Ethiopian Customs Clearing Agents


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


Great Interesting Stuff Here!!

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri














2023_የክፍልፋይ_ባንክ_ፈቃድ_ይመለከታል.pdf
505.9Kb
⚠አስቸኳይ

⚠Urgent

⚜አስመጪዎችና ላኪዎች አንድ የባንክ ፈቃድ ሰነድ ከአንድ ጊዜ በላይ እንዳይጠቀሙ የሚያደርግ የስርዓት ማስተካከያ ስራ ተሰርቶ ወደ ትግበራ እንዲገባ ከህዳር 10 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ የተወሰነ መሆኑን በተመለከተ ጥቅምት 10 ቀን 2016  በደብዳቤ ቁጥር 4/0151/16 ከጉምሩክ ኮሚሽን ለብሔራዊ ባንክ የተላለፈ ሠርኩላር

🏵 በተቋማችን የጉምሩክ ስነ-ስርዓት ለማስፈፀም ተግባራዊ የሆነው የኢትዮጵያ ጉምሩክ ስራ አመራር ስርዓት የተገልጋዮችን ስራ ለማቅለል ሲባል አስመጪዎችና ላኪዎች በባንክ የተፈቀደላቸውን አንድ ጠ የባንክ ፍቃድ ሰነድ እቃዎችን በተለያየ ጊዜያት እንዲያስወጡና እንዲያስገቡ በሚያስችል መልኩ መተግበሩ የሚታወቅ ቢሆንም አንዳንድ አስመጪዎችና ላኪዎች በባንክ የተፈቀደላቸውን አንድ የባንክ ሰነድ የአገርን ጥቅም በሚያሳጣና በህገ-ወጥ መንገድ እየተጠቀሙበት እንደሆነ ተረድተናል::

ስለሆነም ይህንን ህገወጥ ተግባር ለመከላከል የኢትዮጵያ ጉምሩክ ስራ አመራር ስርዓት ላይ አስመጪዎችና ላኪዎች አንድ የባንክ ፈቃድ ሰነድ ከአንድ ጊዜ በላይ እንዳይጠቀሙ የሚያደረግ የስርዓት ማስተካከያ ስራ ተሰርቶ ወደ ትግበራ እንዲገባ ከህዳር 10 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ የተወሰነ መሆኑን አውቃችሁ በዚሁ አግባብ ለባንኮች ይህንን ተግባራዊ ማድረግ የሚያስችል አቅጣጫ በብሔራዊ ባንክ በኩል እንዲሰጥ እየጠየቅን ከላይ ከተገለፀው ቀን ጀምሮ ከባንኮች ለሚሰጡ የክፍልፋይ ባንክ ፈቃድ ሰነዶች በጉምሩክ ስራ እመራር ስርዓት በኩል የማላስተናግድ መሆኑን በማለት ጉምሩክ ኮሚሽን እወቁልኝ ብሏል።






🏵የውጭ ምንዛሪ ክልከላ ውሳኔ ከመተላለፉ አስቀድሞ በተሰጠ የባንክ ፈቃድ እና የባንክ ፈቃድ ማራዘሚያ ተሸከርካሪዎች ወደ አገር እየገቡ በመሆኑ አስመጪዎች ዕቃቸውን አጠቃለው _ እንዲያስገቡ በቂ ጊዜ የተፈቀደ ቢሆንም በተፈቀደው ጊዜ አጠቃለው ባለማስገባታቸው ክልከላ የተደረገባቸው ተሸhርካሪዎች ወደ አገር እንዳይገቡ በቁጥር 4/0051/16 በቀን 11/12/2015 ውሳኔ መተላለፉ ይታወሳል፡፡

ሆኖም ውሳኔ ከመተላለፉ በፊት ወደ አገር ገብተው ትራንዚት አጠናቀው በተለያዩ ጉምሩክ ክሊራንስ ስነ-ስርዓት ሃደቶች ላይ የሚገኙ በተመላሽ ኢትዮጵያውያን ስም ተመዝግበው አገር ውስጥ የገቡ ፤ በመልቲ ሞዳል ስርዓት በመግባት ላይ እያሉ በመግቢያ በሮች የሚገኙ ተሸከርካሪዎች እና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች፣ኤምባሲዎች፣ እና መንግስታዊ መ/ቤቶች በቀጣይነት ወደ አገር የሚያስገቧቸው ተሸከርካሪዎች በጉምሩክ በኩል የሚስተናገዱበት አግባብ በግልጽ መወሰን አስፈልጓል::

1. የውጭ ምንዛሪ ክልከላ ከመደረጉ በፊት በተሰጠ የባንክ ፈቃድ፤ በባንኮች በኩል በተሰጠ ህጋዊ የባንክ ፈቃድ መጠቀሚያ ጊዜ ማራዘሚያ እና ህጋዊ ስልጣን በተሰጠው አካል በተሰጠ ፈቃድ ወደ አገር ገብተው ትራንዚት ያጠናቀቁ እና በክሊራንስ ሃደት ላይ የሚገኙ ተሸከርካሪዎች በተመለከተ አስፈላጊው ቀረጥና ታክስ ተከፍሎ ወይም አግባብ ባለው አካል በተሰጠ የቀረጥና ታክስ ነጻ ፈቃድ የጉምሩክ ስነ-ስርዓት ተፈፅሞባቸው እንዲስተናገዱ እንዲደረግ፤

2. በተመላሽ ኢትዮጵያዊ ስም አገር ውስጥ ገብተው በቅ/ጽ/ቤቶች የሚገኙ ተሸከርካሪዎች በተመለከተ በኮሚሽኑ በኩል በተደረገ ጥናት ተመላሽ ኢትዮጵያውያን ቀረጥና ታክስ ከፍለው አንድ ተሸከርካሪ ወደ አገር የማስገባትን መብት በመጠቀም ህጋዊ መብት ለሌላቸው አካላት ተሽከርካሪን ወደ አገር እያስገቡ መሆኑ ተረጋግጧል፡፡ ስለሆነም ይህ ድርጊት ህጋዊ አሰራሩን ያልተከተለ ስለሆነ በተመላሽ ኢትዮጵያዊያን ስም ተመዝግበው አገር ውስጥ የደረሱ ተሸከርካሪዎች በስማቸው የተመዘገቡ ተመላሽ ኢትዮጵያውያን በአካል እንዲቀርቡ እየተደረገ ዊዝሆልዲንግ ታክስን ጨምሮ የተሽከርካሪውን ሙሉ ቀረጥና ታክስ መክፈላቸው እንደተጠበቀ ሆኖ በተጨማሪነት የቀረጥና ታክሱን 10 በመቶ ቅጣት እንዲከፍሉ እየተደረገ እንዲስተናገዱ ተወስኗል

3. በመልቲ ሞዳል ስርዓት በመጓጓዝ ላይ ሆነው ውሳኔ በተላለፈበት ወቅት በትራንዚት ሃደት ላይ ሆነው በመግቢያ በር በሚገኙ የጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤቶች ቁጥጥር ስር የሚገኙ ተሸከርካሪዎችን በተመለከተ ወደ መዳረሻ ጣቢያ እንዲጓጓዙ ሆኖ እንደ አግባብነቱ ከላይ በተራ ቁጥር ከ1 እና 2 በተወሰነው አግባብ እንዲስተናገዱ ተወስኗል፤

4. የዓለም አቀፍ ድርጅቶች፤ ኢምባሲዎች እና በልዩ ሁኔታ በኢፌዲሪ ገንዘብ ሚኒስቴር፣ እና በጉምሩክ ኮሚሽን በህግ አግባብ በልዩ ሁኔታ ፈቃድ አግኝተው ወደ አገር ያልገቡ ተሸከርካሪዎችን በተመለከተ እገዳው የማይመለከታቸው መሆኑ ታውቆ ትራንዚት መፍቀድን ጨምሮ በቀጣይነት የጉምሩክ አገልግሎት እንዲያገኙ ተወስኗል፡




2023_ትራንዚት_ተፈቅዶላቸው_በወቅቱ_ወደ_ሀገር_ስላልገቡ_ጭነቶች_ይመለከታል.pdf
494.9Kb
⚜ትራንዚት ተፈቅዶላቸው በወቅቱ ወደ ሀገር ስላልገቡ ጭነቶች በተመለከተ

በጉምሩክ ደንብ ቁጥር 518/2014 አንቀጽ 7 ንዑስ አንቀፅ 1 እና 3  መሠረት
🏵የትራንዚት ፈቃድ ያገኙና በደንቡ በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ውስጥ ያልገቡ ዕቃዎችን ጭነው ጅቡቲ ወደብ የሚገኙ ተሽከርከርካሪዎች ያሉና በርካታ ተገልጋዮች ዕቃዎችን የማስገባት ጥያቄ እያቀረቡ በመሆናቸው የትራዚት ፈቃድ ተሰጥቶ ወደ አገር ያልገቡ ዕቃዎችን በደንቡ መሠረት ለመጨረሻ ጊዜ እልባት ለመስጠት እንዲቻል በቁጥር 4/1020/15 በሰኔ ቀን 20 ቀን 2015 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ ተ.ቁ 5 ላይ  በተጠቀሰው መሠረት አቅጣጫ ተሰጥቶበት ከተላለፈበት እስከ ሰኔ 20 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ተመዝግበው የትራንዚት ፈቃድ ያገኙ ዕቃዎችን ወደ ሀገር አስገብተው ማጠናቀቅ የሚገባቸው ቀነ ገደብ መስከረም 15 ቀን 2016 ዓ.ም የሚገባደድ በመሆኑ ቀኑ ከመድረሱ በፊት በተራዘመላቸው ጊዜ ገደብ ውስጥ ዕቃ ማስገባት ያልቻሉ የእያንዳንዱን አስመጪ መረጃን በማውጣት አስቀድመዉ ለድርጅቶቹ እንድያሳውቁና ዕቃዎቻቸውን እንዲያስገቡ እንድያደርጉ ከጉምሩክ ኮሚሽን ነሃሴ 22 ቀን 2015 በደብዳቤ ቁጥር 6.0.1/0038/16 የጉምሩክ ሥነ-ሥርዓት ለሚፈጸምባቸው ቅ/ጽ/ቤቶች የተላለፈ ሠርኩላር


N.B፡-

1. ከጉምሩክ ኮሚሽን ከዚህ በፊት ትራንዚት ተፈቅዶላቸው በወቅቱ ወደ ሀገር ስላልገቡ ጭነቶች በተመለከተ ሰኔ 20 ቀን 2015 በደብዳቤ ቁጥር 4/1020/15 የተላለፈ ሠርኩላር ለማግኘት 👉  (Transit Permit  Issues Circular Issued on June 27, 2023)👈 ይጫኑ








If Interested ......

ቀን 17/12/2015 ዓ.ም

ማስታወቂያ

በ4ኛ ዙር የጉምሩክ አስተላላፊነት ስልጠና ለወሰዳችሁ፤

በ4ኛ ዙር የአዳዲስ የጉምሩክ አስተላላፊነት ስልጠና ከወሰዳችሁ ሰልጣኞች ውስጥ ከዚህ በታች ስም ዝርዝራችሁ የተጠቀሳችሁ የተሰጣችሁን የምዘና ፈተና 75 በመቶና ከዚያ በላይ በማምጣት ያለፋችሁ በመሆኑ የሙያ ማረጋገጫ ሰርተፍኬት የተዘጋጀላችሁ ሲሆን

- ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ
- ውክልና ከሆነ በውልና ማስረጃ የተረጋገጠ ህጋዊ የውክልና ማስረጃ እንዲሁም
- ስም ዝርዝራችሁ ያለበትን ተራ ቁጥር በመያዝ

ከመስቀል አደባባይ ወደ ሳሪስ በሚወስደው መንገድ መሻለኪያ ድልድዩ ፊት ለፊት በሚገኘው የጉምሩክ ኮሚሽን ዋና መ/ቤት 8ኛ ፎቅ የደንበኞች ትምህርትና ድጋፍ ዳይሬክቶሬት በመምጣት ሰርተፍኬት መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

ስም ዝርዝራችሁ የሌለ ሰልጣኞች በዚሁ የቴሌግራም ገጽ የሚለቀቁ የተለያዩ ማስታወቂያዎችን እንድትከታተሉ እናሳስባለን፡፡

በተጨማሪም በ3ኛ ዙር የጉምሩክ አስተላላፊነት ስልጠና ተሳተፋችሁ ድጋሚ ፈተና (Re-Exam) ወስዳችሁ የማለፊያ ነጥብ ያስመዘገባችሁትን ሰልጣኞች ስም ዝርዝር በቅርብ ደንበኞች ትምህርትና ድጋፍ ዳይሬክቶሬት የቴሌግራም ገጽ የምናሳውቅ መሆኑን አውቃችሁ ማስታወቂያ እንድትከታተሉ እናሳስባለን፡፡

በጉምሩክ ኮሚሽን
የደንበኞች ትምህርትና ድጋፍ ዳይሬክቶሬት


2023_ላልተወሰነ_ጊዜ_የውጭ_ምንዛሬ_የማይፈቀድላቸው_እቃዎች_ዝርዝር.pdf
1.7Mb
⚠አስቸኳይ

⚠Urgent

ላልተወሰነ ጊዜ የውጭ ምንዛሬ የማይፈቀድላቸው እቃዎች  በተመለከተ ከጉምሩክ ኮሚሽን ነሃሴ 11 ቀን 2015 በደብዳቤ ቁጥር  4/0051/16  የተላለፈ ሠርኩላር

▶የውጭ ምንዛሪ ክልከላ የተደረገባቸው ተሸከርካሪዎች ከክልከላ በፊት የተሰጠ የቆዬ የባንክ ፈቃድን በባንኮች በኩል በማራዘም እና በስመ ተመላሽ ኢትዮጵያውያን ስም ተሸከርካሪዎች በብዛት ወደ አገር እየገቡ መሆኑን መገንዘብ ተችሏል፡፡

ስለሆነም በገንዘብ ሚኒስቴር ላልተወሰነ ጊዜ የውጭ ምንዛሪ ክልከላ የተደረገባቸው ተሽከርካሪዎች በማናቸውም አስመጪ፣ ተመላሽ ኢትዮጵያዊያን እና ሌሎች ስም በተራዘመም ይሁን በአዲስ መልክ በተሰጠ የባንክ ፈቃድ ወይም በፍራንኮ ቫሉታ የክፍያ ዘዴዎች በመልቲ ሞዳልም ይሁን በዩኒ ሞዳል ትራንስፖርት ስርዓት ወደ ሀገር ማስገባት በጥብቅ የተከለከለ መሆኑን እና ይህን ውሳኔ በመተላለፍ የውጭ ምንዛሪ ክልከላ የተደረገባቸውን ተሸከርካሪዎች ወደ ሀገር ማስገባት ወይም እንዲገቡ መፍቀድ በህግ የሚያስጠይቅ መሆኑን የጉምሩክ ኮሚሽን እወቁልኝ ብሏል።







20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.