ስዊድን በኢሚግሬሽን የአቅም ግንባታ ዘርፍ ኢትዮጵያን ለመደገፍ ፍላጎት እንዳላት አስታወቀች፡፡
ስዊድን የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎትን በአቅም ግንባታ ዘርፍ ለመደገፍ ፍላጐት እንዳላት በኢትዮጵያ የስዊድን አምባሳደር ሃንስ ሄንሪክ ሉንድኩዊስት አስታውቀዋል፡፡
አምባሳደሩ ይሄን ያሉት የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት አምባሳደር ሃንስ ሄንሪክ ሉንድኩዊስት፣ ርብካ ሳሻድ ከፍትህ ዲፖርትመንት እና ማሊን ኩልማር ስደት ተመላሾች ኃላፊን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው ባነጋገሩበት ወቅት ነው።
ዋና ዳይሬክተሯ ተቋሙ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ይበልጥ ቀልጣፋ ከማድረግ አኳያ ኢትዮጵያ እና ስዊዲን በአቅም ግንባታ ዘርፍ በጋራ ሊሰሩ በሚገቡ ጉዳዬች ላይ እንዲሁም ኢትዮጵያ ስደትና ከስደት ተመላሾች ጋር በተያያዘ እያከናወነች ያለችውን ተግባር በሚመለከት አብራርተዋል።
አምባሳደር ሃንስ ሄንሪክ ሉንድኩዊስት በበኩላቸው ኢትዮጵያ ስደትና ከስደት ተመላሾችን በሚመለከት እያከናወነች ያለችውን ስራ እንደሚያደንቁ ገልፀው በዘርፉ ኢትዮጵያን ለመደገፍ አገራቸው ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል ። አክለውም ለተቋሙ ሰራተኞች የአቅም ግንባታ ስልጠና ለመስጠት ፍላጐት እንዳላቸው ገልፀዋል፡፡
ኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት
Telegram:
https://t.me/ICS_EthiopiaFacebook:
https://www.facebook.com/ICSEthiopiaTwitter:
https://twitter.com/ics_ethiopiaTikTok:
https://www.tiktok.com/@ics_ethiopiaYouTube:
https://www.youtube.com/@Ics_Ethiopia