▶️፲. "ይህንንም ነገር ተናግሮ ሳይጨርስ ስሙ ጥልምያኮስ የሚባል መልአከ ሞት ወርዶ ልቡን መታው በዚያችው ሰዓት ሞተ" ይላል (2ኛ መቃ.12፥13)። በመቃብያን ቀዳማዊ ላይ ግን ጺሩጻይዳን የወባ ትንኝ ነክሳው እንደሞተ ነበር የተገለጸውና አይጋጭም?
✔️መልስ፦ አይጋጭም። በብሉይ ኪዳን ማንኛውም ሰው በማንኛውም በሽታ ቢታመምም ነፍሱ ከሥጋው የሚለየው ግን በመልአከ ሞት አማካኝነት ነበር። ስለዚህ ጺሩጻይዳን ወባ ነከሰችውና በጣም ታመመ። በእርሷ ምክንያት ለሞት ደረሰ። ነፍሱን ከሥጋው ደግሞ መልአከ ሞት ለየው። ስለዚህ ምንም የሚጋጭ ነገር የለውም። አንዱ ከአንዱ ጋር የተያያዘ ነውና። ሰው በበሽታ ታሞ ቢሞት የሞቱ መንሥኤ በሽታው ቢሆንም በኋላ ነፍስ ከሥጋ የሚለይ ግን መልአከ ሞት ነው። ስለዚህ የጺሩጻይዳንን ሞት መነሻ ምክንያት ሲያይ በወባ ትንኝ ሞተ ሲባል፣ ነፍሱን ከሥጋ የለየውን ሲያይ በመልአከ ሞት ሞተ ተብሏል።
▶️፲፩. "ሳምራውያን ግን ሥጋችን ትቢያ ይሆናልና አይነሣም ይላሉ" ይላል (2ኛ መቃ.14፥2)። በሌላ ደግሞ "ሰዱቃውያን ግን ነፍሳችን ከሥጋችን ከወጣች በኋላ ከሞቱ ሰዎች ጋራ አንነሣም ለሥጋና ለነፍስም ከሞት በኋላ መነሣት የላቸውም ከሞትንም በኋላ አንነሣም ይላሉ" የሚል አለ (2ኛ መቃ.14፥7)። የሁለቱ ሐሳብ ልዩነት ምንድን ነው?
✔️መልስ፦ የሰዱቃውያን ትምህርት ሰው ሲሞት ነፍሱ እንደ ጉም ተና ትጠፋለች፣ ሥጋውም ፈርሶ በስብሶ ይቀራል የሚል ነው። የሳምራውያን ትምህርት ደግሞ ነፍስ ትኖራለች እንጂ አትጠፋም። ሥጋ ብቻ ነው ፈርሶ በስብሶ የሚቀር የሚል ነው።
▶️፲፪. 2ኛ መቃ.14፥16 ላይ "ሥጋህም ከነፍስህ ተለይቶ ከኖረ በኋላ እንደ አባታችን እንደ አዳም ሥጋ ሰባት እጥፍ ሆኖ የእግዚአብሔር የቸርነቱ ጠል ታስነሣሃለች" ያለው ቢብራራልኝ።
✔️መልስ፦ ሰባት እጥፍ የሚለው ፍጹም ለማለት ነው። እስመ ኍልቍ ሳብዕ ፍጹም በኀበ ዕብራውያን እንዲል። ስለዚህ በምጽአት ጊዜ ምንም ምን ሳይጎድል አካልህ ይነሣል ማለት ነው። የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ መተርጉማን ይህን በጥሩ ተርጉመውታል። ግእዙ "ወሥጋከኒ ተአቲቶ ከዊኖ ምስብዒተ በከመ ሥጋሁ ለአቡነ አዳም ታነሥአከ ጠለ ምሕረቱ ለእግዚአብሔር" የሚለውን "ሥጋህም ከነፍስህ ከተለየ በኋላ እንደ አባታችን እንደ አዳም ሥጋ ፍጹም ሆኖ በእግዚአብሔር በቸርነቱ ጠል ይነሣል" ብለው ተርጉመውታል።
▶️፲፫. "ሥጋዎችም ሬሳቸው በወደቀባት ቦታ ይሰበሰባሉ ነፍሳት የሚኖሩባቸው ቦታቸውም ይከፈታሉ ነፍሳትም ቀድሞ ወደ ተለዩበት ወደ ሥጋ ይመለሳሉ" ይላል (2ኛ መቃ.14፥33)። በትንሣኤ ዘጉባኤ ነፍስና ሥጋ መጀመርያ በተለያዩበት ቦታ (ውሃ ያሰጠመውም ውሃ ውስጥ፣ አውሬ የበላውም የተበላበት ቦታ ላይ፣ ወዘተ) ይዋሓዳሉ ማለቱ ነው? እንደዚያ ከሆነ "በደብረ ጽዮን ከበጎቹ ጋር በቀኝ ያቁመን" የምንለው ጸሎት ምን ይሆን?
✔️መልስ፦ አዎ ቀጥታ የተገለጸው እንዲህ ነው። ሰው ሬሳው ከወደቀበት ሆኖ እንደሚነሣ በግልጽ ተጽፏል። "ወይትጋብኡ ሥጋት ውስተ መካናቲሆሙ ኀበ ወድቀ አብድንቲሆሙ" ያለው ለዚህ ነው። ቀሪ የትንሣኤን አፈጻጸም ስንደርስበት የምናውቀው ይሆናል። ከየወደቁበት ሆነው ከተነሡ በኋላ ጻድቃንን በቀኙ፣ ኃጥኣንን በግራው ያቆማቸዋል። ስለዚህ እኛንም በቸርነቱ በቀኙ ያቁመን እንላለን። በቀኙ ያቁመን ማለት የዘለዓለም ሕይወትን ይስጠን ማለት ነው። በግራ አቆማቸው ማለት ወደ ዘለዓለማዊ የመከራ ቦታ እንዲሄዱ ፈረደባቸው ማለት ነው። በደብረ ጽዮን እግዚአብሔር ነግሦልን ይኖራል ማለት በመንግሥተ ሰማያት ነግሦልን ይኖራል ማለት ነው።
▶️፲፬. 2ኛ መቃ.14፥1 አይሁድ በትንሣኤ ሙታን አያምኑም እንዴ? በተጨማሪ በኦሪት የተጻፉ ስለ ትንሣኤ ሙታን የሚያትቱ ጥቅሶች የትኞቹ ናቸው? (2ኛ መቃ.14፥25)።
✔️መልስ፦ መላው አይሁድ ባይሆኑም ዛሬ እንብላ እንጠጣ፣ ነገ እንሞታለን፣ በዚያም የምናየው የለም የሚሉ የአይሁድ ክፍሎች እንደነበሩ መጽሐፈ መቃብያን በግልጽ ጽፎልናል። በኦሪት ትንሣኤ ሙታን እንዳለ የሚያስረዱ ብዙ ምሳሌዎች አሉ። ከእነዚህም አንዱ የሣራ አርጅቶ መውለድ ነው። ይህን የመሰሉ ብዙ ምሳሌያዊ ትምህርቶች አሉ። ሙሉ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን በመክብባቸው ኦሪት ስለሚላቸው ዳዊትም "እስመ ኢተኀድጋ ውስተ ሲኦል ለነፍስየ" ብሎ ሰውነቴን በመቃብር አትተዋትም ብሏል። በዚህም ትንሣኤ ሙታን መኖሩን አስረድቷል። በመጽሐፈ መቃብያን ቀዳማዊ ላይም በስፋት ትንሣኤ ስለመኖሩ ተገልጿል።
▶️፲፭. 2ኛ መቃ.14፥6 ጳውሎስ ያለው የትንሣኤ ሙታን አረዳድ ከፈሪሳውያን ጋር ተመሳሳይ ነውን? (የሐዋ.ሥራ 23፥6)።
✔️መልስ፦ አይመሳሰልም። ቅዱስ ጳውሎስ ፈሪሳዊ ነኝ ያለው በግብሩ ሳይሆን በትውልዱ ነው። እንጂ እርሱማ ትንሣኤ ሙታንን የሚያምን ስለትንሣኤ ሙታንም በስፋት ያስተማረ ታላቅ ሐዋርያ ነው (ዕብ.6፥2)።
© በትረ ማርያም አበባው
✝️የዩቲዩብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።
🌻የፌስቡክ ገጼ Betremariam Abebaw https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።
✔️መልስ፦ አይጋጭም። በብሉይ ኪዳን ማንኛውም ሰው በማንኛውም በሽታ ቢታመምም ነፍሱ ከሥጋው የሚለየው ግን በመልአከ ሞት አማካኝነት ነበር። ስለዚህ ጺሩጻይዳን ወባ ነከሰችውና በጣም ታመመ። በእርሷ ምክንያት ለሞት ደረሰ። ነፍሱን ከሥጋው ደግሞ መልአከ ሞት ለየው። ስለዚህ ምንም የሚጋጭ ነገር የለውም። አንዱ ከአንዱ ጋር የተያያዘ ነውና። ሰው በበሽታ ታሞ ቢሞት የሞቱ መንሥኤ በሽታው ቢሆንም በኋላ ነፍስ ከሥጋ የሚለይ ግን መልአከ ሞት ነው። ስለዚህ የጺሩጻይዳንን ሞት መነሻ ምክንያት ሲያይ በወባ ትንኝ ሞተ ሲባል፣ ነፍሱን ከሥጋ የለየውን ሲያይ በመልአከ ሞት ሞተ ተብሏል።
▶️፲፩. "ሳምራውያን ግን ሥጋችን ትቢያ ይሆናልና አይነሣም ይላሉ" ይላል (2ኛ መቃ.14፥2)። በሌላ ደግሞ "ሰዱቃውያን ግን ነፍሳችን ከሥጋችን ከወጣች በኋላ ከሞቱ ሰዎች ጋራ አንነሣም ለሥጋና ለነፍስም ከሞት በኋላ መነሣት የላቸውም ከሞትንም በኋላ አንነሣም ይላሉ" የሚል አለ (2ኛ መቃ.14፥7)። የሁለቱ ሐሳብ ልዩነት ምንድን ነው?
✔️መልስ፦ የሰዱቃውያን ትምህርት ሰው ሲሞት ነፍሱ እንደ ጉም ተና ትጠፋለች፣ ሥጋውም ፈርሶ በስብሶ ይቀራል የሚል ነው። የሳምራውያን ትምህርት ደግሞ ነፍስ ትኖራለች እንጂ አትጠፋም። ሥጋ ብቻ ነው ፈርሶ በስብሶ የሚቀር የሚል ነው።
▶️፲፪. 2ኛ መቃ.14፥16 ላይ "ሥጋህም ከነፍስህ ተለይቶ ከኖረ በኋላ እንደ አባታችን እንደ አዳም ሥጋ ሰባት እጥፍ ሆኖ የእግዚአብሔር የቸርነቱ ጠል ታስነሣሃለች" ያለው ቢብራራልኝ።
✔️መልስ፦ ሰባት እጥፍ የሚለው ፍጹም ለማለት ነው። እስመ ኍልቍ ሳብዕ ፍጹም በኀበ ዕብራውያን እንዲል። ስለዚህ በምጽአት ጊዜ ምንም ምን ሳይጎድል አካልህ ይነሣል ማለት ነው። የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ መተርጉማን ይህን በጥሩ ተርጉመውታል። ግእዙ "ወሥጋከኒ ተአቲቶ ከዊኖ ምስብዒተ በከመ ሥጋሁ ለአቡነ አዳም ታነሥአከ ጠለ ምሕረቱ ለእግዚአብሔር" የሚለውን "ሥጋህም ከነፍስህ ከተለየ በኋላ እንደ አባታችን እንደ አዳም ሥጋ ፍጹም ሆኖ በእግዚአብሔር በቸርነቱ ጠል ይነሣል" ብለው ተርጉመውታል።
▶️፲፫. "ሥጋዎችም ሬሳቸው በወደቀባት ቦታ ይሰበሰባሉ ነፍሳት የሚኖሩባቸው ቦታቸውም ይከፈታሉ ነፍሳትም ቀድሞ ወደ ተለዩበት ወደ ሥጋ ይመለሳሉ" ይላል (2ኛ መቃ.14፥33)። በትንሣኤ ዘጉባኤ ነፍስና ሥጋ መጀመርያ በተለያዩበት ቦታ (ውሃ ያሰጠመውም ውሃ ውስጥ፣ አውሬ የበላውም የተበላበት ቦታ ላይ፣ ወዘተ) ይዋሓዳሉ ማለቱ ነው? እንደዚያ ከሆነ "በደብረ ጽዮን ከበጎቹ ጋር በቀኝ ያቁመን" የምንለው ጸሎት ምን ይሆን?
✔️መልስ፦ አዎ ቀጥታ የተገለጸው እንዲህ ነው። ሰው ሬሳው ከወደቀበት ሆኖ እንደሚነሣ በግልጽ ተጽፏል። "ወይትጋብኡ ሥጋት ውስተ መካናቲሆሙ ኀበ ወድቀ አብድንቲሆሙ" ያለው ለዚህ ነው። ቀሪ የትንሣኤን አፈጻጸም ስንደርስበት የምናውቀው ይሆናል። ከየወደቁበት ሆነው ከተነሡ በኋላ ጻድቃንን በቀኙ፣ ኃጥኣንን በግራው ያቆማቸዋል። ስለዚህ እኛንም በቸርነቱ በቀኙ ያቁመን እንላለን። በቀኙ ያቁመን ማለት የዘለዓለም ሕይወትን ይስጠን ማለት ነው። በግራ አቆማቸው ማለት ወደ ዘለዓለማዊ የመከራ ቦታ እንዲሄዱ ፈረደባቸው ማለት ነው። በደብረ ጽዮን እግዚአብሔር ነግሦልን ይኖራል ማለት በመንግሥተ ሰማያት ነግሦልን ይኖራል ማለት ነው።
▶️፲፬. 2ኛ መቃ.14፥1 አይሁድ በትንሣኤ ሙታን አያምኑም እንዴ? በተጨማሪ በኦሪት የተጻፉ ስለ ትንሣኤ ሙታን የሚያትቱ ጥቅሶች የትኞቹ ናቸው? (2ኛ መቃ.14፥25)።
✔️መልስ፦ መላው አይሁድ ባይሆኑም ዛሬ እንብላ እንጠጣ፣ ነገ እንሞታለን፣ በዚያም የምናየው የለም የሚሉ የአይሁድ ክፍሎች እንደነበሩ መጽሐፈ መቃብያን በግልጽ ጽፎልናል። በኦሪት ትንሣኤ ሙታን እንዳለ የሚያስረዱ ብዙ ምሳሌዎች አሉ። ከእነዚህም አንዱ የሣራ አርጅቶ መውለድ ነው። ይህን የመሰሉ ብዙ ምሳሌያዊ ትምህርቶች አሉ። ሙሉ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን በመክብባቸው ኦሪት ስለሚላቸው ዳዊትም "እስመ ኢተኀድጋ ውስተ ሲኦል ለነፍስየ" ብሎ ሰውነቴን በመቃብር አትተዋትም ብሏል። በዚህም ትንሣኤ ሙታን መኖሩን አስረድቷል። በመጽሐፈ መቃብያን ቀዳማዊ ላይም በስፋት ትንሣኤ ስለመኖሩ ተገልጿል።
▶️፲፭. 2ኛ መቃ.14፥6 ጳውሎስ ያለው የትንሣኤ ሙታን አረዳድ ከፈሪሳውያን ጋር ተመሳሳይ ነውን? (የሐዋ.ሥራ 23፥6)።
✔️መልስ፦ አይመሳሰልም። ቅዱስ ጳውሎስ ፈሪሳዊ ነኝ ያለው በግብሩ ሳይሆን በትውልዱ ነው። እንጂ እርሱማ ትንሣኤ ሙታንን የሚያምን ስለትንሣኤ ሙታንም በስፋት ያስተማረ ታላቅ ሐዋርያ ነው (ዕብ.6፥2)።
© በትረ ማርያም አበባው
✝️የዩቲዩብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።
🌻የፌስቡክ ገጼ Betremariam Abebaw https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።