የተኩስ አቁም ስምምነት በተደረሰባት ጋዛ እስራኤል በፈጸመችው የአየር ጥቃት 73 ፍልስጤማውያን መገደላቸው ተገለጸ።
እስራኤል እና ሐማስ የደረሱት የተኩስ አቁም ስምምነት በመጪው እሁድ፣ ጥር 11/2017 ዓ.ም. ተግባራዊ መሆን ይጀምራል የተባለ ሲሆን፣ እስራኤል በጋዛ እየፈጸመችው ያለው ጥቃት እንደቀጠለ ነው።
ሁለቱ ወገኖች የደረሱት የተኩስ አቁም ስምምነት ከእስራኤል በኩል የምክር ቤቱን ይሁንታ ማግኘት አለበት ተብሏል።
የተኩስ አቁም ስምምነቱ ረቡዕ፣ ጥር 7/2017 ዓ.ም. ይፋ መሆኑን ተከትሎ እስራኤል በፈጸመችው ጥቃት 73 ፍልስጤማውያን በአንድ ምሽት መገደላቸውን በሐማስ የሚተዳደረው የሲቪል መከላከያ ኤጀንሲ አስታውቋል።
ከተገደሉት መካከል በጋዛ ከተማ ሼክ ራድዋን ሰፈር በአንድ መኖሪያ ህንጻ ነዋሪ የነበሩ 12 ሰዎች እንደሚገኙበት የጋዛ የጤና ሚኒስቴር ገልጿል።
የእስራኤል መከላከያ በበኩሉ በደቡባዊ እስራኤል "የወደቀ ሚሳኤል" ማግኘቱን መጀመሪያ ላይ አስታውቆ የነበረ ቢሆንም በኋላ ግን ስህተት ነው ብሏል።
እስራኤል የተኩስ አቁም ስምምነቱ ጫፍ ላይ ደርሷል በተባለበት ወቅትም እየፈጸመችው ያለውን የአየር ጥቃት ቀጥላለች።
ዘገባው የ ቢቢሲ (BBC)
እስራኤል እና ሐማስ የደረሱት የተኩስ አቁም ስምምነት በመጪው እሁድ፣ ጥር 11/2017 ዓ.ም. ተግባራዊ መሆን ይጀምራል የተባለ ሲሆን፣ እስራኤል በጋዛ እየፈጸመችው ያለው ጥቃት እንደቀጠለ ነው።
ሁለቱ ወገኖች የደረሱት የተኩስ አቁም ስምምነት ከእስራኤል በኩል የምክር ቤቱን ይሁንታ ማግኘት አለበት ተብሏል።
የተኩስ አቁም ስምምነቱ ረቡዕ፣ ጥር 7/2017 ዓ.ም. ይፋ መሆኑን ተከትሎ እስራኤል በፈጸመችው ጥቃት 73 ፍልስጤማውያን በአንድ ምሽት መገደላቸውን በሐማስ የሚተዳደረው የሲቪል መከላከያ ኤጀንሲ አስታውቋል።
ከተገደሉት መካከል በጋዛ ከተማ ሼክ ራድዋን ሰፈር በአንድ መኖሪያ ህንጻ ነዋሪ የነበሩ 12 ሰዎች እንደሚገኙበት የጋዛ የጤና ሚኒስቴር ገልጿል።
የእስራኤል መከላከያ በበኩሉ በደቡባዊ እስራኤል "የወደቀ ሚሳኤል" ማግኘቱን መጀመሪያ ላይ አስታውቆ የነበረ ቢሆንም በኋላ ግን ስህተት ነው ብሏል።
እስራኤል የተኩስ አቁም ስምምነቱ ጫፍ ላይ ደርሷል በተባለበት ወቅትም እየፈጸመችው ያለውን የአየር ጥቃት ቀጥላለች።
ዘገባው የ ቢቢሲ (BBC)