ትራንፕ በጋዛ ጉዳይ በግብጽ ላይ ተጽእኖ ለማሳደር የህዳሴ ግድብን ጉዳይ እየተጠቀሙበት እንደሚገኙ ተገለጸ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራንፕ የጋዛ ነዋሪዎችን ከአካባቢው በማስወጣት እንደ ግብጽ ባሉ የጎረቤት ሀገራት ለማስፈር ያቀረቡትን ሀሳብ ግብጽ እንድትቀበላቸው ለማድረግ የህዳሴ ግድብን ጉዳይ እንደ መደለያ እየተጠቀሙበት እንደሚገኝ ተገለጸ።
ባሳለፍነው ሳምንት የፕሬዝዳንተ ትራንፕ ከፍተኛ ባለስልጣናት በካይሮ ተገኝተው የጋዛ ነዋሪዎችን ከአከባቢው እንዲለቁ በማድረግ በግብጽ እና ሌሎች ሀገራት ለማስፈር ባቀረቡት እቅድ ዙሪያ መምከራቸው ተጠቁሟል።
የትራንፕ አስተዳደር ባለስልጣናት በግብጽ ላይ ተጽእኖ በማሳደር እቅዱን እንዲቀበሉት ለማድረግ የህዳሴ ግድብን ጉዳይ እንደ መደለያ ማቀረባቸውን ዘኒውአረብ ድረገጽ ምንጮቹን ዋቢ በማረግ ባቀረበው ዘገባ አመላክቷል።
የአሜሪካን ከፍተኛ ባለስልጣናት በካይሮ በነበራቸው ቆይታ ከግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብደላቲ እና ከሀገሪቱ የደህንነት ቢሮ ሃላፊ ሃሰን ራሽድ ጋር “ግብጽ ከኢትዮጵያ ጋር አለመግባባት ውስጥ በገባችበት የህዳሴ ግድብ” እና "አወዛጋቢ በሆነው የጋዛ ነዋሪዎችን ማስለቀቅ” ዙሪያ መክረዋል ሲል ዘገባው አስታውቋል።
በህዳሴ ግድብ ዙሪያ በግብጽና በኢትዮጵያ መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት ለመፍታት አሜሪካ ጣልቃ የምትገባው እና የምትሳተፈው ግብጽ በጋዛ ጉዳይ የትራንፕን እቅድ የምትቀበል ከሆነ ብቻ ነው በሚል የአሜሪካ ባለስልጣናት ጉዳዩን በቅድመ ሁኔታነት ማስቀመጣቸውን ምንጮቹን ዋቢ በማድረግ ዘገባው አመላክቷል።
የግብፅ ባለስልጣናት የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የጋዛ ነዋሪዎችን ወደ ጎረቤት ሀገራት የማስፈር ዕቅድ እንዳልተቀበሉትና "ሙሉ በሙሉ ውድቅ ማድረጋቸውን" ዘገባው አሰታውቋል።
ዘገባው አዲስ ስታንዳርድ ነው
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራንፕ የጋዛ ነዋሪዎችን ከአካባቢው በማስወጣት እንደ ግብጽ ባሉ የጎረቤት ሀገራት ለማስፈር ያቀረቡትን ሀሳብ ግብጽ እንድትቀበላቸው ለማድረግ የህዳሴ ግድብን ጉዳይ እንደ መደለያ እየተጠቀሙበት እንደሚገኝ ተገለጸ።
ባሳለፍነው ሳምንት የፕሬዝዳንተ ትራንፕ ከፍተኛ ባለስልጣናት በካይሮ ተገኝተው የጋዛ ነዋሪዎችን ከአከባቢው እንዲለቁ በማድረግ በግብጽ እና ሌሎች ሀገራት ለማስፈር ባቀረቡት እቅድ ዙሪያ መምከራቸው ተጠቁሟል።
የትራንፕ አስተዳደር ባለስልጣናት በግብጽ ላይ ተጽእኖ በማሳደር እቅዱን እንዲቀበሉት ለማድረግ የህዳሴ ግድብን ጉዳይ እንደ መደለያ ማቀረባቸውን ዘኒውአረብ ድረገጽ ምንጮቹን ዋቢ በማረግ ባቀረበው ዘገባ አመላክቷል።
የአሜሪካን ከፍተኛ ባለስልጣናት በካይሮ በነበራቸው ቆይታ ከግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብደላቲ እና ከሀገሪቱ የደህንነት ቢሮ ሃላፊ ሃሰን ራሽድ ጋር “ግብጽ ከኢትዮጵያ ጋር አለመግባባት ውስጥ በገባችበት የህዳሴ ግድብ” እና "አወዛጋቢ በሆነው የጋዛ ነዋሪዎችን ማስለቀቅ” ዙሪያ መክረዋል ሲል ዘገባው አስታውቋል።
በህዳሴ ግድብ ዙሪያ በግብጽና በኢትዮጵያ መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት ለመፍታት አሜሪካ ጣልቃ የምትገባው እና የምትሳተፈው ግብጽ በጋዛ ጉዳይ የትራንፕን እቅድ የምትቀበል ከሆነ ብቻ ነው በሚል የአሜሪካ ባለስልጣናት ጉዳዩን በቅድመ ሁኔታነት ማስቀመጣቸውን ምንጮቹን ዋቢ በማድረግ ዘገባው አመላክቷል።
የግብፅ ባለስልጣናት የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የጋዛ ነዋሪዎችን ወደ ጎረቤት ሀገራት የማስፈር ዕቅድ እንዳልተቀበሉትና "ሙሉ በሙሉ ውድቅ ማድረጋቸውን" ዘገባው አሰታውቋል።
ዘገባው አዲስ ስታንዳርድ ነው