💙💙 የጥያቄዎች መልስ ክፍል 121 💙💙
▶️፩. 2ኛ መቃ.11፥6 "በሥጋና በነፍስ ሕያዋን ሳሉ ከከብቶቻቸውና ከድንኳኖቻቸው ጋራ ወደ ሲኦል አወረዳቸው" ይላል እንስሳት ሲኦል ይወርዳሉን?
✔️መልስ፦ ሲኦል መካነ ነፍሰ ኃጥእ ናት። በሲኦል የሚኖሩ የበደሉ ሰዎችና አጋንንት ናቸው። እንስሳት፣ አዕዋፋት፣ አራዊትና ሌሎችም ደማውያን ፍጥረታት ሲኦል አይኖሩም። ከዚህ ጥቅስ "በሥጋና በነፍስ ሕያዋን ሳሉ ከከብቶቻቸውና ከድንኳኖቻቸው ጋራ ወደ ሲኦል አወረዳቸው" ያለው ወደ መቃብር ወረዱ ማለት ነው። መቃብርን ሲኦል ስለሚለው ነው። ከነቤታቸውና ከነእንስሳቸው ስለሚቀበሩ መቃብሩን ሲኦል ብሎት መሆኑን ያስተውሉ።
▶️፪. "በምድር ላይ ብዙ ዘመን ከመኖር በገነት አንዲት ቀን መደሰት ይሻላል" ይላል (2ኛ መቃ.13፥4)። ከዚህ አያይዤ መጠየቅ የፈለኩት ሰማዕትነትን በተመለከተ ነው። አንድ ክርስቲያን የሞት ሰማዕትነትን ቢሸሽ ወይም ከሞት ሸሽቶ ቢሰደድ እንደ ኀጢአት ይቆጠርበታል? በሃይማኖት ምክንያት ከሚመጣ ሞት ወይም መከራ ሸሽቶ ከአካባቢ ርቆ ለመኖር ቢወስንስ ኀጢአት ነው?
✔️መልስ፦ ኃጢአት አይሆንበትም። በክርስትና ሁለት ዓይነት ሕይወት አለ። ሁለቱንም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አሳይቶናል። አንደኛው ሞትን ከፈራን መሰደድ እንደምንችል የሚያሳይ ነው። ጌታ ወደ ግብጽ የተሰደደ ለሚሰደዱት አብነት ለመሆን ነው። ኢየሱስ ስዱድ ተስፋሆሙ ለስዱዳን እንዳለ ደራሲ። በእርግጥ እርሱ አርአያ ለመሆን ተሰደደ እንጂ ፈርቶ አልተሰደደም። ከፈራን እንድንሸሽ ራሱ ጌታ "በአንዲቱ ከተማም መከራ ቢያሳዩአችሁ ወደ ሌላይቱ ሽሹ" ብሎ ገልጾልናል (ማቴ.10፥23)። ሁለተኛው ለመሞት የቆረጠ ካለ ደግሞ ሰማዕት እንዲሆን ጌታ በመስቀል ተሰቅሎ ሞቶ አሳይቶናል።
▶️፫. "ስሙ ጥልምያኮስ የሚባል መልአከ ሞት ወርዶ ልቡን መታው" ይላል (2ኛ መቃ.12፥13)። ይህ መልአክ ቅዱስ ነው ርኩስ? መልአከ ሞትስ ቁጥሩ አንድ ነው?
✔️መልስ፦ መልአከ ሞት የሚባል ራሱ ሰይጣን ነው። ሰይጣን ደግሞ ርኩስ ነው እንጂ ቅዱስ አይደለም። ሰይጣን የሚባሉ በሰይጣን ስም የሚጠሩ አጋንንት ሁሉ ናቸው። ስለዚህ ቁጥራቸውም ብዙ ነው። መጽሐፍ ግን በግብር አንድ ከሆኑ ዘንድ በአንዱ የሁሉን ግብር ይገልጻል። ለምሳሌ ሰይጣን የብርሃን መልአክ እንደሚመስል ሲጻፍ ለአንዱ ብቻ የተነገረ ሳይሆን ለሁሉ የተነገረ ነው። ቃል በቃል መልአከ ሞትን ሰይጣን ሲለው "እስመ ደቂቅ ተሳተፉ በሥጋ ወደም። ውእቱኒ ተሳተፎሙ በዝንቱ ወከመ ቢጾሙ ኮነ ሎሙ። ከመ በሞቱ ይስዐሮ ለመልአከ ሞት ዘውእቱ ሰይጣን" ይላል (ዕብ.2፥14)። ትርጉሙም "ልጆች በሥጋና በደም አንድ ናቸውና እርሱ ደግሞ በዚህ ከእነርሱ ጋር አንድ ሆነ። ለእነርሱም እንደ ወንድም ሆነላቸው። መልአከ ሞትን በሞቱ ይሽረው ዘንድ ይኸውም ሰይጣን ነው" ማለት ነው።
▶️፬. "የተናገረው ሁሉ እንደ እግዚአብሔር ቃል ይደረግለት ነበር" ይላል (2ኛ መቃ.11፥6)። ለሙሴ እግዚአብሔር እንዲናገር ተናግሮት ሳለ "እንደ እግዚአብሔር ቃል ይደረግለታል" ማለት ምን ማለት ነው?
✔️መልስ፦ የእግዚአብሔር ቃል ከተነገረ ይደረጋል። እግዚአብሔር ተናግሮ ሳይደረግ የቀረ የለም። ሙሴም በጸጋ ከእግዚአብሔር ቃልን (ትምህርትን) ስለተቀበለ እግዚአብሔር በባሕርይው ሁሉን እንደሚያደርግ ሁሉ ለሙሴም በጸጋ ሁሉ ይደረግለት ነበር ማለት ነው።
▶️፭. "ካህናቱን ይሾማቸዋልና በእነርሱ ዘንድ እንደ እግዚአብሔር አስመሰለው" ይላል (2ኛ መቃ.11፥5)። በእነርሱ ዘንድ እንደ እግዚአብሔር አስመሰለው ሲባል ትርጓሜው ምንድን ነው?
✔️መልስ፦ እግዚአብሔር በባሕርይው እንደሚከበር፣ ካህናትንም እንደሚሾም ሁሉ ሙሴ ደግሞ ከእግዚአብሔር በተቀበለው ጸጋ አሮንንና ካህናትን መሾሙንና በካህናት ዘንድ በጸጋ መከበሩን ለመግለጽ እንደ እግዚአብሔር አስመሰለው ተብሏል።
▶️፮. "በሞትህ ጊዜ የተያዝክባት የሲዖል ገመድ በአንገትህ አለችና ሳትወድ ይፈረድብሃል" ይላል (2ኛ መቃ.14፥11)። ከዚህ ከዘላለማዊ ፍርድ አያይዤ ለፍርድ ዙፋን የሚቀርቡት አምነው ምግባር ያልሠሩት ብቻ ናቸው ወይስ ያላመኑትም ናቸው?
✔️መልስ፦ ሰው የሆነ ሁሉ በዕለተ ምጽአት ይነሣል። ሰው ሆኖ ትንሣኤ የሌለው የለም። ሃይማኖት ያልነበራቸው ከሓድያንም፣ ሃይማኖት ኖሯቸው ምግባር ያልሠሩ ኃጥኣንም፣ ሃይማኖት ኖሯቸው ምግባር ትሩፋት የሠሩ ጻድቃንም ሁሉም ይነሣሉ።
▶️፯. "በአንገትህ የታሠረች ያች ገመድ ለእናትህ ማሕፀን ከሲኦል ግንድ ለአንተ ትበቅላለች። አንተም ባደግህ ጊዜ እርሷም ታድጋለች" ይላል (2ኛ መቃ.14፥12)። ከዚህ ጋር አያይዤ
በእናታቸው ማሕፀን እያሉ የሚሞቱ ትንሣኤ ሙታን ያገኛሉ? ለፍርድስ ይቆማሉ? ከቆሙስ እንዴት ባለ መልኩ?
✔️መልስ፦ ተሥዕሎተ መልክእ የተፈጸመለት ሁሉ በትንሣኤ ጊዜ ይነሣል። ሳይወለዱ በውርጃ የወረዱ ሕፃናት ሁሉ ይነሣሉ። ነፍስ የነበረው ሰው ሁሉ ይነሣል። ማንኛውም የሰው ጽንስ ገና ሲጸነስ ከእናትና ከአባቱ ሥጋን እንደሚነሣ ሁሉ ነፍስንም ይነሣል። ስለዚህ ከጽንስ ጀምሮ ነፍስ ያለው ሰው ስለሆነ ይነሣል። ክርስቶስን ሰው ሆነ የምንለው በተጸነሰ ጊዜ ነው። የተጸነሰበትን ቀን ማለትም መጋቢት 29ን ዕለተ ትስብዕት (ሰው የሆነባት ዕለት) ብለን እናከብራታለን። ስለዚህ ማንኛውም ሰው ከተጸነሰ በኋላ ሰው ስለሚባል ሳይወለድ ቢሞት እንኳ በትንሣኤ ጊዜ ይነሣል። እንዴት ባለ መልኩ ይነሣሉ ለሚለው ያኔ ስንደርስ እናውቀዋለን። መጽሐፍ ሁሉም ወንድ የሠላሳ ዓመት ቁመና ኖሮት ሴት የአሥራ አምስት ዓመት ቁመና ኖሯት ይነሣሉ ብሎናል።
▶️፰. "ያን ጊዜ በነፋስ ውስጥ ያለ ነፋስ ባሕርይህም ቢሆን፥ በውኃ ውስጥ ያለ ውኃ ባሕርይህም ቢሆን፤ በመሬት ውስጥ ያለ መሬት ባሕርይህም ቢሆን፤ በእሳት ውስጥ ያለ እሳት ባሕርይህም ቢሆን ይመጣል። በአንተ ያደረች በጨለማ የምትኖር ነፍስም ብትሆን ትመጣለች" ይላል (2ኛ መቃ.14፥19)። የዚህ ንባብ ትርጓሜ ምንድን ነው?
✔️መልስ፦ ሰው ሲሞት ነፍሱ ከሥጋው ትለያለች። ተለይታም ኃጥእ ከነበረ ሲኦል ይቆያል። ጻድቅ ከነበረ ገነት ይቆያል። ሥጋችን ደግሞ ከአራቱ ባሕርያት የተገኘ እንደመሆኑ የመሬት ባሕርይ ወደ መሬትነት፣ የነፋስ ባሕርይ ወደ ነፋስነት፣ የእሳት ባሕርይ ወደ እሳትነት፣ የውሃ ባሕርይ ወደ ውሃነት ይመለሳል። በዕለተ ምጽአት በዳግም ትንሣኤ ጊዜ ሙታን ሲነሡ አራቱ ባሕርያት ከሞት በፊት ወደነበሩበት የሰውነት ማንነት ይመለሳሉ። የኃጥእ ነፍስም ከጨለማ ከሲኦል ወጥታ ከአራቱ ባሕርያት ጋር ተዋሕዳ ትነሣለች። የጻድቅ ነፍስ ደግሞ ከብርሃን ከገነት ወጥታ ከአራቱ ባሕርያት ጋር ተዋሕዳ ትነሣለች። ከዚያ ዘለዓለማዊ ፍርድ ይደረጋል ማለት ነው።
▶️፱. "በሙሴ ወንበር ተቀምጠህ በቃልህ የሙታን ትንሣኤ የለም ትላለህ" ይላል (2ኛ መቃ.14፥24)። በሙሴ ወንበር ተቀምጠህ ሲል ምን ማለት ነው?
✔️መልስ፦ የሙሴን መጻሕፍት ተቀብለው የሚያስተምሩ ሰዎች በሙሴ ወንበር የተቀመጡ ይባላሉ። ፈሪሳውያን፣ አይሁድ፣ ሳምራውያን፣ ሰዱቃውያን ሁሉ የሙሴን መጻሕፍት ተቀብለው ነገር ግን በመጻሕፍቱ መሠረታዊ ፍሬ ሐሳብ የማያምኑ ስለነበሩ በሙሴ ወንበር ተቀምጣችሁ ትንሣኤ ሙታን የለም ትላላችሁ ተብለው ተገሥጸዋል (ማቴ.23፥2)።
▶️፩. 2ኛ መቃ.11፥6 "በሥጋና በነፍስ ሕያዋን ሳሉ ከከብቶቻቸውና ከድንኳኖቻቸው ጋራ ወደ ሲኦል አወረዳቸው" ይላል እንስሳት ሲኦል ይወርዳሉን?
✔️መልስ፦ ሲኦል መካነ ነፍሰ ኃጥእ ናት። በሲኦል የሚኖሩ የበደሉ ሰዎችና አጋንንት ናቸው። እንስሳት፣ አዕዋፋት፣ አራዊትና ሌሎችም ደማውያን ፍጥረታት ሲኦል አይኖሩም። ከዚህ ጥቅስ "በሥጋና በነፍስ ሕያዋን ሳሉ ከከብቶቻቸውና ከድንኳኖቻቸው ጋራ ወደ ሲኦል አወረዳቸው" ያለው ወደ መቃብር ወረዱ ማለት ነው። መቃብርን ሲኦል ስለሚለው ነው። ከነቤታቸውና ከነእንስሳቸው ስለሚቀበሩ መቃብሩን ሲኦል ብሎት መሆኑን ያስተውሉ።
▶️፪. "በምድር ላይ ብዙ ዘመን ከመኖር በገነት አንዲት ቀን መደሰት ይሻላል" ይላል (2ኛ መቃ.13፥4)። ከዚህ አያይዤ መጠየቅ የፈለኩት ሰማዕትነትን በተመለከተ ነው። አንድ ክርስቲያን የሞት ሰማዕትነትን ቢሸሽ ወይም ከሞት ሸሽቶ ቢሰደድ እንደ ኀጢአት ይቆጠርበታል? በሃይማኖት ምክንያት ከሚመጣ ሞት ወይም መከራ ሸሽቶ ከአካባቢ ርቆ ለመኖር ቢወስንስ ኀጢአት ነው?
✔️መልስ፦ ኃጢአት አይሆንበትም። በክርስትና ሁለት ዓይነት ሕይወት አለ። ሁለቱንም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አሳይቶናል። አንደኛው ሞትን ከፈራን መሰደድ እንደምንችል የሚያሳይ ነው። ጌታ ወደ ግብጽ የተሰደደ ለሚሰደዱት አብነት ለመሆን ነው። ኢየሱስ ስዱድ ተስፋሆሙ ለስዱዳን እንዳለ ደራሲ። በእርግጥ እርሱ አርአያ ለመሆን ተሰደደ እንጂ ፈርቶ አልተሰደደም። ከፈራን እንድንሸሽ ራሱ ጌታ "በአንዲቱ ከተማም መከራ ቢያሳዩአችሁ ወደ ሌላይቱ ሽሹ" ብሎ ገልጾልናል (ማቴ.10፥23)። ሁለተኛው ለመሞት የቆረጠ ካለ ደግሞ ሰማዕት እንዲሆን ጌታ በመስቀል ተሰቅሎ ሞቶ አሳይቶናል።
▶️፫. "ስሙ ጥልምያኮስ የሚባል መልአከ ሞት ወርዶ ልቡን መታው" ይላል (2ኛ መቃ.12፥13)። ይህ መልአክ ቅዱስ ነው ርኩስ? መልአከ ሞትስ ቁጥሩ አንድ ነው?
✔️መልስ፦ መልአከ ሞት የሚባል ራሱ ሰይጣን ነው። ሰይጣን ደግሞ ርኩስ ነው እንጂ ቅዱስ አይደለም። ሰይጣን የሚባሉ በሰይጣን ስም የሚጠሩ አጋንንት ሁሉ ናቸው። ስለዚህ ቁጥራቸውም ብዙ ነው። መጽሐፍ ግን በግብር አንድ ከሆኑ ዘንድ በአንዱ የሁሉን ግብር ይገልጻል። ለምሳሌ ሰይጣን የብርሃን መልአክ እንደሚመስል ሲጻፍ ለአንዱ ብቻ የተነገረ ሳይሆን ለሁሉ የተነገረ ነው። ቃል በቃል መልአከ ሞትን ሰይጣን ሲለው "እስመ ደቂቅ ተሳተፉ በሥጋ ወደም። ውእቱኒ ተሳተፎሙ በዝንቱ ወከመ ቢጾሙ ኮነ ሎሙ። ከመ በሞቱ ይስዐሮ ለመልአከ ሞት ዘውእቱ ሰይጣን" ይላል (ዕብ.2፥14)። ትርጉሙም "ልጆች በሥጋና በደም አንድ ናቸውና እርሱ ደግሞ በዚህ ከእነርሱ ጋር አንድ ሆነ። ለእነርሱም እንደ ወንድም ሆነላቸው። መልአከ ሞትን በሞቱ ይሽረው ዘንድ ይኸውም ሰይጣን ነው" ማለት ነው።
▶️፬. "የተናገረው ሁሉ እንደ እግዚአብሔር ቃል ይደረግለት ነበር" ይላል (2ኛ መቃ.11፥6)። ለሙሴ እግዚአብሔር እንዲናገር ተናግሮት ሳለ "እንደ እግዚአብሔር ቃል ይደረግለታል" ማለት ምን ማለት ነው?
✔️መልስ፦ የእግዚአብሔር ቃል ከተነገረ ይደረጋል። እግዚአብሔር ተናግሮ ሳይደረግ የቀረ የለም። ሙሴም በጸጋ ከእግዚአብሔር ቃልን (ትምህርትን) ስለተቀበለ እግዚአብሔር በባሕርይው ሁሉን እንደሚያደርግ ሁሉ ለሙሴም በጸጋ ሁሉ ይደረግለት ነበር ማለት ነው።
▶️፭. "ካህናቱን ይሾማቸዋልና በእነርሱ ዘንድ እንደ እግዚአብሔር አስመሰለው" ይላል (2ኛ መቃ.11፥5)። በእነርሱ ዘንድ እንደ እግዚአብሔር አስመሰለው ሲባል ትርጓሜው ምንድን ነው?
✔️መልስ፦ እግዚአብሔር በባሕርይው እንደሚከበር፣ ካህናትንም እንደሚሾም ሁሉ ሙሴ ደግሞ ከእግዚአብሔር በተቀበለው ጸጋ አሮንንና ካህናትን መሾሙንና በካህናት ዘንድ በጸጋ መከበሩን ለመግለጽ እንደ እግዚአብሔር አስመሰለው ተብሏል።
▶️፮. "በሞትህ ጊዜ የተያዝክባት የሲዖል ገመድ በአንገትህ አለችና ሳትወድ ይፈረድብሃል" ይላል (2ኛ መቃ.14፥11)። ከዚህ ከዘላለማዊ ፍርድ አያይዤ ለፍርድ ዙፋን የሚቀርቡት አምነው ምግባር ያልሠሩት ብቻ ናቸው ወይስ ያላመኑትም ናቸው?
✔️መልስ፦ ሰው የሆነ ሁሉ በዕለተ ምጽአት ይነሣል። ሰው ሆኖ ትንሣኤ የሌለው የለም። ሃይማኖት ያልነበራቸው ከሓድያንም፣ ሃይማኖት ኖሯቸው ምግባር ያልሠሩ ኃጥኣንም፣ ሃይማኖት ኖሯቸው ምግባር ትሩፋት የሠሩ ጻድቃንም ሁሉም ይነሣሉ።
▶️፯. "በአንገትህ የታሠረች ያች ገመድ ለእናትህ ማሕፀን ከሲኦል ግንድ ለአንተ ትበቅላለች። አንተም ባደግህ ጊዜ እርሷም ታድጋለች" ይላል (2ኛ መቃ.14፥12)። ከዚህ ጋር አያይዤ
በእናታቸው ማሕፀን እያሉ የሚሞቱ ትንሣኤ ሙታን ያገኛሉ? ለፍርድስ ይቆማሉ? ከቆሙስ እንዴት ባለ መልኩ?
✔️መልስ፦ ተሥዕሎተ መልክእ የተፈጸመለት ሁሉ በትንሣኤ ጊዜ ይነሣል። ሳይወለዱ በውርጃ የወረዱ ሕፃናት ሁሉ ይነሣሉ። ነፍስ የነበረው ሰው ሁሉ ይነሣል። ማንኛውም የሰው ጽንስ ገና ሲጸነስ ከእናትና ከአባቱ ሥጋን እንደሚነሣ ሁሉ ነፍስንም ይነሣል። ስለዚህ ከጽንስ ጀምሮ ነፍስ ያለው ሰው ስለሆነ ይነሣል። ክርስቶስን ሰው ሆነ የምንለው በተጸነሰ ጊዜ ነው። የተጸነሰበትን ቀን ማለትም መጋቢት 29ን ዕለተ ትስብዕት (ሰው የሆነባት ዕለት) ብለን እናከብራታለን። ስለዚህ ማንኛውም ሰው ከተጸነሰ በኋላ ሰው ስለሚባል ሳይወለድ ቢሞት እንኳ በትንሣኤ ጊዜ ይነሣል። እንዴት ባለ መልኩ ይነሣሉ ለሚለው ያኔ ስንደርስ እናውቀዋለን። መጽሐፍ ሁሉም ወንድ የሠላሳ ዓመት ቁመና ኖሮት ሴት የአሥራ አምስት ዓመት ቁመና ኖሯት ይነሣሉ ብሎናል።
▶️፰. "ያን ጊዜ በነፋስ ውስጥ ያለ ነፋስ ባሕርይህም ቢሆን፥ በውኃ ውስጥ ያለ ውኃ ባሕርይህም ቢሆን፤ በመሬት ውስጥ ያለ መሬት ባሕርይህም ቢሆን፤ በእሳት ውስጥ ያለ እሳት ባሕርይህም ቢሆን ይመጣል። በአንተ ያደረች በጨለማ የምትኖር ነፍስም ብትሆን ትመጣለች" ይላል (2ኛ መቃ.14፥19)። የዚህ ንባብ ትርጓሜ ምንድን ነው?
✔️መልስ፦ ሰው ሲሞት ነፍሱ ከሥጋው ትለያለች። ተለይታም ኃጥእ ከነበረ ሲኦል ይቆያል። ጻድቅ ከነበረ ገነት ይቆያል። ሥጋችን ደግሞ ከአራቱ ባሕርያት የተገኘ እንደመሆኑ የመሬት ባሕርይ ወደ መሬትነት፣ የነፋስ ባሕርይ ወደ ነፋስነት፣ የእሳት ባሕርይ ወደ እሳትነት፣ የውሃ ባሕርይ ወደ ውሃነት ይመለሳል። በዕለተ ምጽአት በዳግም ትንሣኤ ጊዜ ሙታን ሲነሡ አራቱ ባሕርያት ከሞት በፊት ወደነበሩበት የሰውነት ማንነት ይመለሳሉ። የኃጥእ ነፍስም ከጨለማ ከሲኦል ወጥታ ከአራቱ ባሕርያት ጋር ተዋሕዳ ትነሣለች። የጻድቅ ነፍስ ደግሞ ከብርሃን ከገነት ወጥታ ከአራቱ ባሕርያት ጋር ተዋሕዳ ትነሣለች። ከዚያ ዘለዓለማዊ ፍርድ ይደረጋል ማለት ነው።
▶️፱. "በሙሴ ወንበር ተቀምጠህ በቃልህ የሙታን ትንሣኤ የለም ትላለህ" ይላል (2ኛ መቃ.14፥24)። በሙሴ ወንበር ተቀምጠህ ሲል ምን ማለት ነው?
✔️መልስ፦ የሙሴን መጻሕፍት ተቀብለው የሚያስተምሩ ሰዎች በሙሴ ወንበር የተቀመጡ ይባላሉ። ፈሪሳውያን፣ አይሁድ፣ ሳምራውያን፣ ሰዱቃውያን ሁሉ የሙሴን መጻሕፍት ተቀብለው ነገር ግን በመጻሕፍቱ መሠረታዊ ፍሬ ሐሳብ የማያምኑ ስለነበሩ በሙሴ ወንበር ተቀምጣችሁ ትንሣኤ ሙታን የለም ትላላችሁ ተብለው ተገሥጸዋል (ማቴ.23፥2)።