Immigration And Citizenship Service (ICS Ethiopia)


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


This is the official channel of the FDRE Immigration and Citizenship Services

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri




አዲስ አበባ ያመለከታችሁ ደንበኞቻችን ስም ዝርዝር የለቀቅን ስለሆነ ስምዎን እና ያመለከቱበትን ቅርንጫፍ ወይም ስምዎን እና የትራኪንግ ቁጥርዎን በቴሌግራም ቦታችን @ICSPassportBot ወይም በድረ-ገፅ አማራጭ passport.ics.gov.et ላይ በማስገባት ማየት የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን በስም መነሻ ፊደል ቀናችሁ መሰረት በመገኘት ፓስፖርታችሁን እንድትወሰዱና ወደ ተቋማችን ስትመጡ ኦንላይን ያመለከታችሁበትን ፕሪንት አውት ይዛችሁ እንድትመጡ እናሳስባለን።

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት

——

Telegram: https://t.me/ICS_Ethiopia
Facebook: https://www.facebook.com/ICSEthiopia
Twitter: https://twitter.com/ics_ethiopia
TikTok: https://www.tiktok.com/@ics_ethiopia
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/icsethiopia
YouTube: https://www.youtube.com/@Ics_Ethiopia
Instagram: https://www.instagram.com/icsethiopia/


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዬች ቋሚ ኮሚቴ በጥቁር አንበሳ እና በጐተራ የሚገኘውን የአገልግሎትን ቢሮ ጉብኝት እና ተጨማሪ ጉዳዮች አስመልክተው በኢቲቪ የሰጡት ማብራሪያ

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት
——
Telegram: https://t.me/ICS_Ethiopia
Facebook: https://www.facebook.com/ICSEthiopia
Twitter: https://twitter.com/ics_ethiopia
TikTok: https://www.tiktok.com/@ics_ethiopia
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/icsethiopia
YouTube: https://www.youtube.com/@Ics_Ethiopia
Instagram: https://www.instagram.com/icsethiopia/


የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሲቪልና የቤተሰብ ምዝገባ ስርዓት አዋጅን አጸደቀ።

አዲስ አበባ፤ጥር 29/2017 ዓ.ም

ምክር ቤቱ 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 18ኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል።

በዚሁ ጊዜ ምክር ቤቱ የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሲቪልና የቤተሰብ ምዝገባ ስርዓትን ለመወሰን የወጣውን ረቂቅ አዋጅ አስመልክቶ ያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ አድምጧል።

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ዲማ ነጎ (ዶ/ር)፥ የሲቪልና የቤተሰብ ምዝገባ የመንግስት አገልግሎቶችን ለማቀላጠፍና የዜጎችን የወሳኝ ኩነቶች መረጃ በተደራጀ መልኩ ለመያዝ ያስችላል ብለዋል።

በአግባቡና በወቅቱ የተመዘገቡ ወሳኝ ኩነቶችና የቤተሰብ ምዝገባ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ የልማት ዕቅዶችን በማሳካት ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ሚናቸው የላቀ መሆኑንም ጠቁመዋል።

ከዚህ አኳያ የሲቪልና የቤተሰብ ምዝገባ አዋጅ ከኢትዮጵያውያን ባለፈ ነዋሪነታቸውን በኢትዮጵያ ያደረጉ የውጭ አገር ዜጎች እንዲመዘገቡና የተሻለ የደህንነት ጥበቃ እንዲኖር እንደሚያስችልም ነው ያነሱት።

አዋጁ የሚመለከታቸው አካላት በህግ በሚሰጣቸው ስልጣንና ሃላፊነት መሰረት በቅንጅት እንዲሰሩ ዕድል ይፈጥራል ብለዋል።

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት በበኩላቸው፥ ቀደም ሲል በነበረው አዋጅ የሲቪል ምዝገባው በአግባቡና በተደራጀ መልኩ ባለመቀመጡ በጉዞና በተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ክፍተት ፈጥሯል ብለዋል።

በሌሎች አገሮች የተጠናከረ የሲቪልና የቤተሰብ ምዝገባ በመኖሩ አገልግሎቶችን ፈጣንና ቀልጣፋ ማድረግ ማስቻሉንም ጠቅሰዋል።

ልደትና ጋብቻን ጨምሮ ወሳኝ ኩነቶችን በአግባቡ መዘግቦ መያዝ ለሀገር የልማት ፖሊሲ ዝግጅትና ክለሳ ወሳኝ ነው ብለዋል።

አዋጁ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች በሚደረጉ የሲቪልና የቤተሰብ ምዝገባዎች በቴክኖሎጂ ታግዘው በተናበበ መልኩ እንዲሆን አጋዥ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

(ኢዜአ)

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት
--
Telegram: https://t.me/ICS_Ethiopia
Facebook: https://www.facebook.com/ICSEthiopia
Twitter: https://twitter.com/ics_ethiopia
TikTok: https://www.tiktok.com/@ics_ethiopia
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/icsethiopia
YouTube: https://www.youtube.com/@Ics_Ethiopia


የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የአገልግሎት አሰጣጡን የበለጠ ለማዘመን የጀመራቸው ሥራዎች አበረታች መሆናቸው ተገለጸ፡፡

ጥር 28 ፣2017 ዓ.ም.

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የአገልግሎት አሰጣጡን የበለጠ ለማዘመን የጀመራቸው ሥራዎች አበረታች መሆናቸውን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዬች ቋሚ ኮሚቴ ገልጿል።

ቋሚ ኮሚቴው በጥቁር አንበሳ እና በጐተራ የሚገኘውን የአገልግሎቱን ቢሮ የጐበኘ ሲሆን በተለይ በጐተራ የሚሰጠው አገልግሎት እጅግ ዘመናዊ የሆነ፣ በአንድ መስኮት በርካታ አገልግሎቶችን ማግኘት የሚቻልበት እድልን የፈጠረ ነው ብለዋል፡፡

የቋሚ ኮሚቴው ተቋሙ ከዚህ በፊት በርካታ ችግሮች ያሉበት እንደነበረ ገልፆ የለውጡ አመራር ችግሮቹን ለመፍታት የሄደበት ርቀት እና አገልግሎቱን በዘመናዊ ቴክኖሎጅ በማዘመን ለህ/ሠቡ ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ያለው ስራ የሚያስደንቅ ነው ብለዋል፡፡

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት በበኩላቸው እየሰራን ያለውን ስራ፣ እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችን እና እየፈታን ያለንበትን መንገድ ማየታችሁ ለምናደርገው የኮሙኒኬሽን ስራ ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡

አክለውም ተቋሙ በርካታ ውስብስብ ችግሮች የነበሩበት ተቋም የነበረ መሆኑን ገልፀው አሁን ላይ የሪፎርም አጀንዳዎችን በመቅረጽና እጃችን ላይ ያሉትን ችግሮች ደግሞ በፍጥነት በመፍታት ከሰው ሀይል፣ ከበጀት፣ ከቴክኖሎጅ አኳያ እያሻሻልን መጠናል ብለዋል፡፡

አገልግሎቱን ተደራሽ ለማድረግም በተለያዩ ቦታዎች ላይ ቅ/ጽ/ቤት ለመክፈት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች የተጠናቀቁ መሆኑንና 1000 የሚሆኑ ሰራተኞችን ለመቅጠር በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ምዝገባ በማድረግ ለቅጥር ሂደት ላይ መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡

የቋሚ ኮሚቴው ም/ሰብሳቢ ዶ/ር ፈትሂ ማህዲ በበኩላቸው የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ለዜጐች በርካታ አገልግሎቶችን የሚሰጥ ተቋም እንደመሆኑ ባለፉት አመታት በርካታ ቅሬታዎች የሚነሳበት ተቋም የነበረ መሆኑንና አሁን ላይ ግን ምቹ የስራ አካባቢ ለመፍጠር ፣ አገልግሎቱን የተቀላጠፈ ለማድረግ፣ ቴክኖሎጅን ለመጠቀም የሄደበት ርቀት የሚያበረታታ መሆኑን ገልፀው አዲሱን ኢ ፖስፖርት ለመስጠት ከሀገሪቱና ከዜጐች ፍላጐት አንፃር በፍጥነት ወደ ትግበራ እንዲገባ አሳስበዋል፡፡

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት
--
Telegram: https://t.me/ICS_Ethiopia
Facebook: https://www.facebook.com/ICSEthiopia
Twitter: https://twitter.com/ics_ethiopia
TikTok: https://www.tiktok.com/@ics_ethiopia
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/icsethiopia
YouTube: https://www.youtube.com/@Ics_Ethiopia




አዲስ አበባ እና ደሴ ያመለከታችሁ ደንበኞቻችን ስም ዝርዝር የለቀቅን ስለሆነ ስምዎን እና ያመለከቱበትን ቅርንጫፍ ወይም ስምዎን እና የትራኪንግ ቁጥርዎን በቴሌግራም ቦታችን @ICSPassportBot ወይም በድረ-ገፅ አማራጭ passport.ics.gov.et ላይ በማስገባት ማየት የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን ጽ/ቤቶቹ በሚያወጡት ኘሮግራም መሰረት በመገኘት ፓስፖርታችሁን እንድትወሰወዱና ወደ ተቋማችን ስትመጡ ኦንላይን ያመለከታችሁበትን ፕሪንት አውት ይዛችሁ እንድትመጡ እናሳስባለን።

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት

——

Telegram: https://t.me/ICS_Ethiopia
Facebook: https://www.facebook.com/ICSEthiopia
Twitter: https://twitter.com/ics_ethiopia
TikTok: https://www.tiktok.com/@ics_ethiopia
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/icsethiopia
YouTube: https://www.youtube.com/@Ics_Ethiopia
Instagram: https://www.instagram.com/icsethiopia/


ኢትዮጵያ ከስደትና ከስደት ተመላሾች ጋር በተያያዘ እያከናነች ያለችውን ጥረት ኔዘርላንድ እንደምትደግፍ አስታወቀች

ኢትዮጵያ ከስደትና ከስደት ተመላሾች ጋር በተያያዘ እያከናነች ያለችውን ጥረት ኔዘርላንድ እንደምትደግፍ የአገሪቱ የፍትህና ደህነነት ሚኒስቴር የአለማቀፍ ጉዳዮች ዳይሬክተር የሆኑት ሮብ ቫን ባህሆቨን ገልፀዋል።

የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት በዋና ዳይሬክተሩ የተመራን የኔዘርላንድ ፍትህና ደህንነት ሚኒስቴር ልዑክ በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። ዋና ዳይሬክተሯ
በዚህ ወቅትም ኢትዮጵያ ስደትና ከስደት ተመላሾች ጋር በተያያዘ እያከናወነች ያለችውን ተግባር በሚመለከትና በቀጣይ ከኔዘርላንድ ጋር በዘርፉ ያለን ትብብር ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ለልዑኩ ገለፃ አድርገዋል።ከዚህ በተጨማሪም ተቋሙ በሪፎርም ሂደት ላይ መሆኑን እና የሚሰጡ አገልግሎቶችን በዘመናዊ ቴክኖሎጅ ለማደራጀት በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ለልዑኩ አስረድተዋል፡፡

ሮብ ቫን በበኩላቸው ኢትዮጵያ ስደትና ከስደት ተመላሾችን በሚመለከት እያከናወነች ያለችውን ስራ እንደሚያደንቁ ገለፀው አገራቸው በዚህ ረገድ ኢትዮጵያን ለመደገፍ ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል።

ሁለቱ አካላት በተለይም በአቅም ግንባታ ዘርፍ ላይ ተቋሙ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ይበልጥ ቀልጣፋ ከማድረግ አኳያ በጋራ ሊሰሩ በሚገቡ ጉዳዬች ላይ ውይይት አካሂደዋል፡፡

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት

--
Telegram: https://t.me/ICS_Ethiopia
Facebook: https://www.facebook.com/ICSEthiopia
Twitter: https://twitter.com/ics_ethiopia
TikTok: https://www.tiktok.com/@ics_ethiopia
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/icsethiopia
YouTube: https://www.youtube.com/@Ics_Ethiopia



9 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.