የኤርትራ ጦር ከዛላንበሳና አጎራባች ወረዳዎች ሰዎችን አግቶ እየወሰደ ነው ተባለ
የዛላ አንበሳ ከተማ ከንቲባ ብርሃነ በርሄ እንደተናገሩት ከምስራቃዊ ዞን ከአንድ መቶ በላይ ሰዎች ታግተዉ ተወስደዋል ብለዋል፡፡
ከዛላ አንበሳ 26 ሰዎች፣ ከጉለም ወረዳ 50 እንዲሁም ከኢሮፕ 28 ሰው በኤርትራ ሰራዊት እንደተወሰደ ገልፀው በዚህ ሳምንት ደግሞ ቁጥሩ መጨመሩን ተናግረዋል።
አሁን ላይ ዛላንበሳ ከተማን ጨምሮ ምስራቃዊው ዞን ሙሉ በሙሉ በኤርትራ ጦር ቁጥጥር ስር እንደሆነ የሚናገሩት የከተማዋ ከንቲባ ማህብረሰቡም ብዙ በደል እና ጥቃት እየደረሰበት ነዉ ብለዋል፡፡
የኤርትራ ጦር የአካባቢዉን ነዋሪዎቹ በአልጀርስ ስምምነት መሰረት ኤርትራዊ እንደሆኑ በመግለጽ በኃይል እንደተቆጣጠረም ተሰምቷል፡፡
የፌድራል መንግስት ምንም አይነት ትኩረት አልሰጠንም የሚሉት አቶ ብርሀነ ዳግም ጦርነት አንፈልግም ግን ደግሞ ማንነታችንን እና ህልውናችንን ሊያስከብርልን ይገባል ብወዋል።
በከተማዋ የሚገኙ መሰረተ ልማቶች በጦሩ ሙሉ በሙሉ እንደወደሙ ተነስቶ በከተማው እንዲሁም በአካባቢው ያለው ነዋሪ ለከፋ ችግር እንደተጋለጠም ተናግረዋል፡፡
ከዚህም ጋር ተያይዞ ከ30ሺ በላይ ነዋሪ ተፈናቅሎ በመቀሌ፤ በአዲግራት እንዲሁም በተለያዩ አከባቢዎች በመጠለያ ጣቢያ እንደሚገኝ አቶ ብርሀነ ነግረውኛል ሲል የዘገበው ኢትዮ ኤፍ ኤም 107·8 ነው፡፡
የዛላ አንበሳ ከተማ ከንቲባ ብርሃነ በርሄ እንደተናገሩት ከምስራቃዊ ዞን ከአንድ መቶ በላይ ሰዎች ታግተዉ ተወስደዋል ብለዋል፡፡
ከዛላ አንበሳ 26 ሰዎች፣ ከጉለም ወረዳ 50 እንዲሁም ከኢሮፕ 28 ሰው በኤርትራ ሰራዊት እንደተወሰደ ገልፀው በዚህ ሳምንት ደግሞ ቁጥሩ መጨመሩን ተናግረዋል።
አሁን ላይ ዛላንበሳ ከተማን ጨምሮ ምስራቃዊው ዞን ሙሉ በሙሉ በኤርትራ ጦር ቁጥጥር ስር እንደሆነ የሚናገሩት የከተማዋ ከንቲባ ማህብረሰቡም ብዙ በደል እና ጥቃት እየደረሰበት ነዉ ብለዋል፡፡
የኤርትራ ጦር የአካባቢዉን ነዋሪዎቹ በአልጀርስ ስምምነት መሰረት ኤርትራዊ እንደሆኑ በመግለጽ በኃይል እንደተቆጣጠረም ተሰምቷል፡፡
የፌድራል መንግስት ምንም አይነት ትኩረት አልሰጠንም የሚሉት አቶ ብርሀነ ዳግም ጦርነት አንፈልግም ግን ደግሞ ማንነታችንን እና ህልውናችንን ሊያስከብርልን ይገባል ብወዋል።
በከተማዋ የሚገኙ መሰረተ ልማቶች በጦሩ ሙሉ በሙሉ እንደወደሙ ተነስቶ በከተማው እንዲሁም በአካባቢው ያለው ነዋሪ ለከፋ ችግር እንደተጋለጠም ተናግረዋል፡፡
ከዚህም ጋር ተያይዞ ከ30ሺ በላይ ነዋሪ ተፈናቅሎ በመቀሌ፤ በአዲግራት እንዲሁም በተለያዩ አከባቢዎች በመጠለያ ጣቢያ እንደሚገኝ አቶ ብርሀነ ነግረውኛል ሲል የዘገበው ኢትዮ ኤፍ ኤም 107·8 ነው፡፡