file number 24 2482.09 Diriba Gela.pdf
ለህዝብ ጥቅም በሚል ለእምነት ተቋም የግለሰብ መሬት መሰጠት የሌለበት ስለመሆኑ፤ የሚሰጥ ከሆነም ተገቢው ካሳ መከፈል ያለበት ስለመሆኑ፡፡
በፌዴራልም ሆነ በኦሮሚያ ክልል የገጠር መሬት አዋጅ መሰረት የአንድን አርሶ አደር የእርሻ መሬት ለህዝብ ጥቅም በሚል ሰበብ መሬቱን በሙሉ ወስዶ ለእምነት ተቋም አንዲሰጥ የሚፈቅድ የህግ ድንጋጌ የለም፡፡ የገጠር መሬትን ከግለሰብ አርሶ አደር ወስዶ ለእምነት ተቋም መስጠት ለህዝብ ጥቅም አንደተሰጠ መሬት አይቆጠርም፡፡ መሬቱ ለህዝብ ጥቅም የተወሰደ ነው የሚባል ከሆነም በሕጉ አግባብ ተተኪ መሬት እና ካሳ ሊከፈል ይገባል በማለት የፌዴሬሽን ምክር ቤት በመዝገብ ቁጥር 98/13 ላይ የሕገ መንግስት ትርጉም ውሳኔ ሰጥቷል፡፡
በፌዴራልም ሆነ በኦሮሚያ ክልል የገጠር መሬት አዋጅ መሰረት የአንድን አርሶ አደር የእርሻ መሬት ለህዝብ ጥቅም በሚል ሰበብ መሬቱን በሙሉ ወስዶ ለእምነት ተቋም አንዲሰጥ የሚፈቅድ የህግ ድንጋጌ የለም፡፡ የገጠር መሬትን ከግለሰብ አርሶ አደር ወስዶ ለእምነት ተቋም መስጠት ለህዝብ ጥቅም አንደተሰጠ መሬት አይቆጠርም፡፡ መሬቱ ለህዝብ ጥቅም የተወሰደ ነው የሚባል ከሆነም በሕጉ አግባብ ተተኪ መሬት እና ካሳ ሊከፈል ይገባል በማለት የፌዴሬሽን ምክር ቤት በመዝገብ ቁጥር 98/13 ላይ የሕገ መንግስት ትርጉም ውሳኔ ሰጥቷል፡፡