💙💙 የጥያቄዎች መልስ ክፍል 105 💙💙
▶️፩. ዓሣን መብላት በተመለከተ ዓሣ ከውሃ እንደወጣ እንደሚሞት እና ሳይባረክም ነፍሱ ብትወጣ መብላት ይቻላል? የሚያጠምደው ሰው ማንነትስ እንዳይበላ ያደርገዋል? ምሳሌ አጥማጁ አሕዛብ ቢሆን?
✔️መልስ፦ በዚህ ዙሪያ የተጻፈ አላገኘሁም። ነፍሱ ሳይወጣ የታረደውን ብቻ ብሉ ወይም አትብሉ የሚል አላገኘሁም። አጥማጁ አሕዛብ ይሁንም አይሁንም ግን የሚያመጣው ለውጥ የለም። ማንኛውም ቢያመጣው ባርከን አቡነ ዘበሰማያት ብለን ስንበላው ይቀደሳልና።
▶️፪. ቁጥር 14 ላይ "አሁንም እኔ ብቸኛ ልጃቸው ነኝ" ካለ በኋላ ቁጥር 16 ላይ "ሁለቱም ወጥተው ሄዱ ሌላው ልጃቸውም ተከተላቸው" ይላል (ጦቢ.5፥14-16)። ቢያስታርቁልኝ።
✔️መልስ፦ ሌላው ልጃቸውም ተከተላቸው የሚለው የትርጉም ስሕተት ነው። እንጂ ግእዙ "ወተለዎሙ ከልበ ወልዶሙ" ብሎ የተከተላቸው ውሻው ነው እንጂ ሌላ ልጅ ኖሮ ያ ልጅ አይደለም።
▶️፫. "መልአኩም ክፉ ጋኔን ያደረበት ቢኖር ወይም የረከሰ ረቂቅ ጋኔን ያደረበት ቢኖር ጉበቱንና ልቡን ለዚያ ሰው በፊቱ ያጤሱለታል። ሴትም ብትሆን ያጤሱላታል ከዚያ በኋላ አይታመምም" ይላል። ይህ የዓሣ ልብ እና ሐሞትን በመጽሐፉ ለተጠቀሰው አገልግሎት መጠቀም በሐዲስ ኪዳን አለ?
✔️መልስ፦ ለጊዜው ለሣራ ወለተ ራጉኤልና ለጦቢት ጥቅም ሰጥቷል። ለቀጣይ ግን የእነርሱን ችግር የመሰለ ችግር ለገጠመው ሁሉ መፍትሔው ይህ ይሆን አይሆን ግን የተገለጸ ነገር አላገኘሁም። የእነርሱ መፈወስ ተአምራዊም ጭምር ነበርና። ተአምር ደግሞ ሁል ጊዜ አይደረግም።
▶️፬. መጽሐፈ ጦቢት ላይ የተጠቀሰችው ነነዌ በኋላ ነቢዩ ዮናስ ሰብኳት በንስሓ የተረፈችው ከተማ ናት?
✔️መልስ፦ አወ ራሷ ናት። ከብዙ ዘመን በኋላ እንደገና በድላ ተቃጥላለች።
▶️፭. ጦቢ.11፥16 "ጦቢት ግን በፊታቸው እግዚአብሔርን አመሰገነ ፤ እግዚአብሔር ይቅር ብሎታልና" ይላል። ጦቢት እግዚአብሔርን አሳዝኖ ነበርን?
✔️መልስ፦ ጦቢት እግዚአብሔርን አላሳዘነውም። እግዚአብሔር ይቅር ብሎታል ማለት ከበሽታው አድኖታል ማለት ነው። እግዚአብሔር ይማርህ ስንል ከሕመምህ ያድንህ እንደምንለው ያለ ነው። ጦቢት ዓይኑ ላይ ብልዝ ወጥቶበት ስለነበር በኋላ በመዳኑ እግዚአብሔር አዳነው ለማለት ይቅር አለው ተብሏል።
© በትረ ማርያም አበባው
✝️የዩቲዩብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።
🌻የፌስቡክ ገጼ Betremariam Abebaw https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።
▶️፩. ዓሣን መብላት በተመለከተ ዓሣ ከውሃ እንደወጣ እንደሚሞት እና ሳይባረክም ነፍሱ ብትወጣ መብላት ይቻላል? የሚያጠምደው ሰው ማንነትስ እንዳይበላ ያደርገዋል? ምሳሌ አጥማጁ አሕዛብ ቢሆን?
✔️መልስ፦ በዚህ ዙሪያ የተጻፈ አላገኘሁም። ነፍሱ ሳይወጣ የታረደውን ብቻ ብሉ ወይም አትብሉ የሚል አላገኘሁም። አጥማጁ አሕዛብ ይሁንም አይሁንም ግን የሚያመጣው ለውጥ የለም። ማንኛውም ቢያመጣው ባርከን አቡነ ዘበሰማያት ብለን ስንበላው ይቀደሳልና።
▶️፪. ቁጥር 14 ላይ "አሁንም እኔ ብቸኛ ልጃቸው ነኝ" ካለ በኋላ ቁጥር 16 ላይ "ሁለቱም ወጥተው ሄዱ ሌላው ልጃቸውም ተከተላቸው" ይላል (ጦቢ.5፥14-16)። ቢያስታርቁልኝ።
✔️መልስ፦ ሌላው ልጃቸውም ተከተላቸው የሚለው የትርጉም ስሕተት ነው። እንጂ ግእዙ "ወተለዎሙ ከልበ ወልዶሙ" ብሎ የተከተላቸው ውሻው ነው እንጂ ሌላ ልጅ ኖሮ ያ ልጅ አይደለም።
▶️፫. "መልአኩም ክፉ ጋኔን ያደረበት ቢኖር ወይም የረከሰ ረቂቅ ጋኔን ያደረበት ቢኖር ጉበቱንና ልቡን ለዚያ ሰው በፊቱ ያጤሱለታል። ሴትም ብትሆን ያጤሱላታል ከዚያ በኋላ አይታመምም" ይላል። ይህ የዓሣ ልብ እና ሐሞትን በመጽሐፉ ለተጠቀሰው አገልግሎት መጠቀም በሐዲስ ኪዳን አለ?
✔️መልስ፦ ለጊዜው ለሣራ ወለተ ራጉኤልና ለጦቢት ጥቅም ሰጥቷል። ለቀጣይ ግን የእነርሱን ችግር የመሰለ ችግር ለገጠመው ሁሉ መፍትሔው ይህ ይሆን አይሆን ግን የተገለጸ ነገር አላገኘሁም። የእነርሱ መፈወስ ተአምራዊም ጭምር ነበርና። ተአምር ደግሞ ሁል ጊዜ አይደረግም።
▶️፬. መጽሐፈ ጦቢት ላይ የተጠቀሰችው ነነዌ በኋላ ነቢዩ ዮናስ ሰብኳት በንስሓ የተረፈችው ከተማ ናት?
✔️መልስ፦ አወ ራሷ ናት። ከብዙ ዘመን በኋላ እንደገና በድላ ተቃጥላለች።
▶️፭. ጦቢ.11፥16 "ጦቢት ግን በፊታቸው እግዚአብሔርን አመሰገነ ፤ እግዚአብሔር ይቅር ብሎታልና" ይላል። ጦቢት እግዚአብሔርን አሳዝኖ ነበርን?
✔️መልስ፦ ጦቢት እግዚአብሔርን አላሳዘነውም። እግዚአብሔር ይቅር ብሎታል ማለት ከበሽታው አድኖታል ማለት ነው። እግዚአብሔር ይማርህ ስንል ከሕመምህ ያድንህ እንደምንለው ያለ ነው። ጦቢት ዓይኑ ላይ ብልዝ ወጥቶበት ስለነበር በኋላ በመዳኑ እግዚአብሔር አዳነው ለማለት ይቅር አለው ተብሏል።
© በትረ ማርያም አበባው
✝️የዩቲዩብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።
🌻የፌስቡክ ገጼ Betremariam Abebaw https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።