ልሳነ ግእዝ ⛪️


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


📚 ከዚህ ቻናል የግእዝ ቋንቋ ይማራሉ ማጣቀሻ መጻሕፍት እንለቃለን ።

YouTube 👇👇
https://www.youtube.com/channel/UC0AbE445q7l1pDutVwpw5Ow

Ads
https://telega.io/c/geeztheancient

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri






🤳




ሰላምታ - ፪

አይቴ ውእቱ = የት ነው?

ዳዊትተክለማርያም ሀሎ = ተክለማርያም አለ?

ሰሎሞንናሁ ወጽአ እምነ ማኅደሩ =
አሁን ከቤቱ / ከማደሪያው/ ወጣ፤

ዳዊትአይቴ ዘሖረ ይመስለከ = የት የሄደ ይመስልኻል፤

ሰሎሞንኀበ ቅድስት ማርያም ውእቱ ዘሖረ = ወደ ቅድስት ማርያም ነው የሔደው።

ዳዊትዮም ቀዳሲ ውእቱ =
ዛሬ ቀዳሽ ነው።

ሰሎሞንአኮ = አይደለም፤

ዳዊትኩለሄ ቤተ ክርስቲያን ውእቱ ዘእንበለ ቤተክርስቲያን ሊሉይ ነገር ኢየአምር።
= ሁልጊዜ ቤተክርስቲያን ነው ያለቤተክርስቲያን ሌላ ነገር አያውቅም።

ሰሎሞንውእቱሰ ኀረየ መክፈልተ ሰናየ
= እሱስ መልካም እድልን መረጠ።

ዳዊትማእዜ ይትመየጥ
= መቼ ይመለሳል?

ሰሎሞንዐሠርቱ ሰዓት ይመጽእ በድኅር ነዓ አው ንስቲት ጽንዐ እስከ አሥር ሰዓት
= አሥር ሰዓት ይመጣል በኋላና ወይም ትንሽ ቆይ እስከ አሥር ሰአት።

ዳዊትኦሆ እምዝንቱ እነብር
= እሺ ከዚህ እቀመጣለሁ።

ሰሎሞንእወ በጊዜ ውእቱ ዘይበውእ ውስተ ቤቱ።
= አዎ በጊዜ ነው ወደ ቤቱ የሚገባው።

ዳዊት፦ ምንት ነሲኦ ውእቱ ዘሖረ፤ = ምን ይዞ ነው የሔደው?

ሰሎሞንመጽሐፍ ቅዱስ ወሐመር
= መጽሐፍ ቅዱስና ሐመር።

ዳዊትአንሰ አሌ ሊተ አልብየ ተስፋ።
= እኔስ ወዮልኝ ተስፋም የለኝ።

ሰሎሞንዮጊከ ዘወድቀ ይትነሳ፤ = አይዞህ የወደቀ ይነሳል።

ዳዊትወኀልቀ ዘመንየ በከንቱ፤ = ዘመኔ በከንቱ አለቀ።

ሰሎሞንኢታማስን ተስፋከ ባሕቱ ጽንአ በሃይማኖት ወግበር ሰናየ።
= ተስፋህን አታጥፋ ነገር ግን በሃይማኖትህ ጽና፤ መልካምን አድርግ።

ዳዊትይኩነኒ በከመ ትቤለኒ፤ = እንደምትለኝ ይደረግልኝ ይሁንልኝ

ሰሎሞን
አሜን፤ = ይሁን ይደረግ።



ከመምህር ደሴ ቀለብ - ትንሣኤ ግእዝ መጽሐፍ የተወሰደ።


ሰላምታ ፩


አባ = ሰላም ለከ ወልድየ
ሰላም ላንተ ይሁን ልጄ
ሰሎሞን = እግዚአብሔር ይሴባሕ፤ ወሰላም ለከ አቡየ= እግዚአብሔር ይመስገን ላንተም ሰላም አባቴ

አባ = አብያፂከ፣ ሰብአ ቤትከ ዳኅና ውእቶሙ= ጓደኞችህ፣ ቤተሰቦችህ ደህና ናቸው?

ሰሎሞን =እወ አቡየ ሎቱ ስብሐት = አወ አባቴ ለእርሱ ምስጋና
አባ = ብከኑ መጽሐፈ ጸሎት = የጸሎት መጽሐፍ አለህ?

ሰሎሞን = እወ = አወ
አባ = ልሳነ ግእዝ እፎ ውእቱ፧ የግእዝ ቋንቋ እንዴት ነው?
ሰሎሞን = ቀሊል ውእቱ፡
=ቀላል ነው

አባ = ናሁ ትትናገር ጥቀ፧
አሁን በጣም ትናገራለህ?
ሰሎሞን = ንስቲት ንስቲት፤ ትንሽ፣ትንሽ፤
አባ = ባሕቱ ምንት ይገብር ለከ፧ ነገር ግን ምን ያደርግልሃል?

ዳዊት = ይትሔደስ መንፈስየ አመ ሰማእኩ በእዝንየ ልሳነ ግእዝ። ግእዝ ቋንቋ በሰማሁ ጊዜ መንፈሴ ይታደሳል።
አባ = እንከሰ ኩሉ ሰብእ እመይትናገር ሠናይ ውእቱ። እንግዲያስ ሁሉ ሰው ቢናገረው ጥሩ ነው።
ሰሎሞን = ተስፋየ ውእቱ፤
ተስፋየ ነው
አባ = ናሁ እለመኑ ይትናገሩ ልሳነ ግእዝ። አሁን እነማን የግእዝ ቋንቋን ይናገራሉ?
ሰሎሞን = ብዙኀን ውእቶሙ አኮ አነ ባሕቲትየ። ብዙዎች ናቸው እኔ ብቻ አይደለሁም
አባ = ምንት ትቤ አንተ እንዘ ይትናገሩ ልሳነ ግእዝ። ግእዝ ሲናገሩ አንተ ምን ትላለህ?

ሰሎሞን = ፍስሐ ፈድፈደ ሊተ። ደስታ በዛልኝ።
አባ = ማእዜ ውእቱ ዘወጠኑ ለምሂርመቼ ነው ለመማር የጀመሩ?
ሰሎሞን = በዝንቱ ዓመት፤
በዚህ ዓመት
አባ = እግዚአብሔር ያርእየነ ለፍሬሁ። እግዚአብሔር ፍሬውን ያሳየን
ሰሎሞን = አሜን ለይኩን።
አሜን ይሁንልን

https://t.me/geeztheancient


ስንክሳር አመ ፲ወ፩ ለጥር

አርኬ

ሰላምለጥምቀትከ በኍልቈ ክራማት ሠላሳ ። እምዘወለደተከ ድንግል ዘኢተአምር አበሳ ። አመ ቆምከ ዮም እግዚኦ ለዮርዳኖስ ማዕከለ ከርሣ። ለወድሶትከ ማዕበላቲሃ ተከውሳ። ወባረኩከ አናብርት ወዓሣ።

ሰላም ለጥምቀትከ በዘቦቱ ይነጽሑ ። ኃጣውአ ሰብእ ዘዘዚአሁ ። አመ ላዕሌከ እግዚኦ አእዳወ ዮሐንስ ተሰፍሑ ። ሶበ ርእዩከ ቀላያት ደንገፁ ወፈርሁ ። ማያትኒ በርእስከ ፈልሑ።

በዝንቱ በዓል ዘያሜንን ወይነ ። ወዘያረስዕ ኀዘነ ። ንዑ ንትፈሣሕ እንዘ ናረትዕ ልሳነ። ዘኢያስተርኢ ኅቡእ እስመ አስተርአየ ለነ። እሳት በላዒ አምላክነ።

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ቅዱስ እንጦንዮስ ሰማዕት

በዚችም ቀን ከፋርስ አገር ሰዎች ወገን የሆነ የከበረ እንጣልዮስ በሰማዕትነት ሞተ ። ይህም ቅዱስ አስቀድሞ በሮም አገር የሠራዊት አለቃ መኰንን ሆኖ ዐሥራ ዐምስት ዓመት ኖረ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን 🙏 አሜን።

አርኬ
ሰላም ለእንጣልዮስ ዘረሰየ ማኅሠሦ። ለእግዚአብሔር ጽድቆ ወሰማያዊተ ንግሦ። ጊዜያተ ሠላሰ እስከ መጠወ ነፍሶ። ድኅረ አውቀዩ ልሳኖ ወዘሐቁ ማዕሶ። ለፍጻሜ ስምዑ በሰይፍ መተርዎ ርእሶ።

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

አባ ወቅሪስ ገዳማዊ

በዚችም ዕለት የከበረ ተጋዳይ ለሆነ አባት አባ ወቅሪስ የእረፍቱ መታሰቢያ ነው። ይህም ቅዱስ አባት በባስልዮስ ዘንድ አደገ እርሱም ቅስና ሾመው ይህም ቅዱስ በደም ግባቱ በላሕዩ ደስ የሚል ፊቱም የሚአምር ነበር። በቀደመው ግብሩ ወጣት ሁኖ ሳለ የሹሙን ሚስት ተመኛትና እጅግም ወደዳት እርሷም ወደደችው ወደ ሌላ ቦታ ሒደው ፍላጎታቸውን ይፈጽሙ ዘንድ ተማከሩ ለዚህም ነገር ሲዘጋጁ በሕልሙ ራእይን አየ። እርሱ ታሥሮ በፍርድ አደባባይ ቁሞ ነበር ሌሎችም ብዙዎች እሥረኞች ከእርሱ ጋር አሉ ስለ በደላቸውም እያንዳንዳቸውን ይመረምሯቸው ነበር እርሱም በልቡ የታሰርኩት በምን ይሆን ባሏን ልነጥቀው ስለፈለግሁ ስለዚያች ሴት ነውን እርሱ ከስሶኝ ወደዚህ ታላቅ ግዳጅ ላይ አደረሰኝን አለ። በዚህም ነገር እየተሸበረ ሳለ በቀድሞ ወዳጁ አምሳል አንድ ሰው መጣና የታሰርከው በምንድን ነው? አለው ስለ ኃጢያቱ ስለ አፈረ ሊሰውረው ወደደ ግድ ባለውም ጊዜ እንዲህ ነገረው ወዳጄ ሆይ እገሌ ስለሚስቱ የከሰሰኝ ይመስለኛል ስለዚህም ፈርቼ እሸበራለሁ በወዳጁ አምሳል ወደርሱ የመጣው መልአክም ወዳጄ ሆይ ይህን ስራ እንዳትሰራ ወደርሱም እንዳትመለስ በቅዱስ ወንጌል ማልልኝ እኔም ዋስ እሆንሀለሁ አለው በወንጌልም ማለለት በዚያንም ጊዜ ከእንቅልፉ ነቃ ያየው ራእይም እውነት እንደሆነ አወቀ ። ስለዚህም አገሩን ትቶ ወደ እስክንድርያ ሔደ በዚያም ስሟ ኄራኒ የሚባል እግዚአብሔርን የምትፈራ አንዲት ሴት አገኘ በተነጋገሩም ጊዜ የልቡን ሁሉ ነገራት እርሷም እነዚህን ያማሩ ልብሶችህን ተው ተርታ ልብስንም ለብሰህ እግዚአብሔርን አገልግለው አለችው። ከዚያም ወደ በርሀ ሔደ ከብዙ ተጋድሎ የተነሳ ሆዱ እንደ ድንጋይ እስከ ደረቀ ድረስ ቅጠላቅጠል እየበላ ኖረ ጌታችንም ወደርሱ መጥቶ ፈወሰው። አጋንንትም ስለሚፈታተኑትና ስለሚያሰቃዩት እርሱ በጾምና አጋንንትም ስለሚፈታተኑትና ስለሚያሰቃዩት እርሱ በጾምና በጸሎት በመጋደል በክረምት ዝናብ እየወረደበት ራቁቱን ቁሞ ያድራል በበጋም በቀን የፀሐይ ትኩሳት በሌሊትም ቁር ሰማያዊ ሀብት እስከተሰጠው ድረስ መላዕክትም ወደርሱ መጥተው ሰማያዊ ኅብስትን ሰማያዊ መጠጥን ይመግቡት ነበር ። የተሰወሩ ራእዮችን ያውቅ ዘንድ ተገባው ሶስት ድርሰቶችንም ደረሰ አንዱ በበረሀ ስለሚኖሩ ሁለተኛው በአንድነት ስለሚኖር መነኮሳት ሦስትኛው ስለካህናት ነው ። በአንዲት አለትም ስሙ ቡላ የሚባል ገዳማዊ ወደርሱ መጥቶ እርስ በርሳቸው ሰላምታ ተሰጣጡ አባ ብላም እንዲህ አለው ወንድሜ ወቅሪስ ሆይ በቻህን አትሁን ጥቂት ወንድሞችን ካንተ ጋር አኑር እንጂ ያረጋጉህ ዘንድ ከሰይጣንም ጦርነት እንድትድን እንዲሁም አደረገ ።
ከዕለታትም በአንዱ ሃይማኖትን በለወጡ በአርዮስ በንስጥሮስና በማኒ አምሳል ሆነው ሦስት ሰይጣናት ወደርሱ መጥተው በሃይማኖታቸው ተከራከሩት እርሱም በቅዱሳት መጻሕፍት ቃላትና ሃይማኖታቸው በቀናች አባቶች ትምህርት ረታቸውና አሳፈራቸው ። ብዙዎችም የሆኑ ድንቆች ተአምራቶችን የሚሰራ ሆነ በአንዲትም እለት ወደ ቤተ ክርስቲያን በሔደ ጊዜ ተዘግታ አገኛት መነኮሳቱም መክፈቻ ፈልገው አላገኙም በላይዋም በአማተበ ጊዜ በሩ ተከፈተለት ። አባትህ ሞተ ብለው በነገሩት ጊዜ ዋሽታችኋል አባቴስ የማይሞት ሰማያዊ ነው አለ ተብሎ ስለርሱ የሚነገርለት ወቅሪስ ይህ ነው ዜንውም በገድሉ መጻሐፍና የአባቶች ዜና በተጻፈበት መጻሐፍ አለ ። ከዚህም በኋላ ፈጽሞ በአረጀ ጊዜ ወደ ወደደው እግዚአብሔር ሔደ ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

አርኬ
ሰላም ለወቅሪስ እንተ ርእየ በንዋም። እንዘ ውእቱ እሙረ ከዊኖ በዓውደ ምኵናን ቅውም። ሶበ ተኀይጠ ለብእሲት በስነ ላሕያ አዳም። ከመ ያድኅን ነፍሶ በአውትሮ ጸሎት ወጾም። ነዋኀ ተናከራ ለዛቲ ዓለም።

ሰላም እብል በቃለ ሐሤት ወፍሥሓ። እንዘ እጼውዕ ስመከ ሠርከ ወነግሀ። ዮሐንስ ሰባኪ ጥምቀተ ለንስሓ። ኅፅበኒ ወአንጽሐኒ እስመ አባልየ ረስሐ። በማየ ዮርዳኖስ ዘኵሎ አንጽሐ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

አምላከ ቅዱሳን በጥምቀቱ ይቀድሰን። ከበረከተ ጥምቀቱም ያድለን።

ጥር ፲፩ ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
፩.በዓለ ኤዺፋንያ
፪.ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ
፫.አቡነ ሐራ ድንግል ጻድቅ
፬.አባ ወቅሪስ ገዳማዊ
፭.አባ ዮሐንስ ሊቀ ዻዻሳት
፮.ቅዱስ እንጣልዮስ ሰማዕት


ኤጲፋንያ በዘቦቱ አርአየ እግዚእ ስብሐተ መለኮቱ በውስተ ጥምቀት በቅድመ ዮሐንስ በፈለገ ዮርዳኖስ።


እንኳን አደረሳችሁ




እንቋዕ ለበዓለ ከተራ በሰላም አብጽሐክሙ/ን ❤🙏😍


🥁🪘🪈


መዝሙር ዘሰንበት

ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሖረ ኢየሱስ በትፍሥሕት ውስተ ከብካብ፤ እንዘ ይገብር ተአምረ ወመንክረ በውስተ አሕዛብ፤ ሖረ ኢየሱስ በትፍሥሕት ውስተ ከብካብ፤ አርአዮሙ ስብሐቲሁ አምኑ ቦቱ አርዳኢሁ፤ ሖረ ኢየሱስ በትፍሥሕት ውስተ ከብካብ፤ ወይቤሎሙ ቅድሑ ማየ ወምልዕዎን ለመሳብክት እስከ አፉሆን፤ ሖረ ኢየሱስ በትፍሥሕት ውስተ ከብካብ፤ ጥዒሞ አንከረ ሊቀ ምርፋቅ በረከተ ዘአምላክ ገብረ፤ ሖረ ኢየሱስ በትፍሥሕት ውስተ ከብካብ፤ ቤዛነ ተስፋነ ወልደ አምላክ፤ ወለማይኒ ረሰዮ ወይነ።


+++ ማኅሌት ዘበዓለ ጥምቀት ምስለ ዘቃና ዘገሊላ +++                                                                    
📖  ከአባቶቻችን ጋር የምስጋና ቃል ጋር አንድ ሆነን ለምስጋና እንተጋ ዘንድ፤ ለማኅሌቱም እንግዳ እንዳንሆን እነኋት እንደ ረዳት ትሆነን ዘንድ ከመጽሐፈ ዚቅ የተቀዳውን በሚከተለው ቀርቧል፡፡ መድረኩን ከማኅሌቱ ጋር ለማዋሐድም መድረክ አካባቢ ለሚያገለግሉ ነገር ግን መጽፉን ለመመልከት ላላደረሳቸውም ለማስታወስ ያህል . . .

#ዋዜማ
ሃሌ ሉያ ኃዳፌ ነፍስ ለጻድቃን ወተስፋ ቅቡጻን፤
ክርስቶስ አስተርአየ ውስተ ዓለም፤
እምድንግል ተወልደ ክሡተ ኮነ፤
እንዘ ይትዔዘዝ ለአዝማዲሁ፤
ከዊኖ ሰብአ በዮርዳኖስ ተጠምቀ ፡፡
+++
++
#በሐምስተ ++
በዮርዳኖስ ተጠምቀ ፈጺሞ ሕገ፤
ወአስተርአየ ገሃደ በዮርዳኖስ ተጠምቀ፡፡

++ እግዚአብሔር ነግሠ ++

አስተርእዮ ኮነ ዘክርስቶስ ስነ መለኮት፤
ከመ ርግብ ውስተ ምጥማቃት እንዘ ይብል ዝንቱ ውእቱ ወልድየ ዘአፈቅር ፡፡
+++
#ይትባረክ +++
ርእዩከ ማያት እግዚኦ
ርእዩከ ማያት ወፈርሁ፤
ደንገፁ ቀላያተ ማያት ወደምፀ ማያቲሆሙ፡፡

++
#ሠለስት++
አርአየነ ፈቃዶ በከመ ሥምረቱ ለአምላክነ፤
ወረደ ወተወልደ እምብእሲት፤
ወአንሶሰወ ዲበ ምድር ወአስተርአየ ከመ ሰብእ በበህቅ ልህቀ፤
በሠላሳ ክረምት በዮርዳኖስ ተጠምቀ፡፡
++
#ሰላም ++
ሃሌ ሉያ (4) በሰላም አስተርአየ ወልደ አምላክ ፍጹም፤
ወተወልደ በሀገረ ዳዊት በዮርዳኖስ ተጠምቀ ከመ ይቤዝወነ ፤
ወልደ አምላክ ፍጹም አስተርአየ፡፡
++
#ክብር ይእቲ ++
ኵሎሙ ማኅበረ መላእክቲሁ ይሴብሑ ወይዜምሩ፤
ለዘበሥጋ ሰብእ አስተርአየ ፤
ንዑ ንስግድ ሎቱ ሃሌ ሉያ፡፡

++
#ዝማሬ ++
ኅብስተ ሰማያዌ ወጽዋዓኒ ዘማየ ሕይወት፤
ጠዓሙ ወታእምሩ ከመ ኄር እግዚአብሔር በመንፈስ ቅዱስ፡፡

++# ዕጣነ ሞገር ++
ሃሌ ሉያ (2) ወደሞ ክቡረ መንፈሰ ሕይወት ወቅድሳተ መንፈስ ወሀበነ
ወማየ መንጽሔ ዚአነ፡፡
++
#ሰላም ++
ወረደ ወልድ እምሰማያት ውስተ ምጥማቃት፤
በፍሥሐ ወበሰላም፡፡

#ምልጣን
በፍሥሐ ወበሰላም፤
ወረደ ወልድ እምሰማያት ውስተ ምጥማቃት፡፡
++++

+++
#ማኅሌት +++
ሰላም ለአእዛኒክሙ አናቅጸ ጸሎት ሠናይ፤
ምሥጢራተ ሰሚዕ ሥላሴ ዘኢተልዎ ርእይ
. . . . .
ዚቅ
መኑ ይወርድ ውስተ ቀላይ ክርስቶስ ውእቱ ዘወጽአ እማይ፤
እመንፈስ ቅዱስ ሠለስቲሆሙ እለ አሐዱ እሙንቱ ሠለስቲሆሙ፤
እለ ይከውኑ ሰማዕት ሠለስቲሆሙ፤
ለሊሁ ወረደ መንፈስ ቅዱስ ከመ ይቀድስ ማያተ፤
ስቡሕኒ ውእቱ ወልዑልኒ ውእቱ ለዓለም፤
ጸጋ ወጽድቅሰ በኢየሱስ ክርስቶስ ኮነ፡፡

++
#ነግሥ ++
ሰላም ለማየ ዮርዳኖስ ዮሐንስ ዘአተቦ፤
መንፈስ ቅዱስ ከመ አጥበቦ፤
ሶበ መጽአ ቃል እምሰማይ ለተናብቦ፤
ነድ ለማየ ባሕር ከበቦ፤
ማይ ኀበ የሐውር ጸበቦ፡፡
ዚቅ
ርእዩከ ማያት እግዚኦ
ርእዩከ ማያት ወፈርሁ፤
ደንገፁ ቀላያተ ማያት ወደምፀ ማያቲሆሙ፡፡

+++
#ትምህርተ ኅቡዓት +++
እምሰማያት እም ኀበ አብ አይኅዓ፤
በሕማማተ ሥጋሁ ቤዘወነ ፤
ወደሞ ክቡረ መንፈሰ ሕይወት፤
ወቅድሳተ መንፈስ ወሀበነ፤
ወማየ መንጽሔ ዚአነ፡፡

አልቦ ዚቅ ፡- (እንደ ሚታወቀው ይህ ትምህርተ ኅቡዓት ጌታ ከትንሣኤው በኋላ ከዕርገቱ በፊት በነበሩት ፵ ቀናት ውስጥ ለሐዋርያት ያስተማረው ትምህርት ነው፡፡ ጌታ ባስተማረው ትምህርት ላይ ተጨማሪ ማብራሪያ መስጠት አይገባም በሚል ዕሳቤ ትምህርተ ኅቡዓት በሚቆምበት ወቅት ዚቅ እንዳይኖረው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ደንግገዋል። )

++
#ምልጣን ++
ክርስቶስ ተወልደ ክርስቶስ ተጠምቀ፤
ወለደነ ዳግመ እማይ ወእመንፈስ ቅዱስ፤
እሙነ ኮነ ለፀሐየ ጽድቅ አስተርእዮቱ፤
አማን መንክር ስብሐተ ጥምቀቱ፡፡
++ እስመ ለዓለም ++
ሖረ ኢየሱስ እምገሊላ ኀበ ዮሐንስ ፤
ከመ ያጥምቆ በፈለገ ዮርዳኖስ፤
ወወጺኦ እማይ ተርኅወ ሰማይ፤
መጽአ ቃል እምደመና ዘይብል ዝንቱ ውእቱ ወልድየ ዘአፈቅር ሎቱ ስምዕዎ፡፡

++
#ዕዝል ++
ቀዳሚሁ ቃል ውእቱ ቃል ቃለ እግዚአብሔር፤
ውእቱ ቃል ሥጋ ኮነ ወተገሠ በሥጋ መንፈስ ዘኢይትገሠሥ፤
ወዘኢይትለከፍ ዘመልዕልተ ሰማያት ዘመልዕልተ ሥልጣናት
ወገብረ መንጦላዕተ ፡ ሥጋ ሰብእ መዋቲ
ወረደ ዲበ ምድር ወአንሶሰወ ውተ ዓለም
በበሕቅ ልሕቀ በሠላሳ ክረምት በዮርዳኖስ ተጠምቀ፡፡

++
#ምልጣን ዘዕዝል ++
ዘመልዕልተ ሰማያት ዘመልዕልተ ሥልጣናት
ወገብረ መንጦላዕተ ፡ ሥጋ ሰብእ መዋቲ ፡፡
++
#አቡን ++
ሃሌ ሉያ (5) እስመ ስምዓ ይቀውም ሎቱ አብ ናዛዜ፤
በርእየተ ርግብ ውስተ ምጥማቃት እንዘ ይብል ዝንቱ ውእቱ ወልድየ ዘአፈቅር
ዘኪያሁ ሠመርኩ ይቤ፤ ወለይእቲ ሥጋ እንተ ነሥአ መድኅን እምቅድስት ድንግል
ኪያሃ ሠምረ አብ በሥጋ ምጽአቶ፡፡
++
#ሰላም ++
ዮም ፍስሐ ኮነ በእንተ ልደቱ ለክርስቶስ ወበእንተ ጥምቀቱ፤
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ኃዲጎ ተስዓ ወተስዓተ ነገደ፤
ቆመ ማእከለ ባሕር ገብአ ወወጽአ በሰላም፡፡

+++++++++++++++++++++++++++++++
#ዘቃና ጥር 12
ሥላሴክሙ ሥላሴ ይረስየኒ መካነ፤
ድኅረ ተዋሐድኩሰ ዘሥላሴሁ ብርሃነ፤
ዮርዳኖሰክሙ ዝየ እስመ ኵለንታየ ኮነ፤
ኢየኃሥሥ እምዮርዳኖስ ሰማዕተክሙ ምእመነ ፤
ወኢይትሜነዮ ለታቦር እስመ ታቦር አነ፡፡
ዚቅ
ነአምን በአብ ወነአምን በወልድ ወነአምን በመንፈስ ቅዱስ ፤
እማርያም ዘተወልደ አፍቂሮ ኪያነ መጽ ኀቤነ ዘነቢያት ሰበኩ ለነ፤
በዮርዳኖስ ተጠምቀ ከመ ይፈጽም ኵሎ ሕገ ወአስተርአየ ገሃደ፡፡

++ #መልክዐ ሚካኤል ++
ሰላም ለአጽፋረ እግርከ ፍናዋተ ረድኤት በተኃልፎ፤
ዘኢተዳደቆን እብነ አዕቅፎ፤
ሚካኤል ቀዳሲ ትሥልስተ አካላት በኢያዕርፎ፤
ኢትኅድገኒ በዓለም እስመ ኪያከ እሴፎ፤
አልቦ እምሰብእ ዘየኀድግ ሱታፎ፡፡
ዚቅ
ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ዘበተዋህዶ ይሴለስ
እምኀበ አብ ትጉሃን ይትቄደስ
እሳተ ሕይወት ዘኢይተገሠሥ ወኢይጤየቅ ለዓይን ረቂቅ መንፈስ
ንሰግድ ለትሥልስቱ አሐተ ስግደተ ወሎቱ ናቄርብ ስብሐታተ፡፡


©Aleph ቴሌግራም ቻናል ላይ የተወሰደ።


እንቋዕ አብጽሐክሙ/ን ውሉደ ኢትዮጵያ።


የጊዜ አመልካቾች

ትካት፣ ዐለም - ድሮ፣ ጥንት፣ ቀድሞ - Old times
ዘልፍ ወትር፣ ዘልፈ ወትረ - ወትሮ፣ ዘወትር ያለማቋረጥ
ለዝሉፍ፣ ለዝላፋ - ለወትሮ፣ ለዘወትር፣ ለዘላለም
ቅድም፣ ትማልም - መጀመሪያ - In the Beginning
ትማልም - ትላንት - Yesterday
ቅድመ ትማልም - ከትናንት በስቲያ/ወዲያ - Before yesterday
ዮም፣ ይእዜ - ዛሬ፣ አሁን፣ ዘንድሮ - Today, Now, This year
ናሁ - አሁን - Now
ጌሠም፣ ሳኒታ - ነገ፣ ነገታ፣ ማግስት - Tomorrrow
ድኅረ ጌሠም - ከነገ በስቲያ - After tomorrow
ቅድመ ዝ ዐመት - ከዚህ ዓመት በፊት - Before this year/last year
ዘዮም ዐመት - የዛሬ ዓመት - Year after now/next year
ሣምንት - ሣምንት - week
ዘልፈ፣ ወትረ - ዘወትር - Every day
ለለ/በበ ዕለቱ - ዕየለቱ - Every day
ዋሕድ ዋሕድ ጊዜ - አልፎ አልፎ - Some times
ወርኅ - ወር - Month
ዘዮም ወርኅ - የዛሬ ወር - A month before or after now
ዐመት - ዓመት - Year
ዕለት፣ መዐልት - ቀን - Day
ጽባሕ - ጧት - Morning
ቀትር - ቀትር - After noon
ክ.ዘመን - ክ.ዘመን - Century
ሺሕ - ሺሕ - Millenuiem
መንፈቀ ሌሊት - የሌሊት ግማሽ - Mid night
ቀዳማይ መንፈቅ - የመጀመሪያ ወሰን - First Semester
ካልኣይ ወሰን - የኹለተኛው ወሰን - Second semester


#ልሳነ #ግእዝ #Ge'ez #Language

ገቢር ተገብሮ = አድራጊ ተደራጊ / Direct and indirect Object/

✍️ ገቢር/ አድራጊ /፣ ተገብሮ /ተደራጊ/ ማለት የማይሸጋገሩትንና የሚሸጋገሩትን ግሶች የምንለይበት ሰዋስዋዊ ሙያ ነው፡፡

የሚሻገሩ ግሶች /Transitive Verbs /፦ ማለት ከባለቤቱ ወይም ከድርጊት ፈጻሚው ድርጊቱን በማሳለፍ በድርጊት መፈጸሚያው ላይ ማረፉን የሚያመለክቱ ግሶች ናቸው።
ለምሳሌ፦ አበበ አንበሳ ገደለ፤ ብንል "ገደለ" የሚለው ግስ አበበ የተባለው የዐረፍተ ነገሩ ባለቤት በአንበሳው ላይ ድርጊት መፈጸሙን የሚጠቁም ስለሆነ ነው። ነገር ግን አንበሳ ተገደለ ብንል ድርጊቱ እዚያው አንበሳው ላይ ብቻ መቅረቱን እንጂ ከማን ወደ ማን መኼዱን የሚያመለክት አይኾንም።

የማይሻገሩ ግሶች /Interansitive Verbs በተገብሮ/ passive ይነገራሉ። ነባር አንቀጽና የማለት አንቀጾች የማይሻገሩ አንቀጾች ናቸው።

ገቢር/ተሻጋሪ----ተገብሮ/የማይሻገሩ

አቅረበ - አቀረበ ------ ሞተ - ሞተ
ጸፋአ - መታ ------- ነበረ - ተቀመጠ
ሰበረ - ሰበረ -------- ሖረ - ኼደ
አኀዘ - ያዘ -------- ቆመ - ቆመ
አንበረ -አስቀመጠ
አጥረየ - ገዛ

✍️ ተሻጋሪ ግስ ያለበት ቃል ተሳቢን ያስከትላል።

ምሳሌ
የማይሳቡ - Indirect ☑️ የሚሳቡ - Direct ☑️
እምከ - እናትኽ እመከ - እናትኽን
እምኪ - እናትሺ እመኪ - እናትሽን
ወልድከ - ልጅኽ ወልደከ - ልጅኽን


✍️ ተሻጋሪ ግሶች
ምሳሌ፣ ቀተለ/ገደለ/፣ ቀደሰ / አመሰገነ/፣ በልሀ /በላ/ እናም ሲተረጎም “ን” የሚለውን ትርጉም ያመጣል፡፡
ረከብነ ሕይወተ = ሕይወት አገኘን ሲሆን በግእዝ ግን
ተረክበ ሕይወተ = ሕይወት ተገኘ ቢል ግን አይለውጥም /ስሕተት የለበትም/ ምክንያቱም ተረክበ ተቀተለ እና የመሳሰሉት ተገብሮ/ የማይሻገሩ ናቸውና፡፡

ምሳሌ
ባለቤት /ተገብሮ/ (subject)

ዝ ቤት ሐዲስ ውእቱ -- ይህ ቤት አዲስ ነው፤
ተወልደ ለነ -- ተወለደልን
ተሰቅለ ለነ -- ተሰቀለልን
ሖረ ኀበ ገዳም -- ወደ ገዳም ኼደ።

ተሰብረት ሐመርየ ውስተ ባሕር - መርከቤ በባሕር ውስጥ ተሰበረች።

ቀረብከ አንተ ኀበ እሳት - ወደ እሳት ቀረብክ።
መጽአ ብየ ከይሲ - እባብ መጣብኝ
እነዚህ ከላይ ያየናቸው የማይስቡ/የማይሻገሩ ናቸው።

✍️ ተሳቢ / ገቢር/ (direct object)

ምሳሌ
ወልድየ ሐነፀ ቤተ = ልጄ ቤትን ሠራ፤
ወለደት ወልደ ማርያም -- ማርያም ልጅን ወለደች፤
አንተ ሰበርከ ሐመረ - አንተ መርከብን ሰበርክ።
አቅረበ ለነ ማየ - ውኃን አቀረበልን።
መኑ ሰቀለ ወልደኪ፧ -- ልጅሽን ማን ሰቀለው?
አነ ቀተልኩ ከይሴ - እባብን ገደልኩ፤
ከላይ ያየናቸው የሚስቡ/ የሚሻገሩ ናቸው።

📖 ለማጠቃለል የሚከተሉት ሕግና ሥርዓት አሉት።

1. ከላይ እንዳየነው የመጨረሻው ሳድስ ፊደል ወደ ግእዝ ይለወጣል፡፡
ቤት = ቤተ ይሆናል፡፡

2. ካእብ ወደ ሳብእ ይለወጣል፡፡ ኩሉ= ኩሎ ይሆናል፡፡
ወሖረ ኩሉ ኀበ ቤቱ - ሁሉ ወደ ቤቱ ሄደ።
እግዚአብሔር ያፈቅር ኩ - እግዚአብሔር ሁሉ ይወዳል።

3. ሳልስ ወደ ኀምስ ይለወጣል፡፡ ብእ--- ብእ
ዊ=ዌ ይሆናል፡፡

☑️ ተገብሮ =ብእሲ ሖረ ኀበ ሐቅል
☑️ገቢር =ርኢኩ ብእሴ ውስተ ቤተ

☑️ ተገብሮ = አቤሜሌክ ኢትዮጵያዊ ውእቱ።

☑️ ገቢር = ወባረከ እግዚአብሔር ውእተ ኢትዮጵያዌ - እግዚአብሔር ኢትዮጵያዊውን ባረከ።

4. የተጸውኦ ስሞች
ምሳሌ ሲጨምር፡፡
ሙሴ = ሙሴሃ ይሆናል።



ተለውነ ✍️
https://t.me/geeztheancient


ትእዛዝ፡፵ወ፰ ።
በእንተ፡ዘኢይጸውም፡ጾመ፡አርብዓ፡ወረቡዕ፡ወዐርብ። ኤጲስ፡ቆጶስ፡አው፡ቀሲስ፡አው፡ዲያቆን፡አው፡አናጕንስጢስ፡አው፡መዘምር፡ለእመ፡ኢጾመ ፡ አርብዓ ፡ ቅዱሰ፡ወረቡዕ፡ ወዐርበ፡ይሰዐር፡ለእመ፡ኢከልኦ፡ሕማም፡ዘሥጋ። ወለእመ፡ኮነ፡ሕ ዝባዊ፡ይሰደድ።

ትእዛዝ፡፵ወ፱ ። ለእመ ፡ ጾመ ፡ ኤጲስ፡ ቆጶስ፡ አው፡ቀሲስ፡ አው፡ዲያቆን፡ አው፡፩እምሥዩማን፡ምስለ ፡አይሁድ፡ወይገብር፡ ፋሲካ፡ምስሌሆሙ፡አው፡ይትወከፍ፡በኀቤሆሙ፡አምኃ፡በዓሎሙ፡ ናእተ፡አው፡ዘይመስሎ፡ይሰዐር፤ ወለእመ ኮነ፡ሕዝባዊ፡ይሰደድ። ሕዝባዊ፡ለእመ፡ወሰደ፡ኀበ፡ምኵራበ ፡ አሕዛብ ፡ ወምኵራበ ፡ አይሁድ፡ቅብአ፡ወማኅቶተ፡ይሰደድ።


ትእዛዘ ሐዋርያት
ገጽ ፳፪


ዝ መጽሐፈ ግእዝ ጥቀ ሠናይ ውእቱ




ብራና መጻሕፍት dan repost
Ethiopian_Geez_1300_ca_Krestos_Gospels_Illuminated_WDL_13018.pdf
74.4Mb
ከነጮቹ ዌቭሳይት የተገኘ ነው።
እዚህ ይቀመጥ።

https://t.me/BiranaEthio


ስንክሳር ዘወርኀ ጥር ፯

አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥር ሰባት በዚች ቀን የከበረ አባት የሮሜ ሀገር ሊቀ ጳጳሳት ሶል ጴጥሮስ አረፈ። ይህንንም አባት ስለ ተጋድሎው ገናናነት ስለ አገልግሎቱም ስለ ትሩፋቱ ስለ አዋቂነቱና ስለ ደግነቱ ከእርሱ በፊት የነበረ ሊቀ ጳጳሳት አባ መልጥያኖስ ከአረፈ በኋላ መርጠው ሊቀ ጵጵስና በሮሜ ሀገር ላይ ሾሙት ። በሐዋርያት አለቃ በጴጥሮስ ወንበር በተቀመጠ ጊዜ የዕሌኒ ልጅ የሆነ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስን የክርስትና ጥምቀትን አጠመቀው ከከሀድያን ጋር ስለሚያደርገው ጦርነት ምክንያት ገና አልተጠመቀም ነበርና የጣዖታትንም ቤቶች አፍርሶ የእግዚአብሔርን አብያተ ክርስቲያናት ሠራቸው። የዚህም አባት የሶል ጴጥሮስ ገድሉ እጅግ ብሩህ የሆነ ነው እርሱ ሁል ጊዜ ሕዝቡን ያስተምራቸዋልና ከልቡናቸውም ከሰይጣን የሆነ ጥርጥርንና ክፉ ሐሳብን ያርቃል። ከእነርሳቸው ሥውር የሆነውንም የመጻሕፍት ምሥጢር ተርጕሞ ያስገነዝባቸዋል። አይሁድንና ዮናናውያንን ሁል ጊዜ ይከራከራቸው ነበር ከእርሳቸውም ብዙዎችን መልሶ ወደ ቀናች ሃይማኖት አስገባቸው የክርስትና ጥምቀትንም አጠመቃቸው ስሙም በምእመናን ዘንድ ፈጽሞ የሚያስፈራ እግዚአብሔርን ስለ ማወቅና ስለ ወልደ እግዚአብሔር ሰው መሆን ብዙ ድርሳናትን ደረሰ። በተሾመ በሰባተኛውም ዓመት ስለ አርዮስ በኒቅያ ከተማ ሃይማኖታቸው የቀና የሦስት መቶ ዐሥራ ስምንት የከበሩ አባቶች የአንድነት ስብሰባ ሆነ ይህም አባት ሶል ጴጥሮስ ከእርሳቸው አንዱ ነበር አርዮስንም ከተከታዮቹ ጋር ረገመው አውግዞም ለየው በሹመቱም ዐሥራ አንድ ዓመት ኖረ መልካም ተጋድሎውን ፈጽሞ እግዚአብሔርንም አገልግሎ በሰላም አረፈ።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

አርኬ
ሰላም ለከ ጴጥሮስ ሶል። መጥምቀ ቈስጠንጢኖስ ንጉሥ ከሣቴ መስቀል። መዋዕለ ዕብሬትከ ኮነ ዕብሬተ ርትዕ ወሣህል። እስመ ተቀጥቀጠ ዳጎን ወወድቀ ቤል። በከመ ቀዳሜ ኢሳይያስ ይብል።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
በዚችም ዕለት የቅዱስ ኤፍሬም መታሰቢያው ነው፤ በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን ።

አርኬ

ሰላም ለከ ኤፍሬም አብ።
ምሉአ ጥበብ ። ፈሪሆተ ክርስቶስ ምልአኒ ከመ ማህየብ። በአልባቢሆሙ ለዘይፈርህዎ ሕዝብ። እስመ አድኀኖቱ ተብህለ ለአምላክ ቅሩብ።


፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

በዚችም ቀን የሰሎሞን የጎርጎርዮስ የማርቆስ የአትያኖስ የሉያ የመልይን የሱስዮስ የማርትይ መታሰቢያቸው ነው። በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን አሜን ።

ጥር ፯ ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት


፩.በዓለ ሥሉስ ቅዱስ
፪.ቅዱስ ሶል ዼጥሮስ
፫.ቅዱስ ኤፍሬም
፬.ቅዱስ ሰሎሞን

ወርኀዊ በዓላት
፩.አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
፪.አባ ሲኖዳ (የባሕታውያን አለቃ) ፫.አባ ዳንኤል ዘገዳመ ሲሐት ፬.አባ ባውላ ገዳማዊ
፭.ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ፮.ቅዱስ አግናጥዮስ (ለአንበሳ የተሰጠ)

የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ: የእግዚአብሔርም ፍቅር: የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን ። አሜን ። (፪ኛ ቆሮ. ፲፫፥፲፬)


አመ፮ ለጥር ስንክሳር

አርኬ

ሰላም ለግዝረትከ በመዋዕል ሰሙን። ከመ ትፈጽም ለሊከ ሥርዓተ ኪዳን። እንተ ወሀብከ እግዚኦ አመ ቀዳሚ ዘመን። ግዝረተ መጥባሕት ለወልደ ታራ ምእመን። ወበዕብነ እዝኅ ለአውሴ መስፍን።


አርኬ

ሰላም እብል ለኖኅ በሕቁ። ምስለ ብእሲቱ ወደቂቁ። በገቢረ ታቦት ላዕሌሁ እለ ተሣለቁ። በዝናመ ድምሳሴ ወበማየ አይኅ ኀልቁ። ውእቱሰ አምሠጠ በጽድቁ።


አርኬ
ሰላም ለኤልያስ እንዘ ይነብር በደብር። ሶበ ይቤሎ ላእከ ንጉሥ ኅሱር። ነዓ ፍጡነ ነቢየ እግዚአብሔር። ለእመ አነ ነቢየ አምላክ ክቡር ። እሳተ ሰማይ ወሪዳ ታውዒከ በምድር።

አርኬ
ሰላም ለወርክያኑ ሳምናይ በፍቅድ። እምኍልቈ ጳጳሳት ኄራን ዘይብልዎሙ አዕማድ። አረማውያነ ይሚጥ እምፍኖተ ካህድ። ወያብዕል ክርስቲያነ በጸጋ ፍድፋድ ። ሀብተ መንፈስ ቅዱስ አድምዐ ዘነሥአ እምወልድ።

አርኬ
ሰላም እብል ብእሴ ኅዳፈ። ዘየአምር ምሳሌ ወሥዋሬ ነገር ዘተርፈ። ስእለተ አሐቲ ብእሲት ሶበ ባስልዮስ ተወክፈ። ደምሰሰ በሕይወቱ ዘኃጣውኢሃ መጽሐፈ። ወድኅረ ሞቱ አሐደ ዘተርፈ።

በዚችም ቀን በበረሀ ስልሳ ዘመናት የኖረ አባ ሙሴ አረፈ ። እርሱም የቅዱሳንን ልቡና ከማየቱ የተነሣ አደነቀ ፊቱም ተለውጦ እንደ እሳት ፍም ሆነ በረከቱም ከእኛ ጋር ትሁን ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን አሜን ።

አርኬ


ሰላም ለሙሴ ዘነበረ ገዳመ ። ስሳ አክራመ ። በዛቲ ዕለት እንዘ ይነውም ንዋመ። እስከ እምርእዮቱ አልባበ ቅዱሳን ተደመ ። ወተውላጠ ገጹ እንተ ኮነ ፍሕመ።

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.