♱ ባለ ማኅተቦቹ ♱


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Din


✝️ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን እንኳን ወደ ባለማዕተቦቹ የተዋሕዶ ልጆች ቻናል በሰላም መጣችሁ

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
Din
Statistika
Postlar filtri


🎬 ምን አይነት የኦርቶዶክስ መንፈሳዊ ፊልም መመልከት ይፈልጋሉ❓️

'https://t.me/addlist/6GhqHrWjTU03M2Vk' rel='nofollow'>
🎬   JOIN አዳምና ሔዋን ሙሉ ፊልም 👈 ይንኩ

🎬   JOIN የኢየሱስ ክርስቶስ ፊልም 👈 ይንኩ

🎬   JOIN አቡነ ተክለሃይማኖት ፊልም 👈 ይንኩ

🎬     JOIN ጠቢቡ ሰለሞን ፊልም 👈 ይንኩ

🎬      JOIN የሃያል ሳምሶን ሙሉ ፊልም 👈 ይንኩ

🎬    JOIN የአባ ጳውሊ መንፈሳዊ ፊልም 👈 ይንኩ

🎬    JOIN ቅድስት አርሴማ ሙሉ ፊልም 👈 ይንኩ

🎬     JOIN ሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ ፊልም 👈 ይንኩ

🎬     JOIN የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ፊልም 👈 ይንኩ

🎬    JOIN የነብዩ ቅዱስ ሙሴ ፊልም 👈 ይንኩ

🎬  JOIN  አባ ኖብ ሙሉ መንፈሳዊ ፊልም 👈 ይንኩ


✅ እንደ ምርጫው መርጠው ይ🀄️ላ🀄️ሉ ✅
ማኅቶት Wave ለመቀላቀል
t.me/Makda25


💍💍 የጋብቻ ወቅት እንደመሆኑ የሠርግ መዝሙራትን ከግጥምና ከ ዜማቸው ጋር ማግኘት ከፈለጉ ይቀላቀሉን

https://t.me/+4spyK-uT0MkyZmZk






✟ ጋሜል- ዘ ኦርቶዶክስ ✟ dan repost
"ጌታ ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያው ከውኃ ወጣ። እነሆም ሰማያት ተከፈቱ። የእግዚአብሔርም መንፈስ እንደ ርግብ ሲወርድ፡ በእርሱ ላይም ሲመጣ አየ። እነሆም ድምጽ ከሰማያት መጥቶ:- 'በእርሱ ደስ የሚለኝ፡ የምወደው ልጄ ይህ ነው' አለ።"
(ማቴ. ፫፥፲፮)





🕊 🕊
🕊
🕊
🕊 መልካም የጥምቀት በዓል ይሁንልን! 🕊


✟ ጋሜል- ዘ ኦርቶዶክስ ✟ dan repost
​​​​
🌷እንኳን ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!!



🥀 ጥር 10 ከተራ 🥀
===============


➡️ ከተራ ምንድን ነው? ከተራ 'ከበበ' ካለው የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡ ፍችው ውኃ መከተር፣ መገደብ ማለት ነው፡፡


➡️ በጥምቀት ዋዜማ ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውኃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰቡ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ድንኳን ይተከላሉ፡፡ ድንኳንም ከሌለ ዳስ ሲጥሉ ይውላሉ፡፡ የምንጮች ውኃ እንዲጠራቀም ይከተራሉ (ይገድባሉ) ጉድጓድ እየተቆፈረ ውኃው እንዳይሄድ በመገደብ ለመጠመቂያ (ለጥር 11) ዝግጁ የሚያደርጉበት ዕለት ነው፡፡

➡️ በተጨማሪ በአቅራቢያ የሚገኙት ቤተክርስቲያናት ተሰብስበው ከዚሁ ከተቆፈረው ገንዳ ወይም ከተገደበው ጅረት አጠገብ ባለው ዳስ ወይም ድንኳን ታቦቶቻቸውን ያሳድራሉ ሊቃውንቱም በዚያው እግዚአብሔርን በማህሌት ሲያመሰግኑ ያድራሉ።

➡️ በበዓለ ጥምቀት የታቦታቱ ወደ ወንዝ መውረድ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ በእደ ዮሐንስ ለመጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ በዋዜማው የመሄዱ ምሳሌ ነው፡፡ ታቦቱ የጌታችን፣ ምሳሌ ሲሆኑ ካህናቱ የመጥምቁ ዮሐንስ ምሳሌ ናቸው፡፡ መዘምራኑና ሕዝቡ ደግሞ ዮሐንስ ያጠመቃቸው ሕዝቦች ምሳሌዎች ናቸው፡፡

🌺 መልካም በዓል 🌺

💚@maedot_ze_orthodox
💛@maedot_ze_orthodox
❤️@maedot_ze_orthodox


✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
#ጥር_7_ቀን_በቅዳሴ_ሰዓት_የሚነበቡት_መልእክታት👇
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
ቆላስይስ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁰ ለአለቅነትና ለሥልጣንም ሁሉ ራስ በሆነ በእርሱ ሆናችሁ ተሞልታችኋል።
¹¹ የሥጋንም ሰውነት በመገፈፍ፥ በክርስቶስ መገረዝ፥ በእጅ ባልተደረገ መገረዝ በእርሱ ሆናችሁ ደግሞ ተገረዛችሁ፤
¹² በጥምቀትም ከእርሱ ጋር ተቀብራችሁ፥ በጥምቀት ደግሞ፥ ከሙታን ባስነሣው በእግዚአብሔር አሠራር በማመናችሁ፥ ከእርሱ ጋር ተነሣችሁ።
¹³ እናንተም በበደላችሁና ሥጋችሁን ባለመገረዝ ሙታን በሆናችሁ ጊዜ፥ ከእርሱ ጋር ሕይወትን ሰጣችሁ፤ በደላችሁን ሁሉ ይቅር አላችሁ፤
¹⁴ በእኛ ላይ የነበረውን የሚቃወመንንም በትእዛዛት የተጻፈውን የዕዳ ጽሕፈት ደመሰሰው፤ እርሱንም በመስቀል ጠርቆ ከመንገድ አስወግዶታል፤
¹⁵ አለቅነትንና ሥልጣናትን ገፎ፥ ድል በመንሣት በእርሱ እያዞራቸው በግልጥ አሳያቸው።
¹⁶ እንግዲህ በመብል ወይም በመጠጥ ወይም ስለ በዓል ወይም ስለ ወር መባቻ ወይም ስለ ሰንበት ማንም አይፍረድባችሁ፤
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
1ኛ ዮሐንስ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁵ እርሱም የሰጠን ተስፋ ይህ የዘላለም ሕይወት ነው።
²⁶ ስለሚያስቱአችሁ ሰዎች ይህን ጽፌላችኋለሁ።
²⁷ እናንተስ ከእርሱ የተቀበላችሁት ቅባት በእናንተ ይኖራል፥ ማንም ሊያስተምራችሁ አያስፈልጋችሁም፤ ነገር ግን የእርሱ ቅባት ስለ ሁሉ እንደሚያስተምራችሁ፥ እውነተኛም እንደ ሆነ ውሸትም እንዳልሆነ፥ እናንተንም እንዳስተማራችሁ፥ በእርሱ ኑሩ።
²⁸ አሁንም፥ ልጆች ሆይ፥ በሚገለጥበት ጊዜ እምነት እንዲሆንልን በመምጣቱም በእርሱ ፊት እንዳናፍር በእርሱ ኑሩ።
²⁹ ጻድቅ እንደ ሆነ ካወቃችሁ ጽድቅን የሚያደርግ ሁሉ ከእርሱ እንደ ተወለደ እወቁ።
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
ሐዋርያት 22
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁷ በምድርም ላይ ወድቄ፦ ሳውል ሳውል፥ ስለ ምን ታሳድደኛለህ? የሚለኝን ድምፅ ሰማሁ።
⁸ እኔም መልሼ፦ ጌታ ሆይ፥ አንተ ማን ነህ? አልሁ። እርሱም፦ አንተ የምታሳድደኝ የናዝሬቱ ኢየሱስ እኔ ነኝ አለኝ።
⁹ ከእኔ ጋር የነበሩትም ብርሃኑን አይተው ፈሩ፥ የሚናገረኝን የእርሱን ድምፅ ግን አልሰሙም።
¹⁰ ጌታ ሆይ፥ ምን ላድርግ? አልሁት። ጌታም፦ ተነሥተህ ወደ ደማስቆ ሂድና ታደርገው ዘንድ ስለ ታዘዘው ሁሉን በዚያ ይነግሩሃል አለኝ።
¹¹ ከዚያ ብርሃንም ክብር የተነሣ ማየት ባይሆንልኝ ከእኔ ጋር የነበሩት ሰዎች እጄን ይዘው እየመሩኝ ወደ ደማስቆ ደረስሁ።
¹² በዚያም የኖሩት አይሁድ ሁሉ የመሰከሩለት እንደ ሕጉም በጸሎት የተጋ ሐናንያ የሚሉት አንድ ሰው ነበረ።
¹³ እርሱም ወደ እኔ መጥቶ በአጠገቤም ቆሞ፦ ወንድሜ ሳውል ሆይ፥ እይ አለኝ። እኔም ያን ጊዜውን ወደ እርሱ አየሁ።
¹⁴ እርሱም አለኝ፦ የአባቶቻችን አምላክ ፈቃዱን ታውቅ ዘንድና ጻድቁን ታይ ዘንድ ከአፉም ድምፅን ትሰማ ዘንድ አስቀድሞ መርጦሃል
¹⁵ ባየኸውና በሰማኸው በሰው ሁሉ ፊት ምስክር ትሆንለታለህና።
¹⁶ አሁንስ ለምን ትዘገያለህ? ተነሣና ስሙን እየጠራህ ተጠመቅ ከኃጢአትህም ታጠብ።
¹⁷ ወደ ኢየሩሳሌምም ከተመለሱ በኋላ በመቅደስ ስጸልይ ተመስጦ መጣብኝ፥
¹⁸ እርሱም፦ ፍጠን ከኢየሩሳሌምም ቶሎ ውጣ፥ ስለ እኔ የምትመሰክረውን አይቀበሉህምና ሲለኝ አየሁት።
¹⁹ እኔም፦ ጌታ ሆይ፥ በአንተ የሚያምኑትን በምኵራብ ሁሉ እኔ በወኅኒ አገባና እደበድብ እንደ ነበርሁ እነርሱ ያውቃሉ፤
²⁰ የሰማዕትህንም የእስጢፋኖስን ደም ባፈሰሱ ጊዜ፥ ራሴ ደግሞ በአጠገባቸው ስቆም ተስማምቼ የገዳዮችን ልብስ እጠብቅ ነበር አልሁ።
²¹ እርሱም፦ ሂድ፥ እኔ ወደ አሕዛብ ከዚህ ወደ ሩቅ እልክሃለሁና አለኝ።
²² እስከዚህም ቃል ድረስ ይሰሙት ነበር፥ ድምፃቸውንም ከፍ አድርገው፦ እንደዚህ ያለውን ሰው ከምድር አስወግደው፥ በሕይወት ይኖር ዘንድ አይገባውምና አሉ።
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️

#ጥር_7_ቀን_በቅዳሴ_ሰዓት_የሚነበበው_የሚዜመው_የቅዳሴ_ምስባክ👇

✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
"የሐዩ ወይሁብዎ እምወርቀ ዓረብ። ወዘልፈ ይጼልዩ በእንቲአሁ። ወኵሎ አሚረ ይድኅርዎ። መዝ.71÷15
“እርሱ ይኖራል ከዓረብም ወርቅ ይሰጡታል፤ ሁልጊዜም ወደ እርሱ ይጸልያሉ፥ ዘወትርም ይባርኩታል።"መዝ.71÷15
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️

#ጥር_7_ቀን_የእለቱን_ወንጌል_እናንብብ📖👇
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
ማቴዎስ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²¹ እርሱም ተነሥቶ ሕፃኑንና እናቱን ያዘና ወደ እስራኤል አገር ገባ።
²² በአባቱም በሄሮድስ ፈንታ አርኬላዎስ በይሁዳ እንደ ነገሠ በሰማ ጊዜ፥ ወደዚያ መሄድን ፈራ፤ በሕልምም ተረድቶ ወደ ገሊላ አገር ሄደ፤
²³ በነቢያት፦ ናዝራዊ ይባላል የተባለው ይፈጸም ዘንድ፥ ናዝሬት ወደምትባል ከተማ መጥቶ ኖረ።
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
የሚቀደሰው ቅዳሴ #እግዚእነ ነው። መልካም የ #ቅድስት_ሥላሴ በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️


✞ የመዝሙር ግጥሞች ✞ dan repost
🌺እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ግዝረት በሰላም አደረሰን ለእኛ ሲል ሁሉን የሆነ መድኃኒታችን ክርስቶስ ለፍቅሩና ለክብሩ ያብቃን:: ከበረከተ በዓለ ግዝረቱም አይለየን::






🌺 መልካም በዓለ 🌺


እንኳን #ለጌታችን_ለመድኃኒታችን_ለኢየሱስ_ክርስቶስ_ለልደቱ_መታሰቢያ_ሁለተኛ_ሳምንት_ዕለተ_ሰንበት እግዚአብሔር አምላክ በሰላም ጤና አደረሰን።

#የዚህ_ሳምንት_መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ "#ይሠርቅ_ኮከብ_እምያዕቆብ ወየዐትት ኀጢአተ እም፳ኤል #ወአነሂ_በኵርየ_እሬስዮ ልዑል ውእቱ እምነገሥተ ምድር ወይከውን ምስማከ ለኵሉ ምድር ውስተ አርዕስተ አድባር #ዮምሰ_በሰማያት_ይትፌሥሑ_ሠራዊተ_መላእክት"። ትርጉም፦ #ከያዕቆብ_ኮከብ_ይወጣል፤ ከእስራኤል ኀጢአትን ያስወግዳል፤ #እኔም_በኩሬ_አደርገዋለሁ ከምድር ነገሥታት በላይ ታላቅ ነው፤ ለምድር ሁሉ በተራሮች ራሶች ላይ ምስባክ ይሆናል #ዛሬም_በሰማያት_የመላእክት_ሠራዊት_ደስ_ይላቸዋል። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በድጓው_ላይ።


✟ ጋሜል- ዘ ኦርቶዶክስ ✟ dan repost
​​💗✞ የፍቅር ሐዋርያ ✞💗
==================


⛪️ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ዮሐንስን 'የፍቅር ሐዋርያ' ትለዋለች። ለ70 ዘመናት በቆየ ስብከቱ ስለ ፍቅር ብዙ አስተምሯል። ፍቅርንም በተግባር አስተምሯል። በየደቂቃውም "ደቂቅየ ተፋቀሩ በበይናቲክሙ ልጆቼ ሆይ! እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ" እያለ ይሰብክ ነበር።


➦​ በተለይ ደግሞ ከፈጣሪው ክርስቶስ ጋር የነበረው ፍቅር ፍጹም የተለየ ነበር። በዚህ ምክንያትም ጌታ ባረገ ጊዜ እንዲህ ብሎታል:- "ለፍጡር ከሚገለጥ ምሥጢር ከአንተ የምሠውረው የለኝም" ብሎታል።

➦​ ቀጥሎም በንጹሕ አፉ ስሞታል። ሊቁ:-
"ሰላም ለአፉከ ለዮሐንስ ዘሰዓሞ:
ንጽሐ ኅሊናሁ ወልቡ ለዐይነ ፍትወትከ ሶበ አደሞ" እንዳለው። (መልክዐ ኢየሱስ)

➦​ ቅዱስ ዮሐንስ ከእመቤታችንም ጋር ልዩ ፍቅር ነበረው። እርሷ እንደ ልጇ ስትወደው: እርሱ ደግሞ እንደ እናቱ ልቡ እስኪነድ ድረስ ይወዳት ነበር:: እስከ እግረ መስቀሉ ድረስ ተከትሎ ያገኛት እመቤቱ ናትና።

➦​ ከዚያ ሁሉ ጸጋና ማዕረግ የመድረሱ ምሥጢርም ድንግል ናት። ለ15 ዓመታት በጽላሎተ ረድኤቷ (በረዳትነቷ ጥላ) ተደግፎ አብሯት ሲኖር ብዙ ተምሯል ከመላእክትም በላይ ከብሯል። ከንጽሕናዋ በረከትም ተካፍሏል።

✝️ ስለ ድንግል ማርያምም "ነገረ ማርያም" የሚል ድርሰት ሲኖረው "የሰኔ ጐልጐታንም" የጻፈው እርሱ ነው።


➦​ ድንግል ባረፈችበት ቀንም ልክ እንደ ልጇ ክርስቶስ እርሷም ስማው: ታቅፋው ዐርፋለች። ሊቃውንቱ ለዚህ አይደል በንጹሕ ከንፈሮቿ መሳምን (መባረክን) ሲሹ "በከመ ሰዓምኪ ርዕሰ ዮሐንስ ቀዳሚ: ስዒሞትየ ማርያም ድግሚ" ያሉት።

➦​ ታላቁ ቅዱስ ሐዋርያ ዕድሜው 90 ዓመት በሆነው ጊዜ በዚህች ዕለት ተሰውሯል። ከዚያ አስቀድሞም የዓለምን ፍጻሜ ተመልክቷል። ዛሬ ያለበትን የየሚያውቅ ቸር ፈጣሪው ነው።

💠 እናት ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ዮሐንስን ስትጠራው እንዲሕ ነው።

✨ወንጌላዊ
✨ሐዋርያ
✨ሰማዕት ዘእንበለ ደም
✨አቡቀለምሲስ (ምሥጢራትን ያየ)
✨ታኦሎጐስ (ነባቤ መለኮት)
✨ወልደ ነጐድጉዋድ
✨ደቀ መለኮት ወምሥጢር
✨ፍቁረ እግዚእ
✨ርዕሰ ደናግል (የደናግል አለቃ)
✨ቁጹረ ገጽ
✨ዘረፈቀ ውስተ ሕጽኑ ለኢየሱስ (ከጌታ ጎን የሚቀመጥ)
✨ንስር ሠራሪ ልዑለ ስብከት
✨ምድራዊው መልዐክ
✨ዓምደ ብርሐን
✨ሐዋርያ ትንቢት
✨ቀርነ ቤተ ክርስቲያን
✨ኮከበ ከዋክብት



💠 በቅዱስ ዮሐንስ ላይ ያደረ የእመቤታችን ድንግል ማርያምና የአንድ ልጇ ፍቅር በእኛም ላይ ይደር።



መልካም የገና በዓል
💚@maedot_ze_orthodox
💛@maedot_ze_orthodox
❤️@maedot_ze_orthodox


በፈተና ወድቀህ እንደሆነ ፤ የኃጢአተኝነት(የጥፍተኝነት) ስሜት ከመጸለይ እንቅፋት እንዲሆንብህ አትፍቀድለት።
ንስሓ እስክገባ ብለህ መጸለይን ካቆምክ፤ መቼም ቢሆን ንስሓ አትገባም። ጸሎት ወደ እውነተኛ ንስሐ መግቢያ በር ናትና።

✍️ምክረ አበው🥰


'' ስለ ምን ቸር ትለኛለህ? ''

'' ኢየሱስም፡— ስለ ምን ቸር ትለኛለህ? ከአንዱ ከእግዚአብሔር በቀር ቸር ማንም የለም።''
- ማርቆስ 10:18 -

ይህንን ቃል የተናገረው ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። አንዳንድ ወገኖች ይህንን ቃል በመጥቀስ ኢየሱስ ክርስቶስ ቸር አይደለም ፤ ቸር እግዚአብሔር ብቻ ነው ፥ ስለዚህ እርሱ እግዚአብሔር አይደለም ( ሎቱ ስብሐት) ይላሉ።

ኢየሱስ ክርስቶስ ቸር እግዚአብሔር እንደሆነ ምንም ጥርጥርም የለው። እንኳን ጌታችን፤ ብዙ ሰዎችም ሳይቀር ቸር ተብለዋል...እኛ ቸሮች እንድንሆንም ታዘናል።

🌿 '' ከቸር ሰው ጋር ቸር ሆነህ ትገኛለህ፤ ከቅን ሰው ጋር ቅን ሆነህ ትገኛለህ፤'' (መዝ 17:25)

🌿 '' ቸር ሰው ይራራል ያበድራልም፥ በፍርድም ነገሩን ይፈጽማል።'' ( መዝ 110:5)

🙌 የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት ሰው እንኳ ከሚሰራው ሥራ አንዱ የቸርነት ሥራ ነው።

'' የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ ትዕግሥት፥ ቸርነት፥ በጎነት፥ እምነት፣'' (ገላ 5:22)

እንዲህ ከሆነ የጌታችን ንግግር እንዴት ይታያል?

ጌታችን ልብንና ኩላሊትን የሚመረምር
አምላክ ነውና በሰዎች ልቡና ያለውን ተንኮልና ቀናነት በራሱ ስለሚያውቅ ( ዮሐ 1፡49 ፣ ዮሐ 4፡18 ) የዚህንም ሰው የልቡን ሐሳብ አወቀ። ይህ ሰው በልቡ የኢየሱስን እግዚአብሔርነት ሳያምን እንዲሁ በአፉ #ቸር_መምህር-ሆይ ብሎ የተጠራው። ጌታችንም ከእግዚአብሔር በቀር ሰው በባሕርዩ ቸር ሊባል አይገባውም አለው ( ቅዱሳን ቸር ቢባሉ በጸጋ ነውና)

ጌታችንን ቸር ያለው ሰው እርሱ ክርስቶስ እግዚአብሔር አምላክ እንደሆነ ሳያውቅ - ሳያምን ነበርና እንዲሁ ቸር ብሎ የጠራው።

ስለዚህ አምላክነቴን እግዚአብሔርነቴን ሳታውቅ ሳትረዳ ስለምን ቸር ትለኛለህ? አምላክነቴን ተረድተህ ቸር በለኝ። ከእግዚአብሔር( ከእኔ) በቀር ቸር ማንም የለምና ማለቱ ነው።

👏 ኢየሱስ ቸር እንደሆነ

'' የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ቸር ስጦታ አውቃችኋልና፤ ሀብታም ሲሆን፥ እናንተ በእርሱ ድህነት ባለ ጠጎች ትሆኑ ዘንድ ስለ እናንተ ድሀ ሆነ።'' (2 ቆሮ 8:9)


  “ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።”
  — ሉቃስ 2፥11

ለክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሀነ ልደቱ በሰላም በጤና አደረሳቹ አደረሰን🤲😘


✟ ጋሜል- ዘ ኦርቶዶክስ ✟ dan repost
💗እንኳን ለዓለም ሁሉ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ዓመታዊ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!



መልካም በዓል 🫶




✟ ጋሜል- ዘ ኦርቶዶክስ ✟ dan repost
ይህ ምልክት ይሁናችሁ፤ ሕፃን ልጅ በጨርቅ ተጠቅልሎ በግርግም ተኝቶ ታገኛላችሁ።”


ሉቃስ 2:12


✟ ጋሜል- ዘ ኦርቶዶክስ ✟ dan repost
✨ ሰብአ ሰገል ✨
-----------💗------------


ኮከቡንም ሲያዩ ከመጠን በላይ ተደሰቱ። ወደ ቤትም በገቡ ጊዜ ሕፃኑን ከእናቱ ከማርያም ጋር አዩ፤ ተንበርክከውም ሰገዱለት። ሣጥኖቻቸውን ከፍተው ወርቅ፣ ዕጣን፣ ከርቤም አቀረቡለት።


ማቴዎስ 2:10-11




✟ ጋሜል- ዘ ኦርቶዶክስ ✟ dan repost
​​🎅 የገና አባት (ቅዱስ ኒቆላዎስ) ለድሆች ሥጦታ ይለግስ የነበረ ቅዱስ አባት ነው። ታሪኩም በስንክሳር ታኅሣሥ 10 ላይ ተጽፎአል። "የገና ዛፍ ባሕላችን አይደለም እነርሱ ክረምታቸውን የሚያስታውሱበት ነው ከእኛ ጋር አይገጥምም" "የተወለደውን ክርስቶስ የበዓሉ ማዕከል እንዳናደርግ ያደርገናል" ማለት ትክክለኛ ነገር ነው። Pagan Origin (የባዕድ አምልኮ መነሻ) አለው ብሎ ጣዖት አምልኮ ነው ማለት ግን ከገደብ ያለፈ ድምዳሜ ነው። በከዋክብት ያመልኩ የነበሩት የጥበብ ሰዎች በሚያመልኩት ነገር ወደ ክርስቶስ ተጠርተዋል ፣ የዙሐል ጣዖት ይከበርበት የነበረውን ዕለት ከክርስትና በኋላ በእስክንድርያ የቅዱስ ሚካኤል በዓል ቀን ሆኗል።


➡️ የራሳችንን የገና ባሕላዊ አከባበሮች የገና ጨዋታን ፣ ቀጤማ መጎዝጎዝ የመሳሰሉትን ማክበር ይገባናል። ከዚያ ውጪ በክርስትና መንፈስ እስከተቃኘና የጌታን በበረት መወለድ ፣ የሰብአ ሰገልን ጉዞ ፣ ከዋክብቱን ፣ የመላእክትን ዝማሬ ፣ የእረኞችን ደስታ ፣ የሰብአ ሰገልን እጅ መንሻ የሚያሳይ እስከሆነ ድረስ የኛ ባሕል ያልሆነውን ሁሉ ጣዖት ነው ብሎ ማንቋሸሽ ፣ የሚያምር ነገርን ሁሉ ማውገዝ ያስመስላል። ቅዱስ ኒቆላስም የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የምትዘክረው ቅዱስ ስለሆነ አጋጣሚውን ጻድቁን ለማስተዋወቅም ልንጠቀምበት ይገባል። ሥጦታም የምንሠጣጠው የሰብአ ሰገልን ሥጦታ መነሻ አድርገን ሲሆን ልግስናውን ለነዳያን ብናደርገው የበለጠ በረከት እንቀበልበታለን።

ጌታችን ስለተወለደባት ምሽት {ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬም} አንዲህ አለ :


‹‹ይህች ምሽት ንጹሕ የሆነውና እኛን ሊያነጻን የመጣው (አምላክ) የተገለጠባት ንጽሕት ምሽት ናት፡፡  ጆሮአችን ንጹሕ ይሁን ፤ ዓይኖቻችንም ወደ ንጹሕ ነገር ይመልከቱ ፤ የልባችን ስሜት ቅዱስ ይሁን! ንግግራችንም አክብሮትን ይሞላ!

➦ ይህች ምሽት የዕርቅ ምሽት ናት ፤ ስለዚህ ማንም ሰው ወንድሙን ተቆጥቶ እንዳያስቀይም! ይህች ምሽት ለዓለም ሁሉ ሰላምን ያስገኘች ምሽት ስለሆነች ማንም ሰው አይሸበርባት፡፡ ይህች ምሽት የደግነት ምሽት ስለሆነች ማንም ሰው ክፉ አይሁን! ይህች ምሽት የትሕትና ምሽት ናትና ማንም ሰው እንዳይታበይባት!

➦ ይህች ምሽት የደስታችን ቀን ስለሆነች የበደሉንን አንበቀልባት! የበጎ ፈቃድ ቀን ናትና የጭካኔ ቀን አናድርጋት! የጸጥታ ቀን ናትና በቁጣ የምንነድባት ቀን አናድርጋት! ዛሬ እግዚአብሔር ወደ ኃጢአተኞች የመጣበት ቀን ነው ፤ ስለዚህ ጻድቅ ሰው በኃጢአተኞች ላይ አይኩራባቸው! ዛሬ እጅግ ባለጠጋ የሆነው አምላክ ስለ እኛ ደሃ የሆነበት ቀን ነው፤ ስለዚህ ሀብታም ሰው ድሆችን ወደ ገበታው ይጥራቸው፡፡

➦ ዛሬ ያልጠየቅነውን ሥጦታ የተቀበልንበት ዕለት ነው፡፡ ስለዚህ እጆቻቸውን ዘርግተው እየጮኹ ለሚለምኑን ሰዎች የእርዳታ እጃችንን እንዘርጋ! የዛሬዋ ዕለት ለጸሎቶቻችን የሰማያትን በር ከፍታልናለች ፤ እኛም ይቅርታን ለሚጠይቁን ሰዎች በራችንን እንክፈት! ዛሬ አምላክ የሰውነትን ማኅተም በራሱ ላይ አተመ ፤ ሰውም የአምላክነትን ማኅተም ተጎናጸፈ!››

ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ

💚 @maedot_ze_orthodox
💛 @maedot_ze_orthodox
❤️ @maedot_ze_orthodox



20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.