም⁉️
ያገባሁት ሰው ካልተመቸኝ ብፈታው ምን ችግር አለው⁉️
እንደምንጋባ እርግጠኛ ከሆንን ግብረስጋ ግንኙነት ብንፈጽም ምን ችግር አለው⁉️


ጾም የተቀደሰ የእግዚአብሔር መንገድ መጀመሪያ ነው እና የመልካም ምግባራት አጋር ነው። ጾም በመንፈሳዊ ጦርነቱ መጀመሪያ ላይ በጎነትን ይመራል እና ንፅህናን ይጠብቃል። ጾም የጸሎት አባት፣ የመረጋጋት ምንጭ፣ የዝምታ አስተማሪ፣ የአዕምሮ ብርሃን ነው። የአንደበት ጾም ከአፍ ጾም ይሻላል፣ የልብም ጾም ከሁለቱም ይበልጣል። ከኃጢአትና ከምኞቱ ጋር የሚደረግ ትግል ሁሉ መጀመሪያ በጾም መጀመር አለበት። ልክ እንደ ጋለሞታ ስለ ንጽህና እንደምትናገር ወይም ሰውነታቸውን ሲወድ መንፈሳዊ ጉዳዮችን ሲፈልግ ነው።


[ቅዱስ ይስሐቅ ሶርያዊ]
መልካም የጾም ሳምንት ይኹንላችሁ!


🙏ኦርቶዶክሳዊ ዝማሬ🙏 dan repost
❓በዐብይ ጾም ፫ኛ ሳምንት ስያሜ ምን ይባላል❓
So‘rovnoma
  •   ደብረዘይት
  •   ምኩራብ
  •   ኒቆዲሞስ
  •   መፃጉ
3403 ta ovoz


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የጥቃት ዒላማ ያደረጉ የጥላቻ ንግግሮች እንዲቆሙ ምእመናን ጠየቁ !
መጋቢት  ፩/፳፻፲፯ ዓ/ም
በተለያዩ የማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮች የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ዒላማ ያደረጉ የጥላቻ ንግግሮች እና መልእክቶች በአፋጣኝ እንዲቆሙ እና መንግስትም ሕጋዊ እርምጃ እንዲወስድ ቲኤምሲ ያነጋገራቸው ምእመናን ገልጸዋል።

ማናቸውም ቤተ እምነቶች መብቶቻቸው እንዲከበር እንደሚፈልጉትና የሃይማኖታቸውን አስተምህሮ በነጻነት ማስተላለፍ ሕገ መንግስታዊ መብታቸው እንደሆነ የጠቆሙት አስተያየት ሰጪ ምእመናኑ በተመሳሳይም ሁሉም ቤተ እምነቶች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንን እምነት እና አስተምህሮ ባከበረ መልኩ ሊንቀሳቀሱ እንደሚገባ ገልጸዋል።

ሁሉም ኢትዮጵያውያን የሃይማኖት ነጻነታቸውን ተጠቅመው በማናቸውም መልኩ ሃይማኖታቸውን ማራመድ ሕገ መኖግስታዊ መብታቸው ቢሆንም የሌላውን እምነት ማንቋሸሽ፣ ማኮሰስ እና ማጥላላት ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለው እና ግጭት ቀስቃሽና ጸረ ሰላም እንቅስቃሴ መሆኑ ነው የተገለጸው።

ባለፉት ጊዜያት ከአንዳንድ ቤተ እምነት ተከታዮች ስለ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፣ ስለ ቅዱሳን፣ ስለ ንዋያተ ቅድሳት ብሎም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት በምታስተምቸው ትምህርቶች ላይ ትኩረት ያደረጉ የጥላቻ ንግግሮች ሲተላለፉ መቆየታቸው የሚታወስ ነው

በተለይም መዋቅራዊ ድጋፍ እየተሰጠው በሚመስል መልኩ የጥላቻ ንግግሮች ተባብሰው መቀጠላቸው እና ይኸው ጥላቻም በኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ ብቻ ሳይሆን በሜንስትሪም እና በመጽሐፍትም ጭምር ሲካሄድ መቆየቱ እና እየተካሄደ መሆኑ በርካታ ምእመናንን ያሳዘነና ያስቆጣ መሆኑ ተመላክቶአል።

መንግስት እነዚህን የጥላቻ አራማጆች እና ጸረ ሃይማኖት ግለሰቦችን በሕግ አግባብ እንዲጠይቅም ምእመናን ጥሪ አቅርበዋል


ምጽዋት የፊት መብራት ናት፡፡ አንድ ሰው በጨለማ ሲጓዝ ከኋላው መብራት ቢያበሩለትም እንኳ ከፊቱ የሚቀድመው የገዛ የአካሉ ጥላ እንቅፋት እየሆነበት ይጥለዋል፡፡ ወደ ፊት ያለውን መንገድ አጥርቶ እያየ ያለ ስጋት ለመሄድ እንዲችል የግድ የፊት መብራት ያስፈልገዋል፡፡ ጾም፣ ጸሎት እና ሌሎች መንፈሳዊ ትሩፋት እንደ ኋላ መብራት ናቸው፡፡ የፊት መብራት የተሰኘች ምጽዋት ካልታከለችባቸው እነዚህ ብቻቸውን ዋጋን አያሰጡንም፡፡ ከምጽዋት በላይ ታላቅ ነገር እንደሌለ ልንረዳ ይገባል፡፡"*

*ኢትዮጵያዊው አፈወርቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ*


“ለድሃው ልብሶቹ ቢያድፉበት በውሃ እጠብለት አዲስም ልብስ ገዝተህ አልብሰው፤ ደሃው ወደ ቤትህ የገባ እንደሆነ እግዚአብሔር ወደቤትህ ይገባል፤ በመኖሪያህም ያድራል፡፡ ከመከራ ከስቃይ ላላቀቅኅው ለዚያ ድሃ እግዚአብሔርም አንተን ከሚመጣብህ መከራና ስቃይ ያላቅቅሃል፡፡

የእንግዳውን እግር አጠብክን? የበዛ ሃጢአትህን አጥበህ አስወገድከው፡፡ ለድሃው ይመገብ ዘንድ ማዕድን አቀረብክለትን? እነሆ እግዚአብሔር አብ ከማዕድህ በላ፤ ክርስቶስም ለደሃው ካቀረብክለት ውሃ ጠጥቶ ረካ፤ መንፈስ ቅዱስም ማደሪያ ቤቱ አደረገህ፡፡

ደሃው ባቀረብክለት ማዕድ በልቶና ጠጥቶ ደስ አለውን? ጌታ ክርስቶስን ደስ አሰኘኅው፤ እርሱ ያደረክለትን መልካም ችሮታ የሚረሳ አይደለምና በመላእክትና በሰወች ፊት ያከብርሃል፡፡ ከረሃቡ እንዳሳረፍከው በመጨረሻው ቀን ይመሰክርልሃል፡ ለጥማቱ የሚጠጣ ስላቀረብክለት በመላእክቱ ፊት ያመሰግንሃል፡፡

ልጄ ሆይ መልካም ዘርን በደስታና እግዚአብሔርን ተስፋ በማድረግ ዝራ ልፋትህም ፍሬ ይስጥህ”

(ከስብከት ወተግሳፅ ዘቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ መጽሐፍ የተወሰደ)




አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
መጋቢት 2-የኒቅዮስ ኤጲስቆጶስ አባ መከራዊ በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡
+ ከሮሀ አገር የተገኘውና የተሠወረውን ሁሉ የሚያይ የጻድቃንን ማደሪያና የኃጥአንንም ኩኔን በገሃድ የተመለከተ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዕረፍቱ ነው፡፡

ሰማዕቱ አባ መከራዊ፡- ይኽም ቅዱስ ከደቡባዊ ግብጽ ከእስሙናይን የተገኘ ነው፡፡ የኒቅዮስ አገር ኤጲስቆጶስ ሆኖ በተሾመ ጊዜ በክርስቲያኖች ላይ ታለቅ ስደትና መከራ ሆነ፡፡ አረማዊ መኮንን ወደዚያች አገር ገብቶ ብዙዎቸን በሰማዕትነት ገደለ፡፡ አባ መከራዊንም ጭፍሮቹን ልኮ ካስመጣቸው በኋላ እምነቱን እንዲክድ አስገደደው፡፡ አባ መከራዊ ግን በእምነቱ ስለጸና በጽኑ ግርፋት አስገረፈው፡፡ ዳግመኛም ብርና እርሳሰ አቅልጠው በአፉ ውስጥ እንዲጨምሩበት አዘዘ፡፡ እንደታዘዘውም ባደረጉ ጊዜ ጌታችን አባ መከራዊን አጸናውና ምንም ጉዳት እንዳላገኘው ሆነ፡፡ 

ከዚህም በኋላ ይህ ከሃዲ መኮንን አባ መከራዊን ወደ እስክንድርያው ገዥ ወደ ኄርሜኔዎስ ላከው፡፡ እርሱም አሠረው፡፡ አባ መከራዊም በእሥር ላይ እንዳለ ብዙ ተአምራትን አደረገ፡፡ የአቅፋስ ከተማ ሹም የሆነውን ልጅ እጅና እግሩ ሽባ ነበርና አባ መከራዊ በጸሎቱ ፈወሰው፡፡ እስክንድርያው ገዥ ወደ ኄርሜኔዎስም ይህንን ሲሰማ በአባ መከራዊ ላይ ሥቃይ አበዛበት፡፡ ሕዋሳቶቹ ሁሉ እስኪቆራረጡ ድረስ በመንኮራኩር ውስጥ ጨምሮ አሠቃየው፡፡ ዳግመኛም ለተራቡ አንበሶች ሰጡት፣ በባሕር ውስጥ አሰጠሙት፣ በእሳት ምድጃ ወስጥ ጨመሩት ነገር ግን በእነዚህ መከራዎች ሁሉ ጌታችን ፈጽሞ ያድነው ነበር፡፡

በመጨረሻም መኮንኑ ማሠቃየት በሰለቸው ጊዜ አንገቱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ፡፡ አባ መከራዊም በዛሬዋ ዕለት አንገታቸውን ተሰይፈው ሰማዕትነታቸው በድል ፈጸሙ፡፡ ቅዱስ ሥጋቸውንም በመርከብ አድርገው ወደ አገራቸው ሲወስዱ እግዚአብሔር ያርፍ ዘንድ የወደደበት አገር ላይ ሲደርስ መርከቧ አልንቀሳቀስ አለች፡፡ ከአባ መከራዊም ሥጋ ‹‹ሥጋዬ በውስጡ እንዲኖር እግዚአብሔር የፈቀደው ቦታ ይህ ነው›› የሚል ቃል ወጣ፡፡ ይህንንም ለዚያች አገር ሰዎች በነገሯቸው ጊዜ በዝማሬ በእልልታ ቅዱስ ሥጋቸውን ተቀብለው ወስደው በመልካም ቦታ አስቀመጡት፡፡ የአባ መከራዊ መላ ዘመናቸው 131 ዓመት ነው፡፡ 

ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን!!!    
+ + +     

አቡነ ጎርጎርዮስ ረዓዬ ኅቡዓት፡- ይኽም ቅዱስ በሌላኛው ስሙ ጎርጎርዮስ ዘሀገረ ሮሐ እየተባለ ይጠራል፡፡ ረዓዬ ኅቡዓት ማለት ምስጢራትን የተመለከተ ማለት ነው፡፡ ይህም ጻድቅና ሊቅ በቅዳሴው፣ በሃይማኖተ አበው፣ በስንክሳር፣ በገድለ ሰማዕታትና በገድለ ቅዱሳን ስሙ ተደጋግሞ ተጠቅሷል፡፡ በመጀመሪያ የክርስቲያኖች ጠላት የነበረ ሲሆን ዐመጸኛና ኃጥእ ነበረ፡፡

ክርስቲያኖችንም እየፈለገ ያሠቃይና ይገድል ነበር፡፡ አንድ ቀን ድንገት ሳያስበው መልአክ መጥቶ ነጥቆ ወስዶ የኃጥአንንም የመከራ ቦታዎችንና ሲኦልን አሳይቶ መልሶ አምጥቶ መሬት ላይ ሲጥለው እጅግ ደንግጦ በፍጹም ንስሓ ተመልሶ ሐዲሳትንና ብሉያትን ጠንቅቆ በመማር በብዙ ተጋድሎ መኖር ጀመረ፡፡ 
በሌላ ጊዜ አሁንም መልአኩ በረድኤት ተገልጦለት ነጥቆ ወስዶ ገነትን፣ ብሔረ ሕያዋንን፣ ብሔረ ብዑዓንን፣ መንግሥተ ሰማያን ሁሉ አሳየው፡፡ ከዚህም በኋላ ከአመፁ ወደ እግዚአብሔር በንስሓ ተመልሶ መነኮሰ፡፡ በምንኩስናም ሆኖ በብዙ ተጋድሎ ኖረ፡፡ ከዚህም በኋላ የተሰወረውን ሁሉ የሚያይ ቅዱስ አባት ሆነ፡፡ በሊቀ ጳጳስነት ተሾሞ በማገልገል ብዙ ጣዖታትን አፈራርሶ አብያተ ክርስቲያናትን ሠራ፡፡ በመጨረሻም ሹመቱን በመተው በዓቱን አጽንቶ ብዙ ከተጋደለ በኋላ መጋቢት 2 ቀን በክብር ዐርፏል፡፡

የአቡነ ጎርጎርዮስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!!!


ጠያቂው ተጠየቅ እንጂ…!

"…ክርስቶስ ማነው…? በሚል 303 ጥያቄዎች አሉኝ ብሎ እሱ በማያምንበት ለእኔ ግን ጌታዬ አምላኬና መድኃኒቴ በሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ጥያቄ አቅርቧል። በመጽሐፍ መልክም አሳትሟል። መልካም መብቱ ነው። አሕመዲን ጀበል በጌታ ላይ ተሳልቋል፣ በምስጢረ ሥላሴ ላይ አሹፏል፣ ቀልዷል ብለን ሰልፍ አልወጣንም። ይገደልም አላልንም።

"…አሕመዲን ጀበል በኢየሱስ ክርስቶስ ስለማያምን የፈለገውን የመጻፍ መብት አለው ከተባለ እፎይም ሆነ እኔ ስለማላምንበት ስለ መሀመድ ብጽፍ ለምን ትናደዳለህ? አንተ የእኔን በመናቅህ ዝም እንዳልኩህ እኔም የአንተን ስንቅ ዝም ማለት ነው እኮ ያለብህ። አንተ የእኔን ድንበር አልፈህ ለማዋረድ ስትሞክር እኔ በድንበሬ ላይ ቆሜ የአንተን ባዋርድ ለምንድነው ጎረቤት ሁላ እስኪረበሽ የምትንጫጫው። አንተ "ለነቢይህ" ፍቅር፣ አክብሮት፣ ውዴታ አለኝ ካልክ እኔ ለአምላኬና ለመድኃኒቴ ለኢየሱስ ክርስቶስ ምንም ዓይነት ፍቅር፣ መስዋዕትነት የማልከፍል ይመስልሃል?

"…ንጽጽር ብለህ ያለ አቅምህ መጽሐፍ ቅዱስ ትንተና የጀመርከው አንተው ራስህ ነህ። አንተ የማታውቀውን መጽሐፍ ቅዱስ ገልጠህ ስትዳክር ዝም ብለን ቆይተን፣ መልስም ከዚያው ከመጽሐፍ ቅዱስ ስንሰጥህ ከርመን፣ አይ ቆይ እስኪ ለምን ደግሞ ከቁርዓኑና ከሐዲሱ መልስ አንጠይቃቸውም ብለን ስንነሣ ቆንጨራ ይዞ መፎከር ምን የሚሉት ነው? ወይ አስቀድሞ አለመፎከር፣ አቅምን ዐውቆ መኖርም ጥሩ ነው። ግጠመኝ ካልክ በኋላ አንተ በእኔ መጽሐፍ ቅዱስ ልትሞግተኝ ስትመጣ፣ እኔ ደግሞ በአንተው ቁርዓን ልሞግትህ ስነሣ የምን መነጫነጭ ነው?

"…በመስታወት ቤት የሚኖር ሰው የድንጋይ ውርወራ ጠብ ውስጥ ፈጽሞ አይገባም። ባለጊዜ ነን ተብሎ እንደ ሕጻን በልቅሶ፣ በጩኸት ፍላጎትን ለማሳካት መሯሯጥ ያስገምታል።

• እፎይ…!




ስግር፣ ስበላ፣ ስጠጣ፣ ስቀማ፣ ስሰርቅ ነበርሁ እንጂ፣ ሃይማኖት አልተማርሁ፣ ምግባር አልሠራሁ፣ ሰንበትን አላከበርሁ›› ብላ ትመልስለታለች፡፡ ከዚህም በኋላ መላእክተ ብርሃንን ጠርቶ ‹‹ይህቺ ነፍስ አሕዛብ (ያላመነች ያልተጠመቀች) ናትና ኩነኔ እንጂ መንግሥተ ሰማያት አይገባትም፤ ከሥጋዋ ጋር አዋሕጄ ፍጹም ገሃነመ እሳት እስካገባት ድረስ 4 ቀን መንግሥተ ሰማያትን፣ 3 ቀን ገሃነመ እሳትን አዙራችሁ አሳይታችሁ ከኃጥአን ጋራ በሲኦል በርባሮስ አኑሯት›› ይላቸዋል፡፡ መላእክተ ብርሃንም ይዘዋት ወጥተው 4 ቀን መንግሥተ ሰማያትን የባለ ሕጎችን፣ የደናግሎችን ሀገር፣ የመነኮሳቱን ሀገር፣ ማርና ወተት የምታፈስ የተባለችውን አዙረው አሳይው ሽታዋን ጣዕሟን በልቧ አስርፀው፣ አቅምሰው ‹‹አንቺ ነፍስ ሃይማኖት ብትማሪ፣ ምግባር ብትሠሪ ቦታሽ ይህ ነበር…›› ብለው ይዘዋት ወርደው ገሃነመ እሳትን 3 ቀን የእሳቱን ሰንሰለት፣ የእሳቱን አክሊል፣ የእሳቱን ጨለማ፣ የእሳቱን ቁርበት፣ የእሳቱን ዘንዶ፣ የእሳቱን ዝናር፣ የእሳቱን ጫማ፣ ክርፋቱን ግማቱን፣ አዙረው አሳይተው ‹‹አንቺ ነፍስ በእንዲህ ያለ ቦታ ትሉ ከማያንቀላፋ፣ እሳቱ ከማይጠፋ ለዘላለም በዚህ ያኖርሻል›› ብለው ወደ በርባሮስ ይዘዋት ይሔዳሉ፡፡ ከዚህም በኋላ ከሰኦል ደጅ አድርሰው ለአጋንንት ያስረክቧታል፡፡ አጋንንትም ከጨለማው አግብተው በእሳት ጦር እየወጉ፣ በእሳት አለንጋ እየገረፉ፣ በእሳት መንዶ እየቀጠቀጡ ይወስዷታል፡፡ እርሷም መከራው ሲጸናባት ‹‹ወየው! ወየው!…የእግዝእትነ ማርያም ያለህ!›› ትላለች፡፡ ትማፀናለች፡፡ እመቤታችንም ለሁሉ አማላጅ ናትና መጥታ ‹‹ልጄ ወዳጄ ሆይ! ማርልኝ›› ትለዋለች፡፡ ጌታም ‹‹ይህች ነፍስ እኔንም አንቺንም የበደለች ከሃዲ ናትና አልራራላትም›› ይላታል፡፡ እመቤታችንም ‹‹ምሕረት ልማድህ ነውና ማርልኝ›› ብላ ትሰግዳለች፡፡ ጌታም ‹‹ስለ እናቴ ጥቂት አሳርፏት›› ይላቸዋል፡፡
ዛሬ በዚህ ዓለም አንድ ሰው በቆላ ሲሔድ ከላይ ፀሐዩ፣ ከታች ረመጫቱ (የመሬቱ ግለት) ሲፈጀው ላብ ላብ ሲለው ጥቂት ጥላ ያገኘ እንደሆነ እርፍ ብሎ እንደሚነሣ ሁሉ አጋንንትም ያችን ነፍስ ጥቂት አሳርፈው እንደገና መከራዋን ሲያሳዩአት ይኖራሉ፡፡ እርሷም ከመንግሥተ ሰማያት መውጧን ገሃነመ እሳት መውረዷን እያሰበች ፀፀት እንደ እሳት ሲፈጃት ሲያቃጥላት እስከ ዕለተ ምጽዓት ድረስ በሲኦል ትቀመጣለች፡፡ የኃጥእ ሰው ነፍስ ሥቃይዋ ይህን የመሰለ ነው፡፡ እግዚአብሔር ከዚህ መከራ ሁላችንንም ያድነን! አሜን!!!
ማጠቃለያ፡- በዓለም ላይ ያለ ማንም ኃጥእ ሰው ንጉሥ ይሁን ሎሌ፣ የተማረ ምሑር ይሁን ያልተማረ ጨዋ፣ ሀብታም ይሁን ድሀ ማንኛውም ሰው በእውነተኛዋ ሃይማኖት ያላመነ ምግባር የሌለው ከሆነ በስተመጨረሻ በሞት አፋፍ ላይ ሳለ እጅግ እፈሪውን መልአከ ሞትን በገሃድ በተመለከተ ጊዜ እንደንጉሥ አጋግ ‹‹ከመዝኑ ሞት መሪር-በውኑ ሞት እንደዚህ መራራ ነውን?›› ማለቱ አይቀርም፡፡ ሃይማኖት ላልተማሩ ምግባር ላልሠሩ ለኃጥአንና ለክፉዎች ሞት እጅጉን መራራ ነው፡፡ ይልቁንም ሁለተኛው ሞት በገሃነም ያለው ነው፡፡ በእግዚአብሔር ዳኝነት ወደ እሳት ባሕር ይጣላሉ፣ ሥቃያቸውም አያልቅም፡፡ ራእ 14፡11፣ 20፡13፡፡ ጌታችንም በቅዱስ ቃሉ ‹‹ትሉ ወደማያንቀላፋበት እሳቱ ወደማይጠፋበት›› የሚገቡ እንዳሉ አስተምሯል፡፡ ማር 9፡44-48፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ‹‹እግዚአብሔርን የማያውቁትን፣ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስንም ወንጌል የማይሰሙትን ይበቀላቸዋል፤ ከጌታችን ፊት ከኃይሉም ክብር ርቀው በዘለዓለም ጥፋት ፍዳቸውን ያገኛሉ›› ብሏል፡፡ 1ኛ ተሰ 1፡9፡፡ ከነቢያትም ነቢዩ ኤርምያስ ‹‹እግዚአብሔር ግን እንደ ኃያል ተዋጊ ከእኔ ጋር ነው፣ ስለዚህ አሳዶቼ ይሰናከላሉ፣ ለዘለዓለምም የማይረሳ ጉስቍልናቸውን አላወቁምና ፈጽመው አፈሩ›› በማለት ተናግሯል፡፡ ኤር 20፡11፡፡ ነቢዩ ዳንኤልም ‹‹በምድርም ትቢያ ውስጥ ከአንቀላፉት ብዙዎች እኵሌቶቹ ለዘለዓለም ሕይወት፣ እኵሌቶቹም ለእፍረትና ለዘለዓለም ጉስቍልና ይነሣሉ›› ብሏል፡፡ ዳን 12፡2፡፡
እንግዲህ የነፍስና የሥጋ መለያየት እንደ አጋግ የመረረን ወይም የሚመርረን ሰዎች ሁለተኛው ሞት ሲመጣ ‹‹እንዴት ልንሆን ነው?›› ማለት ይገባል፡፡ ከዚህም ተነሥተን የመጀመሪያውንም የሁለተኛውንም ሞት መራራ የሚያደርገው ሃይማኖትን ከምግባር አስተባብረን አለመያዛችንና ክፋታችን መሆኑን አውቀን ሃይማኖት ተምረን ምግባር ሠርተን ከክፋት ወደ በጎነት መመለስ ይኖርብናል፡፡ ያን ጊዜ ሞታችን እንቅልፍ ወይም እረፍት ይሆንልናል፡፡ 1ኛ ነገ 2፡10፣ ሐዋ 7፡60፣ ራእ 14፡13፡፡
በክርስቶስ ሞት የተሻረ ሞት በእኛ በእውነተኞቹ በክርስቶስ ተከታዮቹ ላይ ሥልጣን አይኖረውም፡፡ 1ኛ ቆሮ 15፡53-57፣ 2ኛጢሞ 1፡10፣ ዕብ 2፡9፣ 14፡15፣ ራእ 18፡፡ ሞት ከክርስቶስ ጋር ለዘለዓለም የሚያኖረን መንገድ ይሆንልናል፡፡ ኢሳ 35፡10፣ 45፡17፣ ዳን 7፡14፣ 12፡2፣ ሉቃ 23፡43፣ ዮሐ 5፡24፣ 1ኛ ተሰ 4፡13፡፡ እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹እኔስ ከዚህ ዓለም ልለይ በክርስቶስም ዘንድ ልኖር እወዳለሁ፤ ይልቁንም ለእኔ ይህ ይሻለኛል፣ ይበልጥብኛልም›› እንላለን፡፡ ፊል 1፡23፡፡ እንደ ቅዱስ ጴጥሮስም ‹‹እግዚአብሔር የሚመጣበትን፣ ሰማያትም ቀልጠው የሚጠፉበትን፣ ፍጥረትም ሁሉ ተቃጥሎ የሚጠፋባትን ዕለት በተስፋ እየጠበቃችሁ ፍጠኑ፤ እኛ ግን ጽድቅ የሚኖርባቸውን አዲሶቹን ሰማያትና አዲሲቱን ምድር ተስፋ እናደርጋለን›› እያልን በተስፋ መንግሥተ ሰማያት እንኖራለን፡፡ 2ኛ ጴጥ 3፡12፡፡ እንደ ቅዱስ ዮሐንስ ‹‹ዓለሙንና በዓለም ያለውን አትውደዱ፤ ዓለሙን የሚወድ ግን የአብ ፍቅር በእርሱ የለም፡፡ በዓለም ያለው ሁሉ እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት፣ ስለ ገንዘብም መመካት ከዓለም እንጂ ከአብ አይደለም፡፡ ዓለሙ ያልፋል፣ ምኞቱም ያልፈል፣ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ሰው ግን ለዘለዓለም ይኖራል›› በማለት በሕይወት እንተረጉመዋለን፡፡ 1ኛ ዮሐ 2፡15-17፡፡
የእግዚአብሔር ቸርነት የድንግል ማርያም አማላጅነት አይለየን! አሜን!!!


ወጥታ በአስክሬኑ ላይ ትቀመጣለች፡፡ በዚህ ጊዜ መልአከ ሞት በጥፍሩ ወግቶ ቆንጥሮ በጥርሱ ቆርጥሞ አላምጦ 3 ጊዜ ይተፋታል፡፡ 3 ጊዜ መትፋቱ ስለምን ነው? ቢሉ ‹‹አንቺ ነፍስ በአርአያ ሥላሴ የተፈጠርሽው የሥላሴን አንድነት ሦስትነት አውቀሽ፣ ሃይማኖት ተምረሽ፣ ምግባር ሠርተሽ፣ ሰንበት አክብረሽ፣ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን በንጽሕና ተቀብለሽ፣ በሕግ በሥርዓት ሆነሽ ልትኖሪ ነበር፡፡ ይህን አላወቅሽም፣ አላደረግሽም ዐመፀኛ ነሽ…›› ሲል 3 ጊዜ እየቆረጣጠመ ይተፋታል፡፡ ‹‹ከመዝኑ ሞት መሪር-በውኑ ሞት እንደዚህ መራራ ነውን?›› እንዳለ ንጉሥ አጋግ፡፡ 1ኛ ሳሙ 15፡32፡፡
ዳግመኛም እኩሉ አጋንንት በሰማይ እኩሉ በምድር ሆነው 13 ጊዜ ወደ ሰማይ፣ 13 ጊዜ ደግሞ ወደ ምድር እያንቀረቀቡ ከምድር ላይ ያፈርጧታል፡፡ ስለምን 13 ጊዜ ወደ ሰማይ እያጓኑ ይጫወቱባታል? ቢሉ ‹‹አንቺ ነፍስ ጌታሽ አምላክሽ በዕለተ ዐርብ 13ቱን ሕማማተ መስቀል የተቀበለልሽ ለአንቺ መድኃኒት፣ ለአርአያ፣ ለቤዛ ነበር፡፡ አንቺ ግን ይህን አውቀሽ ሃይማኖት ተምረሽ፣ ምግባር ሠርተሽ፣ ሰንበትን አክብረሽ አልኖርሽም፤ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን በንጽሕና አልተቀበልሽም፤ ሕጉን ትእዛዙን አልጠበቅሽም፤ ዐመፀኛ ነሽ›› ብለው ስለዚህ 13 ጊዜ ወደ ሰማይ እያጓኑ፣ ከምድር ላይ እያፈረጡ ይጫወቱባታል፡፡ ዳግመኛም የፊጥኝ የግርግሪት የኋሊት አሥረው፣ በእሳት ልጓም ለጉመው፣ በእሳት ሰንሰለት አሥረው፣ አንቀው ይዘው በእሳት በሎታ ራስ ራሷን እየቀጠቀጡ ያስለፈልፏታል፤ ያስጨንቋታል፡፡ እርሷም በዚህ ታላቅ ጭንቅና መከራ ውስጥ ሆና ‹‹…ወዮ የሥላሴ ያለህ!›› ትላለች፤ ታማፅናለች፡፡ መላእክተ ጽልመትም ‹‹ከእኛ ዘንድ ስትመጪ ነው ሥላሴን የምታውቂያቸው? ከዚያ ሳለሽ ስለሥላሴ ብለሽ ሃይማኖት በተማርሽ፣ ምግባር በሠራሽ፣ ሰንበትን ባከበርሽ፣ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን በንጽሕና በተቀበልሽ፣ በሕግ በሥርዓት ሆነሽ በኖርሽ ነበር እንጂ…›› እያሉ ‹‹..በሏት ጨርሷት ቀጥቅጧት›› እየተባባሉ ያሠቃዩአታል፡፡ ዳግመኛም ‹‹…ወዮ ወዮ የመድኃኔዓለም ያለህ!›› እያለች ታማፅናለች፡፡ መላእክተ ጽልመትም ‹‹ከእኛ ዘንድ ስትመጪ ነው መድኃኔዓለምን የምታውቂው? ከዚያ ሳለሽ ስለመድኃኔዓለም ብለሽ ሃይማኖት በተማርሽ፣ ምግባር በሠራሽ፣ የታረዘ ባለበስሽ፣ በመጸውትሽ፣ ቤተ ክርስቲያን ስመሽ በኖርሽ፣ ሰንበትን ባከበርሽ፣ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን በንጽሕና በተቀበልሽ፣ በሕግ በሥርዓት ሆነሽ በኖርሽ ነበር፡፡ መድኃኔዓለምማ በመስቀል ተሰቅሎ፣ ሥጋውን ቆርሶ ደሙነ አፍስሶ የሰጠሸ ለአንቺ መድኃኒት አልነበረምን? ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን በንጽሕና አልቀበልም ብለሽ፣ ሰንበትን አላከብርም ብለሽ፣ ዐርብና ረቡዕን አልጾምም ብለሽ፣ ንስሓ አልገባም ብለሽ ነው እንጂ፡፡ ደግሞ በምድር ላይ ሳለሽ ነው እንጂ መጠንቀቅ…›› እያሉ ‹‹..በሏት ጨርሷት ቀጥቅጧት›› እየተባባሉ ስቃዩአን ያበዙታል፡፡
ያቺ ጉስቋላ ነፍስ ዳግመኛም ‹‹…ወዮ ወዮ የእግዝእትነ ማርያም ያለህ!›› እያለች ታማፅናለች፡፡ መላእክተ ጽልመትም ‹‹ከእኛ ዘንድ ስትመጪ ነው እግዝእትነ ማርያምን ያወቅሻት? ከዚያው ሳለሽ ነበር እንጂ ዝክሯን ማዘከር፣ በዓሏን ማክበር፣ ለተራበ ማብላት፣ ሕጉን ትእዛዙን አጽንቶ መኖር…›› እያሉ ‹‹..በሏት ጨምሩላት›› እየተባባሉ ስቃዩአን ያበዙታል፡፡ ከዚኽም በኋላ የፊተኞቹ እየጎተቱ የኋለኞቹ እያስጨነቁ ይዘዋት ይሔዳሉ፡፡
ከዚኽም በኋላ መላእክተ ብርሃን የጌታን ቃል ሳይሰሙ አይለቋትምና ራስ ራሷን እያዩ ይከታተሏታል፤ እንዲህ ሲከታተሉ ከባሕረ እሳት ይደርሳሉ፡፡ ከዚያም መላእክተ ጽልመት 3 ጊዜ ራሷን ቀጥቅጠው ባሕረ እሳቱን ‹‹ሂጂ ግቢ ተሻገሪው›› ይሏታል፡፡ እርሷም ‹‹ምን ጨብጬ፣ በምንስ ላይ ቆሜ ልሻገረው? ቀኙ እሳት፣ ግራው ውኃ፣ ውስጡ ገደል ነው፣ መንገዱም እንደጭራ የቀጠነ ነውና ምን ረግጬ በምን ላይ ቆሜ ልሻገረው?›› ትላለች፡፡ መላእክተ ጽልመትም ‹‹ለዚህማ መሻገሪያው ታንኳው ለተራበ ማብላት፣ ለተጠማ ማጠጣት፣ ለተቸገረ መርዳት፣ ሰንበትን ማክበር፣ አሥራት በኩራት ማውጣት፣ አንድ በዓል መዘከር፣ ጾም፣ ጸሎት፣ ትሕትና፣ ፍቅር፣ ትዕግሥት፣ ቁጡ አለመሆን፣ ቂም አለመያዝ ነበር፡፡ ዛሬ ከዚህ ደርሰሽ ‹ምን ጨብጬ በምን ላይ ቆሜ ብትይ› ይሆናልን?›› ይሏታል፡፡ እርሷም መልሳ ‹‹ይህስ እንዳለ ባውቅ ኖሮ ስንኳን ሃይማኖት መማር፣ ሰንበትን ማክበር፣ ሀብትን መስጠት ይቅርና እጄን እግሬን ቆርጬ በሰጠሁ ነበር! ብሰማም ዋዛ ፈዛዛ ይመስለኝ ነበር እንጂ›› ትላቸዋለች፡፡ መላእክተ ጽልመትም ‹‹ከእንግዲህ ወዲህ ተመልሰሽ ትሔጃለሽን? ሂጂ ግቢ አሁን ላይ ፀፀት አይረባሽም›› ብለው እነዚያ ክፉውን ሁሉ ሲያስተምሯት የነበሩት ወርውረው ከባሕረ እሳቱ ውስጥ ይጨምሯታል፡፡ እርሷም ከእሳቱ ወጥታ ከባሕሩ፣ ከባሕሩ ወጥታ ከእሳቱ…እያለች አርራ ከስላ ከእሳት እንደገባ ጅማት ተኮማትራ ትሻገራለች፡፡
ዳግመኛም ወዲያ ማዶ ያሉት ‹‹አንቺ ክፉ ምን ያባክንሻል? መንገዱ ይህ አይደለምን!? ፀጥ ብለሽ በመንገዱ አትሻገሪምን!?›› ብለው እየዘበቱባት መልሰው ከባሕረ እሳቱ ውስጥ ይደፏታል፡፡ እርሷም ከእሳቱ ወጥታ ከባሕሩ እያለች አርራ ከስላ እንደቁራ ጠቁራ ትሻገራለች፡፡
ሦስተኛም ወዲህ ማዶ ያሉት ‹‹አንቺ ክፉ ምን ያባክንሻል? መንገዱ ይህ አይደለምን!? ፀጥ ብለሽ በመንገዱ አትሻገሪም!?›› ብለው እየዘበቱባት ወርውረው ይደፏታል፡፡ እርሷም ከእሳቱ ገብታ ከባሕሩ እያለች አርራ ከስላ ትሻገረዋለች፡፡ ዳግመኛም ‹‹ይህንን ሁሉ ሲነግሩኝ ሐሰት ይመስለኝ ነበር›› ብላ እየተጨነቀች ትሻገረዋለች፡፡ ከዚህም በኋላ መከራዋን ስትፈጅ መላእክተ ብርሃን ተቀብለው ይዘዋት ይሔዳሉ፡፡ እርሷም ‹‹ወየው! ከጌታዬ ስደርስ እንዴት እሆን ይሆን…!?›› እያለች ትሔዳለች፡፡ ትሔድም ዛሬ በዚህ ዓለም ያለ ሰው ከንጉሥ አምፆ ተጣልቶ፣ ነፍስ ገድሎ፣ ተይዞ ሊገረፍ፣ ሊቆረጥ፣ ሊፈለጥ፣ ሊሞት እየተጨነቀ እያለቀሰ እንዲሔድ ያችም ጎስቋላ ነፍስ እንደዚያ እየተጨነቀች ትሔዳለች፡፡ ዳግመኛም በዚህ ዓለም ያለ ንጉሥ የሚፈልጥ የሚቆርጥ ሆኖ አስፍቶ ተቆጥቶ እንዲቆይ ሁሉ ፈጣሪዋም ተቆጥቶ ተገርሞ ይቆያታል፡፡ እርሷም በምድር ሳለች ያልተማረች ናትና ደርሳ ሰንግጣ ፈዛ ትቆማለች፡፡ ከዚህም በኋላ መልእክተ ብርሃን ‹‹አንቺ ክፉ፣ ኩሩ፣ ትዕቢተኛ፣ የወትሮው ኩራት አለ መስሎሻል? ፈጣሪሽኮ ነው! ስገጂ እንጂ!...›› ብለው ይገፏታል፡፡ እርሷም ሰግዳ ትቆማለች፡፡ ዕዝ 6፡9፡፡ ከዚህም በኋላ ጌታ ይጠይቃታል፡፡ ምን ብሎ ይጠይቃታል? ቢሉ የወንድ ነፍስ እንደሆነች ‹‹አንቺ ነፍስ እንጨት መቁረጥ፣ መፍለጥ፣ ቤት መሥራት፣ ፈረስ መጋለብ ውኃ ዋና፣ ሰንጠረዥ፣ እርሻ፣ ቁፋሮ፣ በገና፣ ጸናጽል፣ ከበሮ፣ ጽሕፈት፣ ድጉሰት ታውቂያለሽን?›› ብሎ አይጠይቃትም፡፡ የሴትም ነፍስ ብትሆን ‹‹አንቺ ነፍስ አልሞ መደቆስ፣ አለስልሶ መፍተል፣ መፍጨት፣ ወጥ መሥራት፣ እንጀራ መጋገር፣ ጠጅና ጠላ መጥመቅ ታውቂያለሽን?›› ብሎ አይጠይቃትም፡፡ እንግዲያስ ምን ብሎ ይጠይቃታል? ቢሉ ‹‹አንቺ ነፍስ በማን ታመልኪያለሽ? አንድነቴን ሦስትነቴን፣ ምልዐት ስፋቴን፣ ርቀቴን፣ ከሰማየ ሰማያት መውረዴን፣ ከድንግል ማርያም መወለዴን፣ ወልደ አብ በመለኮት፣ ወልደ ማርያም በትስብእት በተዋሕዶ የከበርኩ መሆኔን፣ መገፈፍ መገረፌን፣ መሰቀል መሞቴን፣ መነሣት ማረጌን ታውቂያለችን? ብሎ ይጠይቃታል፡፡ እርሷም ያልተማረች ናትና ‹‹አምላኬ ሆይ! አላውቅም›› ትላለች፡፡ ‹‹ለሥጋዬ ስጥር


ክርስቲያን አልሄድሁ፣ ሃይማኖት አልተማርሁ፣ ምግባርም አልሠራሁ፣ ሰንበትንም አላከበርሁ፣ የተራበ አላበላሁ፣ ለሥጋዬ ስጥር ስግር ስላፋ ስማስን ነበርሁ እንጂ፡፡ እንደ እናንተ ያለም መኖሩን አይቼ ሰምቼም አላውቅም›› ትላቸዋለች፡፡ ከዚህ በኋላ መላእክተ ብርሃን ‹‹ወይ ነፍስ! እንዴት ለደገኛው መንግሥተ ሰማያት ተፈጥረሽ ለገሃነመ እሳት ሆንሽ? በሥላሴ አምሳል ተፈጥረሽ የዲያብሎስ መረገጫ የሰይጣናት መራወጫ ሆንሽ!?›› ብለው አዝነው አልቅሰው ይሔዳሉ፡፡
(እዚህ ጋር አባታችን አባ ኪሮስ የጻድቅ ሰውና የኃጥእ ሰው ነፍስ ከሥጋ ስትለይ በጌታችን ፈቃድ በግልጽ እንደተመለከተ ከገድሉ አውጥተን እንነግራችሁ ዘንድ እንወዳለን፡- ‹‹ጌታችን ለአባ ኪሮስ ‹የነፍስን ከሥጋ መለየት ታይ ዘንድ ወደ አንዲት አገር ትሔድ ዘንድ አዝሃለሁ፣ ካየህም በኋላ ወደ በዓትህ ተመለስ› ብሎት ከእርሱ ተሰወረ፡፡ አባ ኪሮስም በአንደኛው ቀን ተነሥቶ ሲሔድ ከአንዲት ሀገር ደረሰ፡፡ በዚያም ፈጽማ የታመመች አንዲት ሴት አገኘና እርሷ ወዳለችበት ቤት ገባ፡፡ መላእክትን በአጠገቧ ሲመላለሱ ተመለከተ፡፡ በእጃቸው መሰንቆ የያዙ አሉ፣ የገነት አበባ የያዙም አሉ፣ ልብሰ መንግሥትም የያዙ አሉ፣ የጽድቅ ድባብም የያዙ አሉ፡፡ ሁሉም በአንድነት ‹ፈጽሞ ደስ ይበልሽ፣ ከመከራ ወደ እረፍት፣ ከችግር ወደ ብልጽግና ነይ!› ይሏታል፡፡ እንደግድግዳ ከበው ይህን ሲነጋገሩ ከመላእክት አንዱ ስሙ ገብርኤል የሚባል ወደእነርሱ መጣ፡፡ ‹በግድ እንለያት ዘንድ አላዘዘንምና ስለ እርሷ ምን ትላላችሁ! የገነትን አበባ አሽቷት እንጂ› አላቸው፡፡ እንዳዘዛቸውም አፈረጉ፡፡ ነፍስዋም በመዓዛ ገነት በተመስጦ ከሥጋዋ ተለየች፡፡ አባታችን አባ ኪሮስም መላእክትን ‹ነፍስ ከሥጋ ስትለይ እንዲህ ነውን?› አላቸው፡፡ መላእክትም ‹ኪሮስ ሆይ! እንዲህ አትበል፣ ይህ የምታየው ክብር ለጻድቃን ብቻ ነው፡፡ ለኃጥእ ሰው ግን መልአከ ሞት ከሠራዊቱ ጋር በሚያስፈራ ግርማ ይመጣባቸዋል፡፡ የእርሱንም ሥራ በዐይንህ ታይ በጆሮህም ትሰማ ዘንድ አግባብ አይደለም› አሉት፡፡ ይህንንም ነገር ነግረውት መላእክት ወደ ሰማይ ዐረጉ፡፡ አባ ኪሮስም የእግዚአብሔርን ድንቅ ሥራ እያደነቀ ወደ በዓቱ ተመለሰ፡፡ ከዚህም በኋላ አባ ኪሮስ ሦስት ቀን ቆይቶ ወደ ሀገር ወጥቶ ሔደ፡፡ መላእክተ ጽልመት የእሳት በትሮችን ይዘው ሲሽቀዳደሙ አየ፡፡ አባ ኪሮስም ደንግጦ የሚሆነውን ይረዳ ዘንድ ወደ እነርሱ ሔደ፡፡ በዚያም በጽኑ ደዌ የተያዘ አንድ ሰው ነበር፡፡ መላእክተ ጽልመት እንደግድግዳ ከበው በእሳት በትር ይደበድቡታል፡፡ ነፍሱንም ‹አንቺ ጎስቋላ ነፍስ ነይ ውጭ፣ እንደሥራሽም ዋጋሽን ተቀበይ…› እያሉ ይሰድቧታል፡፡ በዚህም ጊዜ ቅዱስ ገብርኤል መጥቶ አባ ኪሮስን በእጁ ያዘው፡፡ ከድንጋጤም የተነሣ ነፍሱ ከሥጋው እንዳትለይ ከእራሱ እስከ እግሩ ጥፍር ድረስ በገነት አበባ አሸውና ‹…መጨረሻውን ታይ ዘንድ ጽና› አለው፡፡ ያንጊዜም መልአከ ሞት መጥቶ በዚያች ነፍስ ላይ መርዙን ተነፈሰባት፣ በአፉም ጎርሶ ውጦ አኝኮ መልሶ ተፋት፡፡ ሦስት ጊዜም መላልሶ እንዲህ አደረጋትና ለመላእክተ ጽልመት ሰጥቷቸው ሔደ፡፡ መላእክተ ጽልመትም ከእነርሱ ለአንዱ በጥፍሩ አሲዘው እስከ ሦስተኛ ሰማይ አውጥተው ወደ ምድር ጣሏት፡፡ ሦስት ጊዜም መላልሰው እንዲሁ አደረጉ፡፡ ከዚህም በኋላ እንደሥራዋ ታገኝ ዘንድ ወደላይ አሳርገው ከእግዚአብሔር ፊት አደረሷት፡፡ ቅዱስ ገብርኤልም አባታችን አባ ኪሮስን ‹የጻድቃንንና የኃጥአንን ሞት አይተሃልና ይህን አስተውል› አለው፡፡ አባ ኪሮስ ግን ከድንጋጤው የተነሣ ታመመ፣ ማናገርም ተሳነው፡፡ ቅዱስ ገብርኤልም ‹አባ ኪሮስ ሆይ! አንተም እንዲህ ትሆናለህን?› አለው፡፡ ይህንንም ብሎ በፊቱና በሁለቱ ጆሮው እፍ አለበት፡፡ ልቡንም በዳሰሰው ጊዜ ፍርሃትና ድንጋጤ ከእርሱ ተወገደለት፡፡ ወዲያም ቅዱስ ገብርኤል ወደላከው ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡ አባ ኪሮስም ፈጽሞ እያዘነ ወደ ‹…ወዮልኝ ወዮታ አለብኝ፣ የማዝነው ለዚያ ሰው ብቻ አይደለም ለራሴም ነው እንጂ…› እያለ ወደ በዓቱ ተመለሰ፡፡ በበዓቱም ሆኖ በዕለቱ ዘጠኝ እልፍ ይደግድ ጀመር፣ እንባውም እንደውኃ ይፈስ ጀመር፡፡ ጌታችንም ወደ እርሱ መጥቶ እስካረጋጋውና እስካጽናናው ቃልኪዳንም እስከሰጠው ድረስ እንዲሁ በታላቅ ተጋድሎ ኖረ፡፡)
መላእክተ ብርሃን ‹‹ወይ ነፍስ! እንዴት ለደገኛው መንግሥተ ሰማያት ተፈጥረሽ ለገሃነመ እሳት ሆንሽ? በሥላሴ አምሳል ተፈጥረሽ የዲያብሎስ መረገጫ የሰይጣናት መራወጫ ሆንሽ!?›› ብለው አዝነው አልቅሰው ይሔዳሉ ወዳልነው ነገር እንመለስ-ከዚህ በኋላ መላእክተ ጽልመት የእሳቱን መንዶ፣ የእሳቱን መጋዝ ይዘው መጥተው እንደ ግድግዳ ቆመው አስጨንቀው አስጠብበው ይጠይቋታል፡፡ ምን ብለው ይጠይቋታል? ቢሉ ‹‹አንቺ ነፍስ በማን ታመልኪ ነበር? የሥላሴን አንድነት ሦስትነት፣ ምልዐት፣ ስፋት፣ ርቀት፣ የጌታን ከሰማይ መውረዱን፣ መወለዱን፣ ወልደ አብ ወልደ ማርያም መሆኑን፣ መገፈፍ፣ መገረፉን፣ መሰቀል፣ መሞቱን፣ መቀበሩን፣ መነሣቱን ማረጉን፣ ዳግም ለፍርድ መምጣቱን ታምኛለሽን?›› ብለው ይጠይቋታል፡፡ እርሷም ያልተማረች ከሆዷ በቀር ሌላ የማታውቅ ናትና ‹‹እኔስ የሥላሴን አንድነት ሦስትነት፣ ምልዐት፣ ስፋት፣ ርቀት፣ የጌታን ከሰማይ መውረዱን፣ መወለዱን፣ ወልደ አብ ወልደ ማርያም መሆኑን፣ መገፈፍ፣ መገረፉን፣ መሰቀል፣ መሞቱን፣ መቀበሩን፣ መነሣቱን ማረጉን፣ ዳግም ለፍርድ መምጣቱን አላውቅም፡፡ ለሥጋዬ ስጥር ስግር ስላፋ ስማስን ነበርሁ እንጂ፣ ሃይማኖት አልተማርሁ፣ ምግባር አልሠራሁ፡ እናንተማ ወዳጆቼ ዘመዶቼ አይደላችሁምን? የመከራችሁኝን ሰምቼ ያዘዛችሁኝን ሠርቼ እኖር ነበር እንጂ›› ትላቸዋለች፡፡
የክፉ የኃጥእ ሰው ነፍስ መላእክተ ጽልመትን የት ታውቃቸዋለችና እንዲህ ትላቸዋለች? ቢሉ የክፉ ሰው ነፍስ እንደሆነች ገና በቁመናዋ ሳለች በህልምም በራእይም ከመላእክተ ጽልመት ጋር ገሃነመ እሳት እየወረደች ታይ ነበረችና ስለዚህ ‹‹አውቃችኋለሁ›› ትላቸዋለች፡፡ ቀድሞም አጋንንት ለእርሷ ያዘኑ መስለው ‹‹አንቺ ነፍስ ሰንበትን ብታከብሪ፣ ምጽዋት ብትመጸውቺ፣ ዓሥራት በኩራት ብታወጪ ቦታሽ ይህ ስለሆነ ምን ያደክምሻል? ይልቅስ ቅጠፊ፣ ስረቂ፣ ነፍስ ግደይ፣ ሰንበትን ሻሪ፣ ጾም ግደፊ፣ ጸሎት አቁሚ፣ ዋርሳ ውረሽ፣ ዝሙት ፈጽሚ… ይህንና የመሳሰለውን አድርጊ እያሉ ሲመክሯት ነበርና ስለዚህ ‹‹አውቃችኋለሁ›› ትላቸዋለች፡፡
ከዚኽም በኋላ መላእክተ ጽልመት ‹‹ለራስሽ አንቺ እገዛ እነዳ፣ እበላ እጠጣ፣ እለብስ፣ እደላደል፣ እቀማጠል ብለሽ እንጂ አንቺ ለእኛ ምን ውለታ ውለሽልናል? ቆርሰሽ አላጎረስሽን ጠልቀሽ አላጠጣሽን! አንቺ ኩሩ ትዕቢተኛ እንግዲህ ነይ ውጪ! በቁመናሽ የሠራሽውን የምግባርሽን ዋጋ ብድራቱን ክፈይ…›› እያሉ ራስ ራሷን እየቀጠቀጡ ያስጨንቋታል፡፡ ያስጠብቧታል፡፡ ‹‹ንዒ ፃኢ ከመ ትትፈደዪ ፍዳ አበሳኪ›› እንዳለ ድርሳነ ሰንበት፡፡ ከዚኽ በኋላ መልአከ ሞት ከአድማስ እስከ አድማስ ተስተካክሎ ቁሞ፣ ጥርሱን አግጦ ዐይኑን አፍጦ ይታያታል፡፡ ጥርሱም በመልአኩ ክንድ 88 ነው፡፡ የመልአኩ ክንድ አንዱ በሰው ክንድ 44 ነው፡፡ የአንድ ዐይኑ መቃድ ስፋት 3 ዓመት ከመንፈቅ ያስኬዳል፡፡ የ2ኛው ዐይኑ መቃድ ስፋት 3 ዓመት ከመንፈቅ ያስኬዳል፡፡ በጠቅላላው የሁለት ዐይኑ መቃድ 7 ዓመት ያስኬዳል፡፡ ቁመቱ ደግሞ ከምድር እስከ ሰማይ ነው፡፡ ከዚኽም በኃላ 3 ጊዜ ተራምዶ መጥቶ ከፊቷ ይቆማል፡፡ ያችም ኃጥእ ነፍስ በዚህ ደንግጣ ስትጨነቅ ተንፈንጥራ


እንዲህም ማለቱ በእግረ ነፍስ ነው እንጂ በእግረ ሥጋስ አታስቆምም፡፡ እንዲህማ ከሆነ ምን አድርጋ ትሻገረዋለች ቢሉ በዚህ ዓለም ያሉ አዕዋፍ ዳሩን ገደሉን ባሕሩን እሳቱን ላይ ላዩን በክንፍ እየበረሩ ተሻግረው እንዲሔዱ የእርሷም ሃይማኖቷና ግብሯ ክንፍ ሆኗት መላእክተ ብርሃን ላይ ላዩን ይዘዋት ይሻገራሉ፡፡ እርሷም ከመካከል ስትደርስ አቈልቁላ አይታ መላእክተ ብርሃንን ‹‹…ይህ እሳቱ፣ ባሕሩ፣ ገደሉ፣ ዱሩ ምንድነው?›› ብላ ትጠይቃቸዋለች፡፡ መላእክተ ብርሃንም ‹‹አንቺ ምግባር ብትሠሪ፣ ሃይማኖት ብትማሪ፣ ሰንበትን ብታከብሪ በዚህ መጣሽ እንጂ ምግባር ያልሠሩ፣ ሃይማኖት ያልተማሩ ዘመዶችሽስ በዚያው አረው ከስለው እንደ ጅማት ተኮማትረው መከራ አይተው ይሻገሩታል›› ይሏታል፡፡ እርሷም በዚህ ጊዜ ‹‹…ወየው! ወየው! በምድራዊው ዓለም ላሉ ሰዎች እንዲህ ያለ ብርቱ መከራ እንዳለባቸው ማን በነገራቸው!?...›› ብላ አዝና ተክዛ አልቅሳ ትሔዳለች፡፡
(የክብር ባለቤት ጌታችን ለድንግል እናቱ ለእመቤታችን በሰኔ 21 ቀን በጎልጎታ ስትጸልይ ሳለ ከገባላት ቃልኪዳን ውስጥ አንዱ ‹‹…በቃልኪዳንሽ የታመነውን ይህችን ጸሎት የያዘውን ሰው በደረቴ አቅፌ ባሕረ እሳትን አሻግረዋለሁ፣ ወደ መንበረ መንግሥቴም አቀርበዋለሁ›› የሚል መሆኑን ያስታውሷል፡፡) ወደ ቀደመው ነገር እንመለስና ያቺም ነፍስ አዝና ተክዛ አልቅሳ ስትሔድ ዛሬ በዚህ ዓለም ያለች ሙሽራ አባት እናቷ መልስ ጠርተዋት በደስታ እንድትሔድ እርሷም ከፈጣሪዋ ለመገናኘት ስትሔድ በፍሥሐ በደስታ ትሔዳለች፡፡ ዳግመኛ ዛሬ በዚህ ዓለም ያሉ እናት አባት ለልጃቸው የሚበላውን የሚጠጣውን አሰናድተው እንዲቆዩ ለእርሷም ፈጣሪዋ የመኖሪያዋን ቦታ መንፈሳዊ ምግብና መጠጥ አዘጋጅቶ በፍሥሐ በደስታ ይቆያታል፡፡ እርሷም ገሃነመ እሳትን አልፋ በመውጣቷ ደስ እያላት ከጌታ ዘንድ ስትደርስ ሰግዳ ትቆማለች፡፡ ሰግዳም ስትቆም ጌታ ይጠይቃታል፡፡ ምን ብሎ ይጠይቃታል? ቢሉ የወንድ ነፍስ እንደሆነች ‹‹አንቺ ነፍስ እንጨት መቁረጥ፣ መፍለጥ፣ ቤት ማነጽ፣ ፈረስ መጋለብ ውኃ ዋና፣ ሰንጠረዥ፣ እርሻ፣ ቁፋሮ፣ በገና፣ ጸናጽል፣ ከበሮ፣ ጽሕፈት፣ ድጉሰት ታውቂያለሽን?›› ብሎ አይጠይቃትም፡፡ የሴትም ነፍስ ብትሆን ‹‹አንቺ ነፍስ አልሞ መደቆስ፣ አለስልሶ መፍተል፣ ወጥ መሥራት፣ እንጀራ መጋገር፣ ጠጅና ጠላ መጥመቅ ታውቂያለሽን?›› ብሎ አይጠይቃትም፡፡
እንግዲያስ ምን ብሎ ይጠይቃታል? ቢሉ ‹‹አንቺ ነፍስ በማን ታምኛለሽ? አንድነቴን ሦስትነቴን፣ ምልዐት ስፋቴን፣ ርቀቴን፣ ከሰማየ ሰማያት መውረዴን፣ ከድንግል ማርያም መወለዴን፣ ወልደ አብ በመለኮት፣ ወልደ ማርያም በትስብእት በተዋሕዶ የከበርኩ መሆኔን፣ መገፈፍ መገረፌን፣ መሰቀል መሞቴን፣ መነሣት ማረጌን ታውቂያለችን? ብሎ ይጠይቃታል፡፡ እርሷም የተማረች ናትና ቃሏም እውነተኛ ነውና ‹‹አዎን አምላኬ ሆይ! አንድነትህን ሦስትነትህን፣ ምልዓት ስፋትህን፣ ርቀትህን፣ መውረድ መወለድህን፣ ወልደ አብ ወልደ ማርያም በተዋሕዶ የከበርህ መሆንህን፣ መገፈፍ መገረፍህን፣ መሰቀል መሞትህን፣ መነሣት ማረግህን ዐውቃለሁ›› ብላ ትመልሳለች፡፡ ከዚያም የጌታ በእውነተኛ ቃሉ መላእክተ ብርሃንን ጠርቶ ‹‹ይህቺ ነፍስ ምእመን (ታማኝ) ናትና መንግሥተ ሰማያት እንጂ ገሃነመ እሳት አይገባትም፣ ከሥጋዋ ጋር አዋሕጄ ፍጹም መንግሥተ ሰማያትን እስካወርሳት ድረስ 4 ቀን ገሃነመ እሳትን፣ 3 ቀን መንግሥተ ሰማያትን አዙራችሁ አሳይታችሁ ከጻድቃን ጋራ በገነት አኑሯት›› ብሎ ያዛል፡፡
ከዚህ በኋላ መላእክተ ብርሃን ይዘዋት ወጥተው መንግሥተ ሰማያትን፣ የባለ ሕጎች አገር የደናግልን፣ የጻድቃንን አገር 3 ቀን አዙረው አሳይተው ሽታዋን ጣዕሟን በልቡናዋ አሥርፀው፤ ‹‹አንቺ ነፍስ ሃይማኖት ስላለሽ በጎ ምግባር ስለሠራሽ በእንዲህ ያለ በደስታ ቦታ ያኖርሻል›› ብለው ወደ ገሃነመ እሳት ይዘዋት ይወርዳሉ፡፡ ከገሃነመ እሳት ውስጥ ያለውን የእሳቱን አክሊል፣ የእሳቱን ዘውድ፣ የእሳቱን ዘንዶ፣ የእሳቱን እባብ፣ የእሳቱን አንበሳ፣ የእሳቱን መጋዝ፣ የእሳቱን ሰይፍ፣ የእሳቱን ጦር፣ የእሳቱን ዝናር፣ የእሳቱን ጫማ ይህንንና የመሳሰለውን ሁሉ ካፋቱን ክርፋቱን፣ ግማቱን ሁሉ 4 ቀን አዙረው አሳይተው ‹‹አንቺ ነፍስ ሃይማኖት ባይኖርሽ በጎ ምግባር ባትሠሪ ኖሮ በእንዲህ ያለ መከራ ያኖርሽ ነበር፡፡ ነገር ግን ሃይማኖት ስላለሽ በጎ ምግባር ስለሠራሽ ጌታ በቸርነቱ ከእንዲህ ያለ መከራ አውጥቶ በደስታ ያኖርሻል›› ብለው ወስደው ከጻድቃን ጋር ያኖሯታል፡፡ ሀገረ ሕያዋንን፣ ሀገረ ሰማዕታትን፣ ሀገረ ደናግልን፣ ሀገረ መነኰሳትን፣ ሀገረ ሕጋውያንን እያዞሩ እያሳዩ ‹‹አንቺ ነፍስ ሃይማኖት ብትማሪ ምግባር ብትሠሪ ጌታ በቸርነቱ ከዲያቢሎስ መገዛት ከእንዲህ ያለ መከራ አውጥቶ ከእንዲህ ያለ ተድላ ደስታ አበቃሽ›› ብለው ወስደው ከጻድቃን ጋራ በገነት ያኖሯታል፡፡ ኋላም ከገሃነመ እሳት መውጣቷን፣ መንግሥተ ሰማያት መግባቷን እያሰበች እስከጊዜ ምጽዓት ድረስ በገነት በደስታ ትኖራለች፡፡
ገነት ያለችው በወዴየት ነው? ቢሉ በፀሐይ መውጫ ወይም በስተምሥራቅ በኩል ናት፡፡ በ4ቱ ማዕዛኗ ዐራት ተራሮች አሏት፤ በ4ቱ ተራሮች መካከል 4 አፍላጋት ገብተው ያጠጧታል፡፡
ደገኛይቱ ነፍስ የገሃነመ እሳትን ሥቃይ እያሰበች ከገሃነመ እሳት መውጣቷንና መንግሥተ ሰማያት መግባቷን እያሰበች ፈጣሪዋን እያመሰገነች እስከ ጊዜ ምጽዓት ድረስ በፍሥሐ በደስታ ትኖራለች፡፡ ከምጽአትም በኋላ ከሥጋዋ ጋራ ተዋሕዳ ተድላ ደስታ ካለበት ፍጹም መንግሥተ ሰማያት ትገባለች፡፡ መንግሥተ ሰማያት ያለችው በወዴት ነው? ቢሉ ከኢዮር በላይ ከሰማይ ውዱድ በታች በመካከላቸው ናት፡፡ ሃይማኖት ከምግባር አስተባብሮ የያዘ የመልካም ሰው ነፍስ በዚህ ሁኔታ ዘላለማዊ የክብር ዋጋዋን ተቀብላ ትኖራለች፡፡ ከገቡ መውጣት ካገኙ ማጣት ከሌለባት ከዚህች ፍጹም ተድላ ደስታ ካለባት ርስት መንግሥተ ሰማያት ለመግባት የመድኃኔዓለም ቸርነቱ የድንግል እናቱ የቅዱሳኑ የሰማዕታቱ ሁሉ ምልጃና ጸሎት ይርዳን! አሜን!!!
ሃይማኖት ያልተማረ ከምግባር ጎደለ የኃጥእ ሰው ነፍስስ እንዴት ትሆናለች? ቢሉ የኃጥእ ሰው ነፍስ ገና ከሥጋዋ ሳትለይ በጻዕረ ሞቷ ሳለች መላእክተ ጽልመት በግራ መላእክተ ብርሃን በቀኝ ሆነው ይመጡባታል፡፡ መጥተውም ባዩአት ጊዜ በጨለማ ቁርበት ተጠቅልላ በእሳት ሰንሰለት ታስራ የእሳት አክሊል ደፍታ የእሳት ዝናር ታጥቃ፣ የእሳት ጫማ ተጫምታ፣ ከቁራ 7 እጅ ጠቁራ፣ ከፍታ ከርፍታ ዲያብሎስን መስላ ትታያቸዋለች፡፡ ከዚህ በኋላ መላእክተ ብርሃንን ትገማቸዋለች፣ ትከረፋቸዋለች፤ እነርሱም ይፀየፏታል፡፡ ከእርሷ ርቀው ፈቀቅ ብለው ቆመው ይጠይቋታል፡፡ ምን ብለው ይጠይቋታል? ቢሉ ‹‹አንቺ ነፍስ በማን ታመልኪያለሽ? የሥላሴን አንድነት ሦስትነት፣ ምልዐት፣ ስፋት፣ ርቀት፣ የጌታን ከሰማይ መውረዱን፣ መወለዱን፣ ወልደ አብ ወልደ ማርያም መሆኑን፣ መገፈፍ፣ መገረፉን፣ መሰቀል፣ መሞቱን፣ መቀበሩን፣ መነሣቱን ማረጉን፣ ዳግም ለፍርድ መምጣቱን ታምኛለሽን? የእግዚአብሔርን እንግዳ ተቀብለሻል? ሰንበትን አክብረሻልን?›› ብለው ይጠይቋታል፡፡ እርሷም ያልተማረች ናትና ‹‹እኔስ የሥላሴን አንድነት ሦስትነት፣ ምልዐት፣ ስፋት፣ ርቀት፣ የጌታን ከሰማይ መውረዱን፣ መወለዱን፣ ወልደ አብ ወልደ ማርያም መሆኑን፣ መገፈፍ፣ መገረፉን፣ መሰቀል፣ መሞቱን፣ መቀበሩን፣ መነሣቱን ማረጉን፣ ዳግም ለፍርድ መምጣቱን አላውቅም፡፡ በምንሰ አውቃለሁ? መምህራንን አልጠየቅሁ፣ መጻሕፍትን አላነበብሁ፣ ቤተ


‹‹በውኑ ሞት እንደዚህ መራራ ነውን?›› 1ኛ ሳሙ 15፡32።

(ከዐቢይ ጾሙ ጋር በተገናኘ በብዙዎቻችሁ ጥያቄ መሠረት በድጋሚ የቀረበ)

ይኽ ጽሑፍ ነፍስ ከሥጋ ስትለይ በፍጹም ደስታ አሊያም በእንዴት ያለ አስጨናቂ መከራ ውስጥ እንደምትገኝ የሚያስረዳ ግሩም ምሥጢርን የተመላ ነውና በጥሞና አንብበነው ለነፍሳችን የሚሆን ስንቅ እንሰንቅ ዘንድ ለኹላችን ተዘጋጀልን! (የጽሑፉ ምንጭ ደብረ ሊባኖስ አንድነት ገዳም ‹‹ሕማማተ መስቀል›› በሚል ርዕስ ካሳተመው ድርሳን ላይ ‹‹ሕይወተ ምእመናን›› የሚለው ንዑስ ርዕስ ነው፡፡)
በርዕሱ ላይ ያለውን ኃይለ ቃል ‹‹በውኑ ሞት እንደዚህ መራራ ነውን?›› (1ኛ ሳሙ 15፡32) ሲል የተናገረው በሞት ጣዕር ላይ የነበረው የአማሌቃውያን ንጉሥ አጋግ ነው፡፡ ንጉሥ አጋግ ሃይማኖት የሌለው፣ የብዙ ንጹሐንን ደም በግፍ ሲያፈስ የኖረ ኃጥእ ሰው ነበር፡፡ እርሱም በተራው በሞት አፋፍ ላይ ሳለ ፈራ፣ ተንቀጠቀጠ፡፡ ከጭንቀት ብዛት ጅማቶቹ እርስ በርሳቸው ተለያዩ፤ አጥንቶች ተላቀቁ፡፡
በዓለም ላይ ያለ ማንም ኃጥእ ሰው ንጉሥ ይሁን ሎሌ፣ የተማረ ምሑር ይሁን ያልተማረ ጨዋ፣ ሀብታም ይሁን ድሀ ማንኛውም ሰው በእውነተኛዋ ሃይማኖት ያላመነ ምግባር የሌለው ከሆነ በስተመጨረሻ በሞት አፋፍ ላይ ሳለ እጅግ እፈሪውን መልአከ ሞትን በገሃድ በተመለከተ ጊዜ እንደንጉሥ አጋግ ‹‹ከመዝኑ ሞት መሪር-በውኑ ሞት እንደዚህ መራራ ነውን?›› ማለቱ አይቀርም፡፡ ስለዚህ በአጭሩ ምእመናን ስለ ሃይማኖታቸው ጠንቅቀው ሊያውቁ፣ ምግባር፣ ትሩፋት ሊሠሩ ይገባቸዋል፡፡ ይህስ ስለምንድን ነው? ቢሉ ኋላ በዕለተ ሞት በጌታ ቃል መጠየቅ አይቀርምና ነው፡፡ የክብር ባለቤት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ‹‹በዚህች ምድር ሳላችሁ ሃይማኖት ተማሩ፣ ምግባር ሥሩ›› ብሎ አዟልና ነው፡፡
ኋላ በዕለተ ሞት ጊዜ በጌታ ቃል ምን ተብሎ ይጠየቃል? ቢሉ የመልካም ሰው ነፍስ እንደሆነች ከሥጋዋ ሳትለይ ገና በፃዕረ ሞቷ ሳለች መላእክተ ብርሃን በቀኝ፣ መላእከተ ጽልመት በግራ ሆነው ይመጡባታል፡፡ መጥተውም ባዩዋት ጊዜ የብርሃን ቀሚስ ለብሳ፣ የብርሃን መጐናጸፊያ ተጐናጽፋ፣ የብርሃን አክሊል ደፍታ፣ የብርሃን ዝውድ ተቀዳጅታ፣ የብርሃን ዝናር ታጥቃ፣ የብርሃን ጫማ ተጫምታ፣ የመስቀል ምልክት ያለበት የብርሃን ዘንግ ይዛ፣ ከፀሐይ 7 እጅ አብርታ፣ ከመብረቅ 7 እጅ አስፈርታ፣ አምራና ሠምራ ጌታዋን ክርስቶስን መስላ ትቆያቸዋለች፡፡
ከዚህም በኋላ መላእክተ ጽልመትን እንደ እሳት ትፈጃቸዋለች፤ እንደ ፀሐይ ታንፀባርቅባቸዋለች፤ እነርሱም ይፈሯታል፡፡ ከፊቷ ርቀው ፈቀቅ ብለው ይቆማሉ፡፡ በዚያው ርቀው በቆሙበት ሆነው ጠርተው ይጠይቋታል፡፡ ምን ብለው ይጠይቋታል? ቢሉ ‹‹አንቺ ነፍስ በማን ታመልኪያለሽ? የሥላሴን አንድነት ሦስትነት፣ ምልዐት፣ ስፋት፣ ርቀት፣ የጌታን ከሰማይ መውረዱን፣ መወለዱን፣ ወልደ አብ ወልደ ማርያም መሆኑን፣ መገፈፍ፣ መገረፉን፣ መሰቀል፣ መሞቱን፣ መቀበሩን፣ መነሣቱን ማረጉን፣ ዳግም ለፍርድ መምጣቱን ታምኛለሽን? የእግዚአብሔርን እንግዳ ተቀብለሻል? ሰንበትን አክብረሻልን?›› ብለው ይጠይቋታል፡፡ እርሷም እውነተኛ የተማረች ሃይማኖተኛ ናትና ‹‹አዎን የሥላሴን አንድነት ሦስትነት፣ ምልዐት፣ ስፋት፣ ርቀት፣ የጌታን ከሰማይ መውረዱን፣ መወለዱን፣ ወልደ አብ ወልደ ማርያም መሆኑን፣ መገፈፍ፣ መገረፉን፣ መሰቀል፣ መሞቱን፣ መቀበሩን፣ መነሣቱን ማረጉን፣ ዳግም ለፍርድ መምጣቱን አምናለሁ…ነገር ግን እንደ እናንተ ያለ የከፋ የከረፋ አይቼም ሰምቼም አላውቅም›› ብላ ትመልስላቸዋለች፡፡
መላእክተ ጽልመትም መርምረው የእርነሱ ድርሻ አለመሆኗን ካረጋገጡ በኋላ አፍረው ተዋርደው ‹‹አንቺ ነፍስ እኛ ያጣናትን መንግሥተ ሰማያት አንቺ አገኘሻት!...›› እያሉ እያዘኑ እየተከዙ ትተዋት ይሔዳሉ፡፡
ከዚህም በኋላ መላእክተ ብርሃን ከገነት መልካም መዓዛ ያለው የሽቱ አበባ ቆርጠው ይዘው መጥተው ካጠገቧ ከበዋት ይቆማሉ፡፡ ቆመውም ይጠይቋታል፡፡ ምን ብለው ይጠይቋታል? ቢሉ ‹‹አንቺ ነፍስ በማን ታመልኪያለሽ? የሥላሴን አንድነት ሦስትነት፣ ምልዐት፣ ስፋት፣ ርቀት፣ የጌታን ከሰማይ መውረዱን፣ መወለዱን፣ ወልደ አብ ወልደ ማርያም መሆኑን፣ መገፈፍ፣ መገረፉን፣ መሰቀል፣ መሞቱን፣ መቀበሩን፣ መነሣቱን ማረጉን፣ ዳግም ለፍርድ መምጣቱን ታምኛለሽን? የእግዚአብሔርን እንግዳ ተቀብለሻል? ሰንበትን አክብረሻልን?›› ብለው ይጠይቋታል፡፡ እርሷም ቃሏ እውነት ነውና ‹‹አዎን የሥላሴን አንድነት ሦስትነት፣ ምልዐት፣ ስፋት፣ ርቀት፣ የጌታን ከሰማይ መውረዱን፣ መወለዱን፣ ወልደ አብ ወልደ ማርያም መሆኑን፣ መገፈፍ፣ መገረፉን፣ መሰቀል፣ መሞቱን፣ መቀበሩን፣ መነሣቱን ማረጉን፣ ዳግም ለፍርድ መምጣቱን አምናለሁ›› ብላ ትመልስላቸዋለች፡፡ ዳግመኛም ‹‹5ቱን አዕማደ ምሥጢር 13ቱን ሕማማተ መስቀል ተምረሻል? ሰንበትን አክብረሻል? የእግዚአብሔር እንግዳ ተቀብለሻልን?›› ብለው ይጠይቋታል፡፡ እርሷም ‹‹አዎን አውቃለሁ እናንተማ ወዳጆቼ ዘመዶቼ አይደላችሁምን? የመከራችሁንኝ ሰምቼ፣ ያዘዛችሁኝን ሠርቼ እኖር የለምን? ብላ ትመልስላቸዋለች፡፡ የጻድቅ ነፍስ መላእክተ የት ታውቃቸዋለችና ነው? ቢሉ የመልካም ሰው ነፍስ የሆነች እንደሆነ ገና በቁመናዋ በዓለመ ሥጋ ሳለች በአካለ ነፍስ ከመላእክተ ብርሃን ጋራ ከሰማየ ሰማያት የእወጣች እየወረደች ጌታዋን ፈጣሪዋን ስታመሰግን ትኖር ነበርና ስለዚህ ‹‹አውቃችኋለሁ›› ትላቸዋለች፡፡ መላእክተ ብርሃንም ያችን ነፍስ መርምረው የእነሱ ወገን መሆኗን ካረጋገጡ በኋላ ‹‹ከቃልሽ እናግኘው ብለን ነው እንጂ አዎን እኛማ እናውቅሻለን›› ብለው ይመሰክሩላታል፡፡
ከዚኽም በኋላ ነቢዩ ዳዊት በገናውን፣ ዕዝራ መሰንቆውን ይዘው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እልፍ አዕላፍ መላእክትን፣ ጻድቃን፣ ሰማዕታትን፣ ደናግል መነኰሳትን አስከትሎ ወርዶ በቁመናዋ የሠራችውን የምግባሯን ዋጋ ቃልኪዳን ሰጥቷት ተመልሶ ያርጋል፡፡ መውጣት መውረዱ ለእኛ ክብር ሲል በለበሰው ሥጋ ነው እንጂ በመለሎትነቱስ በሁሉ የመላ ስለሆነ መውጣት መውረድ የለበትም፡፡
ከዚኽም በኋላ መልአከ ሞት አምሮ ሠምሮ መልአከ ብርሃን መስሎ ይታያታል፡፡ ስለምን መልአከ ሞት መልአከ ሣህል መልአከ ብርሃን መስሎ ይታያታል ቢሉ? እንዳትባባ እንዳትፈራ ነው፡፡ ከዚኽም በኋላ መላእክተ ብርሃን ያንን ከገነት ቆርጠው ያመጡትን የሽቱ አበባ ከአፍንጫዋ ላይ ጣል አድርገው ሲያነሡት በመልካሙ የሽታ መዓዛ ተመስጣ ነፍስ ከሥጋዋ ትለያለች፡፡
ከዚኽም በኋላ መላእክተ ብርሃን በፊት በኋላ፣ በቀኝ በግራ ሆነው ዕዝራ መሰንቆውን፣ ዳዊት መገናውን እየደረደሩ እያመሰገኑ ዳዊት ‹‹የጻድቅ ሰው ሞት በእግዚአብሔር ዘንድ ክቡር ነው›› (መዝ 115፡6) እያለ፣ ዕዝራም ‹‹የጻድቃን ሞታቸው ሕይወታቸው ነው…›› እያሉ በዝማሬ በይባቤ ይዘዋት ይሔዳሉ፡፡
ከዚኽም በኋላ መላእክተ ጽልመት ከጌታ ቃል ሳይሰሙ ትእዛዝ ሳይቀበሉ አይመለሱምና ራስ ራሷን እየተመለከቱ ሲከታተሏት ከባሕረ እሳት ይደርሳሉ፡፡ የባሕረ እሳት ቦታዋ ስፍራዋ ወዴት ነው? መጠኗስ ምን ያህል ነው? ቢሉ ቦታዋ ከጠፈር በላይ ከሐኖስ በታች ከመካከል በምጽንዓተ ሰማይ ነው፡፡ ልኳም ይህችን ሰው የሠፈረባት ዓለም ታህላለች፤ ቀኝዋ እሳት ግራዋ ባሕር ነው፣ ውስጧ ገደል መንገዷም ከጭራ የቀጠነ ጠባብ ነው፡፡ ዕዝ 5፡8፡፡

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.