ግሩም ምስጢር ያለው ወፍ
"ከራድዮን ወፍ ይባላል
ከራድዮን ነጭ ወፍ ሲሆን በሊቃውንት ዘንድ የታወቀ ነው። ጠቢባን በድካም ፈልገው አድነው ይይዙታል፣ የታመመ ሰው
ቢኖር ያቀርቡታል ፤ እሱም በሽተኛውን ትኩር ብሎ ያየዋል የማይድን ለሞት የቀረበ ከሆነ ፊቱን አዙሮ ይመለሳል፣ ቀኑ ገና
ከሆነ ግን አፉን ከፍቶ ከበሽተኛው አፍ እስትንፋሱን ይወስዳል፣ በልዑል እግዚአብሔር ኃይል የሰውየው ደዌ ሙሉ ለሙሉ
ወደ ወፉ በእስትንፋሱ ይተላለፋል። ሰውየው ይድናል ወፉ ይታመማል።
ፊት ነጭ የነበረው እንደ ከሰል ይጠቁራል፣ ህመም ሲሰማው ወደ አየር ይነጠቃል ሲብስበት ወደ ባህር ራሱን
ይወረውራል። በባህር 3 መዓልት 3 ሌሊት ቆይቶ ጽጉሩን መልጦ አዲስ ተክቶ፣ድኖ፣ታድሶ፣ኃያል ሆኖ ይወጣል።
ይህ ፍጥረት በዕለተ። ሃሙስ እግዚአብሔር ፈጥሮታል።
ስለምን ፈጠርው ቢሉ የወልደ እግዚአብሔር ክርስቶስን ሞትና ትንሳዔ ለማያምኑ ትምህርት ምሳሌ አብነት ይሆን ዘንድ
ሥላሴ ይህን ወፍ የማዳን ኃይል ሰተው ፈጥረውታል።
ትንታኔ፦
ከራድዮን ወፍ ---- የክርስቶስ ምሳሌ
የታመመው ሰው --- የአዳም ዘር ምሳሌ ሲሆን
ወፉ በዐይኑ መመልከቱ --- በክርስቶስ ላመነ ሁሉ ድኅነት ምህረት ማግኘቱ ምሳሌ
ወፉ መታመሙ---- ክርስቶስ ስለ እኛ በደል መታመሙ ምሳሌ።
መጥቆሩ ---- ስለእኛ ቤዛ ከኀጢአተኛ የመቆጠሩ ምሳሌ
ወፉ ወደ ላይ መውጣቱ---- ክርስቶስ ከፍ ብሎ መሰቀሉ ምሳሌ
ወፉ በባህር 3ቀን 3ሌሊት መኖሩ ----ክርስቶስ በከርሰ መቃብር 3ቀን 3 ሌሊት መቆየቱ ምሳሌ
ከራድዮን ወፍ ታድሶ ኃያል ሆኖ ከባህር መውጣቱ ---ክርስቶስ በሲዖል የነበሩ ነፍሳትን አድሶ አንጽቶ ገነት አስገብቶ፤
እርሱም ከቅድስት ድንግል ማርያም በነሣው በለበሰው ሥጋ ወደ ቀደሞ መለኮታዊ ሥልጣኑ ኃይሉ መቀመጡ ምሳሌ
ነው።
..........
እንግዲህ ምን እንላለን ሥላሴ አስቀድመው የአዳምን መበደል ሞትም እንዲመጣበት ያውቃሉና ገና ዓለም ሲፈጠር
እግዚአብሔር አንድያ ልጁን አሳልፎ ለመስጠት ዝግጁ እንደ ነበር የከራዲዮን ወፍ አፈጣጠር ምስክር ሆነን።
እግዚአብሔር ፍቅር ነው የምንለው ለዚህ ነው።
ይቆየን
ቸርነቱ ፍቅሩ ምህረቱ አይለየን
ምንጭ የሥነ ፍጥረት አንድምታ፣ መጽሐፈ አክሲማሮስ፤
>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>
ስመ ዖፍ ጥሩ ነጭ መልከ መልካም ወፍ የክርስቶስ አርኣያ የሰውነቱ አምሳል ፊላሎጎስ መጽሐፍ ተመልከት፡፡
ለዘተወልደ እምድንግል ምንተ ንብሎ ናስተማስሎ አርዌ ገዳምኑ አንበሳ ወሚመ ከራድዮን ዖፍ ጸዐዳ ንጉሠ ይሁዳ
እምዘርዐ ዳዊት ዘመጽአ (ድጓ)፡፡
"ከራድዮን ወፍ ይባላል
ከራድዮን ነጭ ወፍ ሲሆን በሊቃውንት ዘንድ የታወቀ ነው። ጠቢባን በድካም ፈልገው አድነው ይይዙታል፣ የታመመ ሰው
ቢኖር ያቀርቡታል ፤ እሱም በሽተኛውን ትኩር ብሎ ያየዋል የማይድን ለሞት የቀረበ ከሆነ ፊቱን አዙሮ ይመለሳል፣ ቀኑ ገና
ከሆነ ግን አፉን ከፍቶ ከበሽተኛው አፍ እስትንፋሱን ይወስዳል፣ በልዑል እግዚአብሔር ኃይል የሰውየው ደዌ ሙሉ ለሙሉ
ወደ ወፉ በእስትንፋሱ ይተላለፋል። ሰውየው ይድናል ወፉ ይታመማል።
ፊት ነጭ የነበረው እንደ ከሰል ይጠቁራል፣ ህመም ሲሰማው ወደ አየር ይነጠቃል ሲብስበት ወደ ባህር ራሱን
ይወረውራል። በባህር 3 መዓልት 3 ሌሊት ቆይቶ ጽጉሩን መልጦ አዲስ ተክቶ፣ድኖ፣ታድሶ፣ኃያል ሆኖ ይወጣል።
ይህ ፍጥረት በዕለተ። ሃሙስ እግዚአብሔር ፈጥሮታል።
ስለምን ፈጠርው ቢሉ የወልደ እግዚአብሔር ክርስቶስን ሞትና ትንሳዔ ለማያምኑ ትምህርት ምሳሌ አብነት ይሆን ዘንድ
ሥላሴ ይህን ወፍ የማዳን ኃይል ሰተው ፈጥረውታል።
ትንታኔ፦
ከራድዮን ወፍ ---- የክርስቶስ ምሳሌ
የታመመው ሰው --- የአዳም ዘር ምሳሌ ሲሆን
ወፉ በዐይኑ መመልከቱ --- በክርስቶስ ላመነ ሁሉ ድኅነት ምህረት ማግኘቱ ምሳሌ
ወፉ መታመሙ---- ክርስቶስ ስለ እኛ በደል መታመሙ ምሳሌ።
መጥቆሩ ---- ስለእኛ ቤዛ ከኀጢአተኛ የመቆጠሩ ምሳሌ
ወፉ ወደ ላይ መውጣቱ---- ክርስቶስ ከፍ ብሎ መሰቀሉ ምሳሌ
ወፉ በባህር 3ቀን 3ሌሊት መኖሩ ----ክርስቶስ በከርሰ መቃብር 3ቀን 3 ሌሊት መቆየቱ ምሳሌ
ከራድዮን ወፍ ታድሶ ኃያል ሆኖ ከባህር መውጣቱ ---ክርስቶስ በሲዖል የነበሩ ነፍሳትን አድሶ አንጽቶ ገነት አስገብቶ፤
እርሱም ከቅድስት ድንግል ማርያም በነሣው በለበሰው ሥጋ ወደ ቀደሞ መለኮታዊ ሥልጣኑ ኃይሉ መቀመጡ ምሳሌ
ነው።
..........
እንግዲህ ምን እንላለን ሥላሴ አስቀድመው የአዳምን መበደል ሞትም እንዲመጣበት ያውቃሉና ገና ዓለም ሲፈጠር
እግዚአብሔር አንድያ ልጁን አሳልፎ ለመስጠት ዝግጁ እንደ ነበር የከራዲዮን ወፍ አፈጣጠር ምስክር ሆነን።
እግዚአብሔር ፍቅር ነው የምንለው ለዚህ ነው።
ይቆየን
ቸርነቱ ፍቅሩ ምህረቱ አይለየን
ምንጭ የሥነ ፍጥረት አንድምታ፣ መጽሐፈ አክሲማሮስ፤
>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>
ስመ ዖፍ ጥሩ ነጭ መልከ መልካም ወፍ የክርስቶስ አርኣያ የሰውነቱ አምሳል ፊላሎጎስ መጽሐፍ ተመልከት፡፡
ለዘተወልደ እምድንግል ምንተ ንብሎ ናስተማስሎ አርዌ ገዳምኑ አንበሳ ወሚመ ከራድዮን ዖፍ ጸዐዳ ንጉሠ ይሁዳ
እምዘርዐ ዳዊት ዘመጽአ (ድጓ)፡፡