ስንክሳር አመ ፲ወ፩ ለጥር
አርኬ
ሰላምለጥምቀትከ በኍልቈ ክራማት ሠላሳ ። እምዘወለደተከ ድንግል ዘኢተአምር አበሳ ። አመ ቆምከ ዮም እግዚኦ ለዮርዳኖስ ማዕከለ ከርሣ። ለወድሶትከ ማዕበላቲሃ ተከውሳ። ወባረኩከ አናብርት ወዓሣ።
ሰላም ለጥምቀትከ በዘቦቱ ይነጽሑ ። ኃጣውአ ሰብእ ዘዘዚአሁ ። አመ ላዕሌከ እግዚኦ አእዳወ ዮሐንስ ተሰፍሑ ። ሶበ ርእዩከ ቀላያት ደንገፁ ወፈርሁ ። ማያትኒ በርእስከ ፈልሑ።
በዝንቱ በዓል ዘያሜንን ወይነ ። ወዘያረስዕ ኀዘነ ። ንዑ ንትፈሣሕ እንዘ ናረትዕ ልሳነ። ዘኢያስተርኢ ኅቡእ እስመ አስተርአየ ለነ። እሳት በላዒ አምላክነ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ቅዱስ እንጦንዮስ ሰማዕት
በዚችም ቀን ከፋርስ አገር ሰዎች ወገን የሆነ የከበረ እንጣልዮስ በሰማዕትነት ሞተ ። ይህም ቅዱስ አስቀድሞ በሮም አገር የሠራዊት አለቃ መኰንን ሆኖ ዐሥራ ዐምስት ዓመት ኖረ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን 🙏 አሜን።
አርኬ
ሰላም ለእንጣልዮስ ዘረሰየ ማኅሠሦ። ለእግዚአብሔር ጽድቆ ወሰማያዊተ ንግሦ። ጊዜያተ ሠላሰ እስከ መጠወ ነፍሶ። ድኅረ አውቀዩ ልሳኖ ወዘሐቁ ማዕሶ። ለፍጻሜ ስምዑ በሰይፍ መተርዎ ርእሶ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
አባ ወቅሪስ ገዳማዊ
በዚችም ዕለት የከበረ ተጋዳይ ለሆነ አባት አባ ወቅሪስ የእረፍቱ መታሰቢያ ነው። ይህም ቅዱስ አባት በባስልዮስ ዘንድ አደገ እርሱም ቅስና ሾመው ይህም ቅዱስ በደም ግባቱ በላሕዩ ደስ የሚል ፊቱም የሚአምር ነበር። በቀደመው ግብሩ ወጣት ሁኖ ሳለ የሹሙን ሚስት ተመኛትና እጅግም ወደዳት እርሷም ወደደችው ወደ ሌላ ቦታ ሒደው ፍላጎታቸውን ይፈጽሙ ዘንድ ተማከሩ ለዚህም ነገር ሲዘጋጁ በሕልሙ ራእይን አየ። እርሱ ታሥሮ በፍርድ አደባባይ ቁሞ ነበር ሌሎችም ብዙዎች እሥረኞች ከእርሱ ጋር አሉ ስለ በደላቸውም እያንዳንዳቸውን ይመረምሯቸው ነበር እርሱም በልቡ የታሰርኩት በምን ይሆን ባሏን ልነጥቀው ስለፈለግሁ ስለዚያች ሴት ነውን እርሱ ከስሶኝ ወደዚህ ታላቅ ግዳጅ ላይ አደረሰኝን አለ። በዚህም ነገር እየተሸበረ ሳለ በቀድሞ ወዳጁ አምሳል አንድ ሰው መጣና የታሰርከው በምንድን ነው? አለው ስለ ኃጢያቱ ስለ አፈረ ሊሰውረው ወደደ ግድ ባለውም ጊዜ እንዲህ ነገረው ወዳጄ ሆይ እገሌ ስለሚስቱ የከሰሰኝ ይመስለኛል ስለዚህም ፈርቼ እሸበራለሁ በወዳጁ አምሳል ወደርሱ የመጣው መልአክም ወዳጄ ሆይ ይህን ስራ እንዳትሰራ ወደርሱም እንዳትመለስ በቅዱስ ወንጌል ማልልኝ እኔም ዋስ እሆንሀለሁ አለው በወንጌልም ማለለት በዚያንም ጊዜ ከእንቅልፉ ነቃ ያየው ራእይም እውነት እንደሆነ አወቀ ። ስለዚህም አገሩን ትቶ ወደ እስክንድርያ ሔደ በዚያም ስሟ ኄራኒ የሚባል እግዚአብሔርን የምትፈራ አንዲት ሴት አገኘ በተነጋገሩም ጊዜ የልቡን ሁሉ ነገራት እርሷም እነዚህን ያማሩ ልብሶችህን ተው ተርታ ልብስንም ለብሰህ እግዚአብሔርን አገልግለው አለችው። ከዚያም ወደ በርሀ ሔደ ከብዙ ተጋድሎ የተነሳ ሆዱ እንደ ድንጋይ እስከ ደረቀ ድረስ ቅጠላቅጠል እየበላ ኖረ ጌታችንም ወደርሱ መጥቶ ፈወሰው። አጋንንትም ስለሚፈታተኑትና ስለሚያሰቃዩት እርሱ በጾምና አጋንንትም ስለሚፈታተኑትና ስለሚያሰቃዩት እርሱ በጾምና በጸሎት በመጋደል በክረምት ዝናብ እየወረደበት ራቁቱን ቁሞ ያድራል በበጋም በቀን የፀሐይ ትኩሳት በሌሊትም ቁር ሰማያዊ ሀብት እስከተሰጠው ድረስ መላዕክትም ወደርሱ መጥተው ሰማያዊ ኅብስትን ሰማያዊ መጠጥን ይመግቡት ነበር ። የተሰወሩ ራእዮችን ያውቅ ዘንድ ተገባው ሶስት ድርሰቶችንም ደረሰ አንዱ በበረሀ ስለሚኖሩ ሁለተኛው በአንድነት ስለሚኖር መነኮሳት ሦስትኛው ስለካህናት ነው ። በአንዲት አለትም ስሙ ቡላ የሚባል ገዳማዊ ወደርሱ መጥቶ እርስ በርሳቸው ሰላምታ ተሰጣጡ አባ ብላም እንዲህ አለው ወንድሜ ወቅሪስ ሆይ በቻህን አትሁን ጥቂት ወንድሞችን ካንተ ጋር አኑር እንጂ ያረጋጉህ ዘንድ ከሰይጣንም ጦርነት እንድትድን እንዲሁም አደረገ ።
ከዕለታትም በአንዱ ሃይማኖትን በለወጡ በአርዮስ በንስጥሮስና በማኒ አምሳል ሆነው ሦስት ሰይጣናት ወደርሱ መጥተው በሃይማኖታቸው ተከራከሩት እርሱም በቅዱሳት መጻሕፍት ቃላትና ሃይማኖታቸው በቀናች አባቶች ትምህርት ረታቸውና አሳፈራቸው ። ብዙዎችም የሆኑ ድንቆች ተአምራቶችን የሚሰራ ሆነ በአንዲትም እለት ወደ ቤተ ክርስቲያን በሔደ ጊዜ ተዘግታ አገኛት መነኮሳቱም መክፈቻ ፈልገው አላገኙም በላይዋም በአማተበ ጊዜ በሩ ተከፈተለት ። አባትህ ሞተ ብለው በነገሩት ጊዜ ዋሽታችኋል አባቴስ የማይሞት ሰማያዊ ነው አለ ተብሎ ስለርሱ የሚነገርለት ወቅሪስ ይህ ነው ዜንውም በገድሉ መጻሐፍና የአባቶች ዜና በተጻፈበት መጻሐፍ አለ ። ከዚህም በኋላ ፈጽሞ በአረጀ ጊዜ ወደ ወደደው እግዚአብሔር ሔደ ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
አርኬ
ሰላም ለወቅሪስ እንተ ርእየ በንዋም። እንዘ ውእቱ እሙረ ከዊኖ በዓውደ ምኵናን ቅውም። ሶበ ተኀይጠ ለብእሲት በስነ ላሕያ አዳም። ከመ ያድኅን ነፍሶ በአውትሮ ጸሎት ወጾም። ነዋኀ ተናከራ ለዛቲ ዓለም።
ሰላም እብል በቃለ ሐሤት ወፍሥሓ። እንዘ እጼውዕ ስመከ ሠርከ ወነግሀ። ዮሐንስ ሰባኪ ጥምቀተ ለንስሓ። ኅፅበኒ ወአንጽሐኒ እስመ አባልየ ረስሐ። በማየ ዮርዳኖስ ዘኵሎ አንጽሐ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
አምላከ ቅዱሳን በጥምቀቱ ይቀድሰን። ከበረከተ ጥምቀቱም ያድለን።
ጥር ፲፩ ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
፩.በዓለ ኤዺፋንያ
፪.ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ
፫.አቡነ ሐራ ድንግል ጻድቅ
፬.አባ ወቅሪስ ገዳማዊ
፭.አባ ዮሐንስ ሊቀ ዻዻሳት
፮.ቅዱስ እንጣልዮስ ሰማዕት
አርኬ
ሰላምለጥምቀትከ በኍልቈ ክራማት ሠላሳ ። እምዘወለደተከ ድንግል ዘኢተአምር አበሳ ። አመ ቆምከ ዮም እግዚኦ ለዮርዳኖስ ማዕከለ ከርሣ። ለወድሶትከ ማዕበላቲሃ ተከውሳ። ወባረኩከ አናብርት ወዓሣ።
ሰላም ለጥምቀትከ በዘቦቱ ይነጽሑ ። ኃጣውአ ሰብእ ዘዘዚአሁ ። አመ ላዕሌከ እግዚኦ አእዳወ ዮሐንስ ተሰፍሑ ። ሶበ ርእዩከ ቀላያት ደንገፁ ወፈርሁ ። ማያትኒ በርእስከ ፈልሑ።
በዝንቱ በዓል ዘያሜንን ወይነ ። ወዘያረስዕ ኀዘነ ። ንዑ ንትፈሣሕ እንዘ ናረትዕ ልሳነ። ዘኢያስተርኢ ኅቡእ እስመ አስተርአየ ለነ። እሳት በላዒ አምላክነ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ቅዱስ እንጦንዮስ ሰማዕት
በዚችም ቀን ከፋርስ አገር ሰዎች ወገን የሆነ የከበረ እንጣልዮስ በሰማዕትነት ሞተ ። ይህም ቅዱስ አስቀድሞ በሮም አገር የሠራዊት አለቃ መኰንን ሆኖ ዐሥራ ዐምስት ዓመት ኖረ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን 🙏 አሜን።
አርኬ
ሰላም ለእንጣልዮስ ዘረሰየ ማኅሠሦ። ለእግዚአብሔር ጽድቆ ወሰማያዊተ ንግሦ። ጊዜያተ ሠላሰ እስከ መጠወ ነፍሶ። ድኅረ አውቀዩ ልሳኖ ወዘሐቁ ማዕሶ። ለፍጻሜ ስምዑ በሰይፍ መተርዎ ርእሶ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
አባ ወቅሪስ ገዳማዊ
በዚችም ዕለት የከበረ ተጋዳይ ለሆነ አባት አባ ወቅሪስ የእረፍቱ መታሰቢያ ነው። ይህም ቅዱስ አባት በባስልዮስ ዘንድ አደገ እርሱም ቅስና ሾመው ይህም ቅዱስ በደም ግባቱ በላሕዩ ደስ የሚል ፊቱም የሚአምር ነበር። በቀደመው ግብሩ ወጣት ሁኖ ሳለ የሹሙን ሚስት ተመኛትና እጅግም ወደዳት እርሷም ወደደችው ወደ ሌላ ቦታ ሒደው ፍላጎታቸውን ይፈጽሙ ዘንድ ተማከሩ ለዚህም ነገር ሲዘጋጁ በሕልሙ ራእይን አየ። እርሱ ታሥሮ በፍርድ አደባባይ ቁሞ ነበር ሌሎችም ብዙዎች እሥረኞች ከእርሱ ጋር አሉ ስለ በደላቸውም እያንዳንዳቸውን ይመረምሯቸው ነበር እርሱም በልቡ የታሰርኩት በምን ይሆን ባሏን ልነጥቀው ስለፈለግሁ ስለዚያች ሴት ነውን እርሱ ከስሶኝ ወደዚህ ታላቅ ግዳጅ ላይ አደረሰኝን አለ። በዚህም ነገር እየተሸበረ ሳለ በቀድሞ ወዳጁ አምሳል አንድ ሰው መጣና የታሰርከው በምንድን ነው? አለው ስለ ኃጢያቱ ስለ አፈረ ሊሰውረው ወደደ ግድ ባለውም ጊዜ እንዲህ ነገረው ወዳጄ ሆይ እገሌ ስለሚስቱ የከሰሰኝ ይመስለኛል ስለዚህም ፈርቼ እሸበራለሁ በወዳጁ አምሳል ወደርሱ የመጣው መልአክም ወዳጄ ሆይ ይህን ስራ እንዳትሰራ ወደርሱም እንዳትመለስ በቅዱስ ወንጌል ማልልኝ እኔም ዋስ እሆንሀለሁ አለው በወንጌልም ማለለት በዚያንም ጊዜ ከእንቅልፉ ነቃ ያየው ራእይም እውነት እንደሆነ አወቀ ። ስለዚህም አገሩን ትቶ ወደ እስክንድርያ ሔደ በዚያም ስሟ ኄራኒ የሚባል እግዚአብሔርን የምትፈራ አንዲት ሴት አገኘ በተነጋገሩም ጊዜ የልቡን ሁሉ ነገራት እርሷም እነዚህን ያማሩ ልብሶችህን ተው ተርታ ልብስንም ለብሰህ እግዚአብሔርን አገልግለው አለችው። ከዚያም ወደ በርሀ ሔደ ከብዙ ተጋድሎ የተነሳ ሆዱ እንደ ድንጋይ እስከ ደረቀ ድረስ ቅጠላቅጠል እየበላ ኖረ ጌታችንም ወደርሱ መጥቶ ፈወሰው። አጋንንትም ስለሚፈታተኑትና ስለሚያሰቃዩት እርሱ በጾምና አጋንንትም ስለሚፈታተኑትና ስለሚያሰቃዩት እርሱ በጾምና በጸሎት በመጋደል በክረምት ዝናብ እየወረደበት ራቁቱን ቁሞ ያድራል በበጋም በቀን የፀሐይ ትኩሳት በሌሊትም ቁር ሰማያዊ ሀብት እስከተሰጠው ድረስ መላዕክትም ወደርሱ መጥተው ሰማያዊ ኅብስትን ሰማያዊ መጠጥን ይመግቡት ነበር ። የተሰወሩ ራእዮችን ያውቅ ዘንድ ተገባው ሶስት ድርሰቶችንም ደረሰ አንዱ በበረሀ ስለሚኖሩ ሁለተኛው በአንድነት ስለሚኖር መነኮሳት ሦስትኛው ስለካህናት ነው ። በአንዲት አለትም ስሙ ቡላ የሚባል ገዳማዊ ወደርሱ መጥቶ እርስ በርሳቸው ሰላምታ ተሰጣጡ አባ ብላም እንዲህ አለው ወንድሜ ወቅሪስ ሆይ በቻህን አትሁን ጥቂት ወንድሞችን ካንተ ጋር አኑር እንጂ ያረጋጉህ ዘንድ ከሰይጣንም ጦርነት እንድትድን እንዲሁም አደረገ ።
ከዕለታትም በአንዱ ሃይማኖትን በለወጡ በአርዮስ በንስጥሮስና በማኒ አምሳል ሆነው ሦስት ሰይጣናት ወደርሱ መጥተው በሃይማኖታቸው ተከራከሩት እርሱም በቅዱሳት መጻሕፍት ቃላትና ሃይማኖታቸው በቀናች አባቶች ትምህርት ረታቸውና አሳፈራቸው ። ብዙዎችም የሆኑ ድንቆች ተአምራቶችን የሚሰራ ሆነ በአንዲትም እለት ወደ ቤተ ክርስቲያን በሔደ ጊዜ ተዘግታ አገኛት መነኮሳቱም መክፈቻ ፈልገው አላገኙም በላይዋም በአማተበ ጊዜ በሩ ተከፈተለት ። አባትህ ሞተ ብለው በነገሩት ጊዜ ዋሽታችኋል አባቴስ የማይሞት ሰማያዊ ነው አለ ተብሎ ስለርሱ የሚነገርለት ወቅሪስ ይህ ነው ዜንውም በገድሉ መጻሐፍና የአባቶች ዜና በተጻፈበት መጻሐፍ አለ ። ከዚህም በኋላ ፈጽሞ በአረጀ ጊዜ ወደ ወደደው እግዚአብሔር ሔደ ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
አርኬ
ሰላም ለወቅሪስ እንተ ርእየ በንዋም። እንዘ ውእቱ እሙረ ከዊኖ በዓውደ ምኵናን ቅውም። ሶበ ተኀይጠ ለብእሲት በስነ ላሕያ አዳም። ከመ ያድኅን ነፍሶ በአውትሮ ጸሎት ወጾም። ነዋኀ ተናከራ ለዛቲ ዓለም።
ሰላም እብል በቃለ ሐሤት ወፍሥሓ። እንዘ እጼውዕ ስመከ ሠርከ ወነግሀ። ዮሐንስ ሰባኪ ጥምቀተ ለንስሓ። ኅፅበኒ ወአንጽሐኒ እስመ አባልየ ረስሐ። በማየ ዮርዳኖስ ዘኵሎ አንጽሐ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
አምላከ ቅዱሳን በጥምቀቱ ይቀድሰን። ከበረከተ ጥምቀቱም ያድለን።
ጥር ፲፩ ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
፩.በዓለ ኤዺፋንያ
፪.ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ
፫.አቡነ ሐራ ድንግል ጻድቅ
፬.አባ ወቅሪስ ገዳማዊ
፭.አባ ዮሐንስ ሊቀ ዻዻሳት
፮.ቅዱስ እንጣልዮስ ሰማዕት