ከመጽሐፍት መንደር💠


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


አንብብ አዕምሮህ ልክ አንደባህር ይሰፋል። ወንዞችም ለአንተ መገበር ይጀምራሉ። አንተ ወደ ሰዎች ሳይሆን ሰዎችም ወደአንተ ይመጣሉ። ማንብብ ሙሉ ሰው ያደርጋል!! አንብብ ብታነብ የሚቀርብህ ድንቁርና
🟩🟩🟩🟩🟩🟩🟩🟩🟩🟩
🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨
🟥🟥🟥🟥🟥🟥🟥🟥🟥🟥
ለማንኛውም አስተያየት
@manbabemuluyadergal_bot

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


ማለት አይደለም…አንዳንዱ ግንኙነቶች ምንም ቢለፋባቸውና ፍሬ አያፈሩም…ያንተም እንደዛ ሆኖ ይሆናል››
‹‹ይገርማል››
‹‹ምኑ ነው የሚገርመው?››
‹‹እኔ ሳልሆን አንቺ ነሽ የፍቅር አማካሪ መሆን የነበረብሽ››
‹‹እንግዲህ በችሎታዬ ከተማመንክ ስልጠና ሰጥተህ ወደፊት በረዳትነት ልትቀጥረኝ ትችላለህ››
‹‹ደስ ይለኝ ነበር…ደሞዝሽ ይከብደኛል እንጂ››
‹‹አይዞህ..አትፍራኝ …አንደራደራለን››
‹‹አመሰግናለሁ…አንቺ ጋር መደወሌ ምክንያታዊ ባይሆንም ..ግን ሰርቷል አግዘሺኛል፣አሁን ትንሽ ቀለል አለኝ፡፡››
‹‹አሁን መጠጣቱ ይብቃህ…ሻወር ወሰድና ተኛ…ጥዋት ስትነሳ ሁሉ ነገር ቀለል ብሎህ ታድራለህ››
‹‹እሺ….እንዳልሺኝ አደርጋለው….ደህና እደሪ››

‹‹ደህና እደር››ብላ ስልኩን ዘጋችው ፡

ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
ከመጽሐፍት መንደር
ከመጽሐፍት መንደር
ከመጽሐፍት መንደር

♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️


‹‹‹አይ ይሄ ለነገሮች ያለን ትርጉም ልዩነት ላይ የተመሰረተ ነው፡፡እኔ ወላጅ አልባ ብቻ ሳልሆን ዘመድ አልባ በሆንኩበት በዛ ጨለማ ጊዜ እናትና አባትህ ያለምንም ማቅማማት ወደቤታቸው ወስደው ከዛሬ ጀመሮ አንቺም ሌለኛዋ ልጃችን ነሽ አሉኝ፡፡እውነትም እንዳሉት ለእህትህ ስህን የሚደረገው ሁሉ ለእኔም ይደረግልኝ ነበር..ለእሷ ቀሚስ ሲገዛ ለእኔም ዘለውኝ አያውቁም.. ከፓንት አቅም ለእሷ የተገዛው አይነት ለእኔም ይገዛልኝ ነበር… የእውነት ልጃቸው ነበርኩ..ዩኒቨርሲቲ ገብቼ አንድም ወር የኪስ ገንዘብ ለእኔ ከመላክ እረስተውና ዘለውኝ አያውቁም…እና ሁለቱም ሲሞቱ ከእናንተ እኩል ነው ያጣዋቸው…..አንተ የምትወዳቸውን ያህል እኔም ወዳቸዋለው…አሁን የሚናፍቁህን ያህል

እኔንም ይናፍቁኛል..እና እኔ የእውነትም አንተም ወንድሜ እነሱም ወላጆቼ እንደሆኑ ነው የማምነው..ይሄንን እምነቴን ማንም በየትኛውም ሎጂክ ተከራክሮ ሊያስቀይረኝ አይችልም…እምነት ያው ከቃሉም እንደምትረዳው ዝምብለህ ነገሩን በቀና ልብ መቀበል አይደል..እኔም እንደዛው ተቀብዬዋለው…፡፡አሁን እንተ የደም ትስስር የለንም ምናምን ብትለኝ.በአንዱ ጆሮዬ ገብቶ በአንድ ይፈሳል እንጂ በእኔ ስሜት ላይ ምንም የሚያመጣው ለውጥ የለም…አንተ እንደፈለከው ማመን ትችላለህ…እህቴ አይደለሽም ልትለኝም ትችላለህ…በግድ ላሳምንህ አልችልም..፡፡››
‹‹ይገርማል… ልጅ እያለንም ጭምር እንዲህ ነገሮችን ውስብስብ ማድረግ ትወጂ ነበር…እሺ አሁን ለምን ተመልሼ እንደመጣሁ ታውቂያለሽ?››
‹‹ያው የሰው ሀገር አይደል ..ደብሮህ ነዋ››
‹‹አይ አይደለም….ከመስፍን ጋር እንደተፋታችሁ ስሰማና ፣አገር ለቆ እንደሄደ ሳረጋግጥ…ዳግመኛ እድሌን ለመመከር ነው..ምን አልባት አሁን እነአባዬና እማዬ በህይወት ስለሌሉ እሺ ብለሽ ፍቅሬን ትቀበይዋለሽ..እኔንም ከቁም ሞት ቀስቅሰሽ ታድኚኛለሽ..ባል አድርገሽ ታገቢኛለሽ ብዬ ነው››
ዝም ብላ በፍዘት ታየው ጀመር…ቡዝዝ ባሉት አይኖቾ እንባ ሞላባቸው…
‹‹ወንድሜ እኔ በጣም ነው የምወድህ..ያንተ ከጎኔ መሆን የሚፈጥርልኝ ጥንካሬና የመንፈስ ከፍታ ልትገምተው አትችልም…አንተ የራስህን ሰው አግኝተህ አፍቅረህና አግብተህ እዚሁ
አጠገቤ አዲስአበባ እንድትኖር ነው የምፈልገው…እባክህ ወንድሜ መልሰህ ጥለሀኝ አትሂድ
..ዳግመኛ እሰደዳለሁ ካልከኝ..በጣም ነው የማዝነው..እራሴንም መቼም ይቅር አልለውም››
‹‹የምታወራው ምንም ሊገባው አልቻለም..እሱ የሚያወራው እሷን ስለማግባት እና አብሮ አንድ ቤት ስለመኖር…እሷ የምታወራው ስለእሱ ዳግመኛ መሰደድ…‹‹ድንገት ሳላውቅ ተመልሼ ሄዳለው ብያት ይሆን እንዴ ?››ሲል እራሱን ተጠራጠረ፡፡
‹‹ኪያ ምን ነካሽ…?ተመልሼ ሔዳለው ብዬሻለው…እንዴ..?››
‹‹አላልከኝም…ግን ወንድሜ በወላጆቻችን አጥንት ይዤሀለው፣ምንም ቢፈጠር ምንም ጥለኸኝ እንደማትሄድ ቃል ግባልኝ››

‹‹እሺ..እንዳልሽ ቃል ገባልሻለው…ምንም ቢፈጠር ምንም ተመልሼ በድጋሚ አልሰደድም፡፡››
‹‹ጥሩ….ማታ የምቀበለው እንግዳ መስፍን ነው››
የቤተሰቦቹን ሞት የሰማ ቀን እንኳን እንዲህ አልደነገጠም‹‹ምን ..?መስፍን….?ከየት…ወጭ አይደል እንዴ?››
‹‹አዎ..ለአለፉት ሁለት ሶስት ወራት ስንደዋወል ነበር..ችግሮቻችን ተነጋገርን ለመፍታት እና የተበላሸውን ግንኙነታንን ለማስተካከል ወስነን አሁን እየመጣ ነው…ዛሬ ሁለት ሰዓት ነው የሚገባው..ቀጥታ ከቦሌ እኔ ነኝ የምቀበለው..እየመጣ መሆኑን ቤተሰቦቹም አያውቁ..ማለቴ ከቦሌ ቀጥታ ወደቤት ነው ይዤው የምመጣው..ልጅንም በጣም ናፍቆል..እና ተነጋግረን ችግሮቻችንን መቅረፍ ከቻልን ነገሮች ወደድሮ ቦታቸው ይመለሳሉ ማለት ነው..ያው ታውቃለህ የፍቺው ጉዳይ ገና ፕሮሰስ ላይ ነው…ያ ማለት አሁንም በህግ ፊት ባልና ሚስቶች ነን››
ድንዝዝ ባለ ስሜት ንግግሯን እስክትጨርስ ዝም ብሎ አዳመጣት…በፍጽም ፀጥታ ነው የተቀመጠው…ሰውነቱ አይንቀሳቀስም…የአይኖቹ ቅንድቦች እንኳን መንቀሳቀስ አቁመው ነበር፣ትንፋሹ መተንፈስም እንዳቆመ አይነት የመታፈን ስሜት እየተሰማው ነው…ንግግሯን ካጠናቀቀች በኃላም እሱ በዝምታው እንደቀጠለ ነው፡፡
ግራ ገባት…የሆነ ነገር እንዲል እየጠበቀችው ነው…እንዲወቅሳት..እንዲረግማት….በእሷ እንዲያማርር እየጠበቀች ነው..እሱ ግን እንደዛ እያደረገ አይደለም…አስፈሪ ዝምታ ላይ ነው፡፡
‹‹ወንድ….ሜ››
‹‹ሂሳብ ክፈይና እንሂድ››ብሎ መኪናውን ቁልፍ ከጠረጴዛ ላይ አነሳና ቀመ ..ወደመኪናው መራመድ ጀመረ…ከቦርሳዋ ብር አውጥታ ጠረጴዛ ላይ ወረወረችና ፈጠን ብላ ከኃላው ተከተለችው፡፡በህይወቱ እደዛሬው ባዶነትና ተስፋ ቢስነት ተሰምቶት አያውቅም..ፍፅም ተስፋ መቁረጥ ማለት ምን ማለት እንደሆነ የገባውም ዛሬ ነው..በቃ መቼም ይህቺን ሴት ማግባት እንደማይችል አምኖ ተቀበለ…ባያገባትም ግን መቼም ደግሞ ማፍቀሩን እንደማያቆም ያውቃል፡፡

እቤት አድርሷት ብዙም ሳይቆይ ነው ወደቤቱ ያመራው፡፡የሚኖረው ወላጀቹ ቤት ነው ሁሉም ወንድሞቹ የራሳቸውን ህይወት መስርተውና የገዛ ቤታቸውን ሰርተው ቤቱን የለቀቁት ገና ወላጆቹ በህይወት እያሉ ነው፡፡እህቱም ሀገር ውስጥ አትኖርም አሁን በብቸኝነት እየኖረበት ያለው እሱ ነው፡፡ወደቤት ሲገባ ሙሉ ጠርሙስ ጎርደን ጅን ይዞ ነበር የገባው….ገና በቀኑ ነው መኝታ ቤቱን ዘግቶ መጠጣት የጀመረው…
ማታ አንድ ሰዓት ሲሆን ጥንብዝ ብሎ ሰክሮ ነበር‹‹ይሄን ያንን ጉረኛ ልትቀበለው ቦሌ አየር ማረፊያ ቆማ ብርድ እያንቀጠቀጣት ነው››አለ..አሳዘነችው…‹‹ለእሷ የምገባት እኔ ነበርኩ….››ማልቀስ አማረው..እዬዬ ብሎ ማልቀስ አማርው..ግን ማድረግ አልቻለም፡፡ስልኩን ከኪሱ አወጣና ‹‹ማውራት ከቻልሽ ደውይልኝ ››ብሎ ፃፈና ለከ..
ከ5 ደቂቃ በኃላ ተደወለለት‹‹ወይ እግዜር ይስጥሽ…አትደውይልኝም ብዬ ፈርቼ ነበር››
‹‹ምነው? ችግር አለ እንዴ…?ወላጆቼ ምን ሆኑ?››
‹‹‹እነሱ ሰላም ናቸው..በጣም ሰላም ናቸው…ዛሬ አዲስ አበባ ተመልሰናል..እነሱም እቤታቸው ናቸው….እኔ ግን…››ሲያወራ አፉ ይኮለታተፋል..
‹‹ምነው ?አንተ ምን ሆንክ?››
‹‹ተሰብሬለሁ…ሌላ ማወራው ሰው ስለሌለን ነው አንቺ ጋር የደወልኩት…አይገርምም ደህና ጓደኛ እንኳን የለኝም….ቢኖረኝም እንዲህ አይነት ነገር የምነግራቸው አይደሉም››
‹‹ወይኔ በፈጣሪ..እስኪ የሆንከውን ንገረኝ…?.››
‹‹በፀሎት…››
‹‹ወዬ››
‹‹አሁን ካለሽበት መጥተሸ አጠገቤ ብትሆኚና ብታጣጪኝ ደስ ይለኝ ነበር››
‹‹እኔም ደስ ይለኝ ነበር…እይዞህ አንተ ብዙ ነገር የምታውቅ ሰው አይደለህ..?››
‹‹ማወቅ ምን ይሰራል…በፍቅር ስትንኮታኮቺ እኮ ያንቺ ማወቅ እርባነ ቢስ ነው፡፡እኔ እንደውም ይሄንን የፍቅርና የጋብቻ አማካሪ የሚባለውን ጫወታ መተው አለብኝ..አዎ ፍቃዴን መልሼ ቢሮዬን ዘጋለሁ…››

‹‹ለምን ..ያ ደግሞ ምን ማለት ነው?››
‹‹አይታይሽም እንዴ…ከልጅነቴ ጀምሮ ሳፈቅራት የኖርኳትን ሴት የሆነ ዘዴ ተጠቅሜ እንድታፈቅረኝና እሺ ብላኝ እንድታገባኝ ማድረግ ካልቻልኩ እንዴት ነው ሌላ ሰውን ማገዝ የምችለው…ይሄው ለሁለተኛ ጊዜ አጣኋት …ያሁን ማጣት ደግሞ ይግባኝ የሌለው ነው…እራሴንም ሰዎችንም እያጭበረበርኩ እንደሆነ ነው የሚሰማኝ፡፡›› ‹‹አይ..ያ እውነት አይደለም…ቤተሰቦቼን ምን ያህል እንዳገዝካቸው እኔ ነኝ ማውቀው..አረ የእነሱን ተወውና እኔን እራሱ በስልክ ብቻ በምታወራኝ ምን ያህል ጥንካሬና ብርታት እንደምትሰጠኝ አታውቅም..ፈፅሞ በምንም ምክንያት ተስፋ መቁረጥ የለብህም..ደግሞ አንድ ግንኙነት አልተሳካምና ጠቅላላ ያንተ ህይወት አበቃለት


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ሀያሁለት

ባልና ሚስቶቹን ቤታቸው ወስዶ እንደጣላቸው ቀጥታ የመኪናውን መሪ ወደአስቴር ቢሮ ነው የጠመዘዘው…ገብቶ ምሳ እንዲበላ ቢለምኑት እንኳን እሺ አላለቸውም፡፡እንደሚመጣ አልነገራትም ቀጥታ ከቢሮዋ ፊት ለፊት አቆመና ደወለ
‹‹ሄሎ ወንድሜ….እንዴት ነው ቢሾፍቱ በጣም ተመችታሀለች መሰለኝ?፡፡››
‹‹መጥቻለው….ምሳ አትጋብዢኝም?፡፡››
‹‹የእውነት መጣህ?››
‹‹አዎ ቢሮሽ ፊት ፊት መኪናዬን አቁሜያለው፡፡››
‹‹በቃ መጣሁ››ብላ ስልኩን ዘጋች….5 ደቂቃ ነው ያስጠበቀችው፡፡ገና የቢሮዋን የህንፃ ደረጃ ስትወርድ ጀምሮ ነው አይኑ ውስጥ የገባችው…ሙሉ ሮዝ ቀለም ያለው ጉረድ ቀሚስና ኮት ለብሳለች…ፀጉሯ ወደኃላዋ ትከሻዋ ላይ እንዲተኛ ተደርጎል…ውብ ሆናለች….መኪናዋን ስለምታውቃት ብዙም ሳትደነጋገር ቀጥታ ወደእሱ ነው ያመራችው…ይህቺ ሴት እህቱ እንድትሆን አይደለም የሚፈልገው…ጓደኛም እንድትሆነው አይደለም…የፍቅር አጋሩ ሚስቱ ሊያደርጋት ነው ምኞቱ..ይሄ ምኞቱ ደግሞ አሁን በቅርብ በውስጡ የበቀለ ስላልሆነ ህመሙ ቀላል አይደለም…ገና አፍ ፈቶ በኮልታፋ አንደበት መንተባተብ በጀመረበት በጮርቃነት እድሜው ጀመሮ እሷ ሚስቱ እንደሆነች ያስብ ነበር፣እርግጥ በዛን እድሜ ሚስት ማለት እራሱ ትርጉሙ ምን ማለት አንደሆነ አያውቅም ነበር፣ቢሆንም ጭላንጭል የሆነ ግንዛቤ ነበረው…ሚስት ማለት አንድ ክፍል ውስጥ አንድ አልጋ ላይ ሁሌ አብራ

የምትተኛ ሴት እንደሆነች ከአባትና ከእናቱ ግንኙነት መረዳት በቻለበት ጊዜ ነው፣ከእሱ ጋር ለዘላለም መተኛት ያለባት ሴት አስቴር እንደሆነች ወስኖ የነበረው፣በዛን የልጅነት ጊዜ እናቷ የቤታቸውን እንጀራ ልትጋግር ስትመጣ አስከትላት ስትመጣ ጀምሮ እዛው እሷን ማስቀረት ምኞቱ ነበር…እና ያ ምኞት ግለቱን ጠብቆ እየፋመ ነበር የቀጠለው…
ጊዜው ሲደርስ ግን ነገሮች ቀደም ብሎ እንዳሰባቸው ቀላል አልነበሩም…ገቢናውን ከፈተላት ገባች.. ጉንጩን አገላብጣ ሳመችው…ሁል ጊዜ የእሷ መሳም ከሌላው መሳም በጣም ይለይበታል…ወፈር ብሎ ወደፊት ግልብጥ ያለው ፍም ከንፈሯ ሰውነቱ ላይ ሲርፍ የተለየ ሙቀት ነው ሰውነቱ የሚያመነጨው…ልክ የጋለ ቢላዋ አካል ላይ ሲያርፍ የሚሰማው አይነት ትሽሽሽ..የሚል የማቃጠል የመለብለብና የመላጠ ስሜት……
‹‹አንተ ወፍረህ ነው የመጣሀው….ስራ ላይ ነበርክ ወይስ ጫጉላ ሽርሽር ላይ?››
‹‹በይው…አንቺም ተመችቶሻል…ምሳ የት አንብላ?››
‹‹ወደ እኔ ቤት ንዳው››
‹‹ምነው ከሰዓት ስራ የለሽም እንዴ?››
‹‹ዛሬ ቅዳሜ እኮ ነው…ግማሽ ቀን ነው የምንሰራው››
‹‹እና አራበሽም ..በልተን ብንሄድ አይሻልም?››
‹‹አይ ሰራተኛዬ አዘጋጅታ እየጠበቀችን ነው…ዘና ብለን ቤታችን ብንበላ ይሻላል….ወንድሜ ስለመጣህ ደስ ብሎኛል››
‹‹እኔም ከሰዓት ስራ ስለሌለሽ ደስ ብሎኛል››ብሎ መኪናዋን ወደ አስፓልት መሀል አስገባና ነዳት….የእውነትም ከሰዓት ስራ የለኝም ብላ ወደቤቷ ይዛው እየሄደች በመሆኑ ከፍተኛ ደስታ ተስምቶታል…ከአመታት በኃላ መልሶ ዛሬ እድሉን ይሞክራል፡፡አዎ በስደት ከሄደበት ባእድ ሀገር ተመልሶ የመጣውም ለዚሁ ነው፡፡ከባሎ እንደተለያየችና እሱም በዛ ንዴት ከሀገር ውጭ መሰደዱን ሲሰማ ነው ሁሉን ነገር እርግፍ አድርጎ የመጣው…አንሆ ተመልሶ በመጣበት ባለፉት ስድስት ወሮች እሷን ከገባችበት ድባቴ እንድትወጣና ያልተሳካ ትዳሯ ከፈጠረባትን የስነልቦና መሰበር እንድታገግም እንደወንድም እንደ ጓደኛም ከዛም አልፎ እንደባለሞያም  ከጎኗ  ሆኖ  ሲያግዛትና  ሲደግፋት  ነበር…አሁን  ግን  ልቧ  ሌላ  ፍቅር

ለማስተናገድ ዝግጁ ነው ብሎ ያስባል..በዛ ላይ የእሱ እና የእሷ ፍቅር አዲስ ዛሬ የበቀላ ሳይሆን ድሮ በየሁለቱም ልብ ተዳፍኖ ያለ ነው…አሁን ያንን መቆስቆስና መልሶ እንዲቀጣጠል ትንሽ የፍቅር ቤንዚል ማርከፍከፍ ነው…ለዚህ ድርጊት ያበረታታው ሰሞኑን ያየው በአቶ ሃይለልኡል እና በወ.ሮ ስንዱ መካከል የተከሰተው የፍቅር ግርሻ ነው፡፡
‹‹አዎ…አስቴርን አገባታለሁ…ከበፊት ባሏ የወለደችውን አንድ ልጅም እንደልጄ አድርጌ አሳድገዋለው››በውስጡ አልጎመጎመ…‹‹እና በቅርብ ቀን እሷም ወንድሜ የምትለውን ጥሪ ትተውና ባሌ ብላ ትጠራኛለች…ልጇም አጎቴ ብሎ የሚጠራውን አቁሞ አባቴ እንዲለኝ
አደርጋለው››ይሄንን ስላሰበ ብቻ ውስጡ በደስታ ተፍነከነከ..ቤት ሲደርሱ እውነትም እንዳለችው ቆንጆ ምሳ ተዘጋጅቶ ነበር የጠበቃቸው፡፡እየተጎራረሱ በሉ፡፡ከምግብ በኃላ ብና ተፈላላቸው..እሷ ሁለት ሲኒ እሱ አንድ ሲና ጠጡና ተጠናቀቀ፡፡
‹‹እዚሁ ልንገራት ወይስ ይዣት ወጣ ልበልና ዘና ያለ ቦታ ወስጄ ዘና ባለ ስሜት ላይ ከሆነች በኃላ ልንገራት ››እያለ ሲወዛገብ ቆየና‹‹እ…ፕሮግራማችን እንዴት ነው….?ወጣ እንበል ወይስ እዚሁ ነው የምንቆየው?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹አይ…ወጣ እንላለን..ሱፐርማርኬት ወጥቼ መሸማመት አለብኝ..መጠነኛ ድግስ ደግሳለው፣ማታ እንግዳ አለብኝ››
ንግግሯ ግራ አጋባውም.. ደነገጠም፡፡
‹‹የማታ እንግዳ ምን አይነት ነው?›› our
‹‹አንተም አለህበት…ዛሬ እዚህ ነው አይደል የምታድረው?››
እሷ ጋር እንዲያድር ስለጠየቀችው ደስ ብሏታል ..ግን እንግዳውስ…?ለመሆኑ ማን ነው
…?ሴት ነው ወንድ?፡፡‹‹እሺ ..እዚህ ነው የማድረው…ግን እንግዳውስ?››
‹‹እንግዲህ እሱን ከመጣ በኃላ ነው የምናውቀው…ልደር ካለ ግን እምቢ ማደር አትችልም የምለው አይነት ሰው አይደለም››በማለት ግራ አጋቢ መልስ ሰጠችው፡፡መልሷ ይብልጥ ቁርጠት ለቀቀበት…ይሄኔ ከመስሪያ ቤቷ ባለደረቦች አንዱ ነው….ሀለቃዋ ይሆን እንዴ…?ቢሆንስ ልደር ስላለ እንዴት እሺ ልትለው ትችላለች..?››ወይ ሴቶች ምን አይነት ቅኔ የሆኑ ፍጡሮች እንደሆኑ ሁሌ እንደደነቀው ነው፡፡ወንድም ሴትም በአንድ ላይ ሰው ተብሎ

መፈረጁ  አግባብ  አይደለም….አስተሳሰባችን  እምነትና  ፍላጎታችን  ምኑም  እኮ አይገናኝም››ሲል በውስጡ አብሰለሰለና..ነገሮች እስኪደርሱ ጠብቆ ለማየት ወሰነ…
‹‹ከዛ በፊ የተመቻቸ ጊዜ ካገኘው ነግራታለሁ…እንደውም ከማታው ፕሮግራሞ በፊት የእኔን ሀሳብ መስማት አለባት››የሚል ድምዳሜ ላይ ደረሰ‹‹በቃ እንሂዳ››አላት፡፡
‹‹እሺ፣ተነስ ብላ ቦርሳዋን አንጠለጠለችና ተነሳች..ተያይዘው ወጡ ..ያለችው ሱፐር ማርኬት ይዛው ከገባች በኃላ ምትፈልገውን ነገሮች ሁሉ ተገዝተው በመኪናው ከተጫኑ በኃላ.. ማኪያቶ እንጠጣ ብሎ አንድ ፀጥተኛ ካፌ ይዞት ገባና..ፊት ለፊት እንደተቀመጡ እንደምንም እራሱን አጠንክሮ ወደነጥብ መንደርደር ጀመረ
‹‹ለምን ወደውጭ እንደሄድኩ ታውቂያለሽ አይደል?››
‹‹ሁለተኛ ዲግሪህን ለመማር ነዋ››
‹‹አይ ያማ ሽፋን ነው….እውነተኛ ምክንያቴን አንቺም በደንብ ታውቂዋለሽ..ወደውጭ የሄድኩት ባንቺ ተበሳጭቼ ነው፡፡››
‹‹አንተን ለማበሳጨት ብዬ ግን ምንም ያደረኩት ነገር የለም››
‹‹እሱን ማግባት አልነበረብሽም››
‹‹ለምን …ታዲያ አንተን ወንድሜን ማግባት ነበረብኝ?››
‹‹ምን ችግር አለው?እርግጥ እንደወንድምና እህት አንድቤት አድገናል..ግን የስጋ ትስስር አልነበረንም›


እቴጌ  ጣይቱ ብጡል

  ጣይቱ ከአባታቸው ከደጃዝማች ብጡልና ከእናታቸው ከወይዘሮ የውብዳር
ነሀሴ ፲፪ ቀን ፲፰፻፴፪ ዓ.ም በአሁኑ ደቡብ ጎንደር ዞን ደብረታቦር ከተማ ተወለዱ።

አባታቸው የጎንደርና የወሎ፣ እናታቸው ደግሞ የጎጃም ተወላጅ ናቸው። አባታቸው በጦርነት በመሞታቸው በ፲፫ ዓመታቸው ደብረታቦርን ለቀው ወደ እናታቸው ትውልድ ቦታ ወደ ጎጃም ሄዱ
ንጉሥ ምኒልክ በሚያዚያ ወር ፲፰፻፷፱ ዓ.ም ወደ ባህርዳር ተጉዘው በእናታቸው በወይዘሮ የውብዳር ቤት ዘመድ ወዳጅ በታደመበት ከወይዘሮ ጣይቱ ብጡል ጋር ተጫጩ።

ከዚያም ሚያዚያ ፳፭ ቀን ፲፰፻፸፭ ዓ.ም በአንኮበር መድሃኒዓለም ቤተክርስቲያን በቁርባን ተጋቡ።ጥቅምት ፳፯ቀን ፲፰፻፹፪ ዓ.ም ጣይቱ ብጡል  እቴጌ  ተብለው  ተሰየሙ ።

እቴጌ  ጣይቱ ፖለቲካዊና  ሀይማኖታዊ ክርክሮች  ላይ  እየተገኙ የመንግስታቸውን  አቋም  ያስረዱና ይከራከሩ  ነበር ። አፄ ምኒልክ ወደ ዘመቻ ሲንቀሳቀሱ የመንግስት ዓይንና ጆሮ ሆነው  አገልግለዋል ።የአዲስ አበባን ከተማ የመሠረቷት እቴጌ  ጣይቱ ናቸው ። የመጀመሪያውን ዘመናዊ ሆቴልም ከፍተዋል ። እቴጌ ጣይቱ በተለያየ  መልኩ  አገራዊ ተልዕኳቸውን  የተወጡ ጀግና  ሴት  ነበሩ ጣሊያኖች በውጫሌ  ውል ካስፈረሟቸው ነጥቦች  መካከል  አንቀፅ ፲፯ ሥር ያለው ሀሳብ በስህተት  መተርጎሙን አጥብቀው  ተቃውመዋል ። አንቀፅ  ፲፯ን ጣሊያኖች ኢትዮጵያን በሚጎዳ መልኩ  አዛብተው  ጥቅም  ላይ  እንዲውል  ባደረጉበት  ጊዜ ውሉን  ከመቀበል  ጦርነትን እመርጣለሁ በማለት  የማያወላውል አቋማቸውን  አሳውቀዋል ።  በዚህም  በኢትዮጵያና  በጣሊያን  መካከል  እሰጣገባው ተካርሮ  ጦርነቱ አይቀሬ  ሆነ ። አፄ  ምኒልክ  ምታ  ነጋሪት ክተት  ሰራዊት  ብለው  ወደ አድዋ ጦርነት ዘመቱ እቴጌ ጣይቱም በራሳቸው  የሚመራ  ፴፻ እግረኛ ጦርና ፷፻ ፈረሰኛአስከትለው ከባለቤታቸው  ጎን በመሠለፍ የካቲት ፳፫ቀን ፲፰፻፹፰ዓ.ም አድዋ ላይ  ጠላትን  ድል  አደረጉ ። እቴጌ ጣይቱ ጦርነት ከመጀመሩ  ከጥቂት  ቀናት  በፊት ለጦር  አበጋዞች የጦርነት  ስልት  አቀረቡ ። ይህም  የጠላት  ወታደሮች  ውሃ  የሚጠጡበትን ምንጭ  በመቆጣጠር  ማጥቃት እንደሚቻል  ያቀረቡት  ሀሳብ  ነበር ። ሀሳባቸውም  በአፄ  ምኒልክና  በሁሉም  የጦር  አበጋዞች ዘንድ ተቀባይነትን ስላገኘ ጠላት ውሃ የሚጠጣበት ምንጭ በኢትዮጵያ ወታደሮች ቁጥጥር ስር ዋለ። እቴጌ ጣይቱ የካቲት ፬ ቀን ፲፱፻፲ ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ቢለዩም ስማቸውና ያከናወኗቸው ተግባራት ግን  ከሌሎች እውቅ የኢትዮጵያ አርበኞች ጋር ዘላለም  ሲወሳ  ይኖራል።
                  




አቶ ኃይለልኡልም እጅ በሰጠ ድምፅ‹‹አንተ ምን ብናደርግ ትመክረናለህ?››ሲሉ እሱኑ መልሰው ጠየቁት፡፡
‹‹ይሄውላችሁ እንደእኔ እንደእኔ በፀሎት ወደቤት መመለስ ያለባት በእናንተ ላይ የነበራት ቅሬታ ሙሉ በሙሉ ተቀርፎ…ሁሉን ነገር በራሷ መንገድ አረጋግጣና ፈቅዳ…ደስ ብሎት ነው
…ይሄውላችሁ አሁን አብዛኛውን አስቸጋሪ የነበረውን መንገድ ተጉዛችኃላ …እስኪ አስቡት ከአስራአምስተ ቀን በፊት ወደቢሾፍቱ ስንሄድ አንድ መኪና ውስጥ መቀመጥ እራሱ የሚቀፋችሁ ሰዎች ነበራችሁ፣ትዝ ይላችኃላ ጋሼ ገቢና ነበር የተቀመጥከው…አሁንስ ይሄው በደስታ ጎን ለጎን በራሳችሁ ፍቃድ ተቀምጣችሁ እርስ በርስ ተጣብቃችሁ የደስታ ወሬ እያወራችሁ ትሳሳቃላችሁ..ከባዱ ነገር እናንተን እዚህ ስሜት ላይ ማድረስ ነበር…ከአሁን ወዲህ ያለው ይሄንን ግንኙነት መሰረት እንዲይዝና ስር እንዲሰድ ማድረግ ብቻ ነው… ያ ደግሞ ቀላል ነው…ቢያንስ 15 ቀን መታገስ ያቅታችኃላ….?፡፡››
‹‹እና ባለችበት ትቀመጥ እያልክ ነው…?ያለችበት ሁኔታ… እቤቱ የሰዎቹ ኑሮ ምኑም አይመቻትም እኮ…››
ከቀናት በፊት ስላለችበት ቤት ሲጠይቃት ያለችው ነገር ትዝ አለውና ፈገግ አለ፡፡

‹‹እውነቴን ነው..እርግጥ ሽማግሌው በጣም ጥሩና ደግ ሰው ናቸው….ቢሆንም ኑሮቸው ከእጅ ወደአፍ ነው..ልጄ ከቤት ስትወጣም ደህና ብር እንኳን ይዛ አልወጣችም››
‹‹አይዞችሁ እስከዛሬ ድምጻን አጥፍታ ኖረች ማለት በጣም ቢመቻት ነው….ደግሞ እንዳላችሁ ባይመቻትም ለ15 ቀን ምንም አትሆንም፡፡አለመመቸትን ማጣጣም በቀጣይ ለሚመጣ መመቸት መደላደል መፍጠር ነው፡፡››
‹‹እሺ ቢያንስ እንሄድና ከሩቅም ቢሆንም እንያት››
‹‹እንደእሱ ይቻላል››አላና ያጠፋውን የመኪና ሞተር አስነሳው፡፡
ሰለሞን መኪናውን ነዳና  ከተካ መኪናው ፊት ለፊት አቆመ….ተካ መኪናውን ከፊቷ ወጣን ወደእነሱ መጣ ..ሰለሞን የገቢናው በራፍ ከፈተለት ……ገባና ቁጭ አለ››
ወደኃላ ዞረና…..‹‹አሁንም ውስጥ ነች…እንዴት ነው ምናደረገው? ››
‹‹ቆይ እስኪ ተረጋጋ ስትወጣ እንያት….››ሁሉም አይናቸውን የግቢው መውጫ መግቢያ ላይ ተከሉ….በርከት ያሉ ሴቶች ሲወጡ ሲገቡ ይታያል፣››
‹‹ምንድነው ብዙ ሰዎች ይታያሉ… ችግር አለ እንዴ?››አቶ ኃይለ ልኡል ጠየቁ፡፡
‹‹አይ ጌታዬ ችግር የለም… እኔም በመጀመሪያ ግራ ገብቶኝ ነበር…ስጠይቅ ግን ፣ሰዎቹ ነገ የማሪያም ፅዋ ማህበር አለባቸው ..የድግሱ ስራ ለማገዝ የመጡ ጎራቤቶች ናቸው››
‹‹እ …እንደዛ ነው….››በፀሎት ወጥታ ከሩቅ ለማየት ከአንድ ሰዓት በላይ በትዕግስት መጠበቅ ነበረባቸው….ግቢ ውስጥ ካለ የማንጎ ዛፍ ስር ቆማ ከአቶ ለሜቻ ጋር እየተሳሳቀች ስታወራ ነበር የተመለከቱት…ሁለቱም ወላጆች ሄደው ልጃቸው ላይ ለመጠምጠም የሚተናነቃቸውን ስሜት በመከራ ነበር የተቆጠጠሩት፡፡ሁለቱም ስሜታዊ ሆነው እንባ አውጥተው እስከማልቀስ ደርሰው ነበር፡፡
‹‹አሁን በቃ ይበቃናል…ከዚህ በላይ እዚህ ከቆየን  ራሳችንን ማጋለጥ ይሆናል…ድንገት እዚህ እንዳለች እንደደረስንባት ካወቀች….ቦታ ለመቀየር ታስብና ዳግመኛ አድራሻዋን ትሰውርብን ይሆናል፡፡››ሰለሞን ነው የተናገረው፡፡
‹‹አዎ ትክክለ ነህ….እንዴት ነው ምናደርገው ታዲያ? እሱ እዚሁ ይጠብቃት አይደል…?››.

‹‹አይ ምንም ጠባቂ አያስፈልግም…ባይሆን በየቀኑ እየመጣ ለተወሰነ ደቂቃ ሰላም መሆኗን ብቻ ካረጋገጠ ይበቃል፣አሁን ሁላችንም ነን አካባቢውን መልቀቅ ያለብን፡፡››ሰለሞን ቁርጥ ያለ ውሳኔውን አስተላለፈ…የተቃወመው ወይም የተከራከረው አልነበረም፡፡
‹‹እሺ ይሁን …..በቃ ተካ አንተም ወደቤትህ ሄደህ እረፍ …ነገ ደውልልሀለው››ብለው አሰናበቱት…‹‹እሺ ጌታዬ እንዳሉ››ብሎ ገቢናውን ለቆ ወረደና ወደአቆማት መኪና ተንቀሳቀሰ…..ሰለሞንም ባልና ሚስቱን ይዞ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ተፈተለከ….

ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
ከመጽሐፍት መንደር
ከመጽሐፍት መንደር
ከመጽሐፍት መንደር

♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ሀያአንድ

ተካ አቶ ኃይለልኡል ባዘዙት መሰረት ሽጉጡን ሙሉ ጥይት ሞልቶ ወገቡ ላይ ከሸጎጠ በኃላ አጉሊ መሳሪያ ያዘና  ማንን ሳያስከትል ቀጥታ መኪና ውስጥ ገብቶ ወደ ቃሊቲ ነዳው….የሰውዬውን ጥርጣሬ ምንም አልተዋጠለትም…‹‹ልጅቷ ስንት አማራጭ እያላት እንዴት እዛ ጭንቁርቁስ ቤት ከጭርቁስቁስ ሰዎች ጋር ለመቆየት ታስባለች? ››ሲል እራሱን ጠየቀ፡፡ ሊዋጥለት አልቻም…፡፡

በፀሎት ከጠፋችበት ቀን አንስቶ በመላ ሀገሪቱ ፍላጋ የተሰማሩትን በመቶ የሚቆጠሩ ግለሰቦችን የሚመራው ..መረጃ የሚቀበለው አዲስ ቦታ ስምሪት የሚሰጠው እሱ ነው፡፡እና የእሱ እቅድ የሆነ ቦታ መኖሯን በሆነ መንገድ ቀድሞ ቢደርስበት እንደምንም ብሎ የራሱ ሰው በሚስጥር እንዲያገኛት አድርጎ በእጅ አዙር 5 ሚሊዬኑን የሽልማት ገንዘብ ለመቀባበል አቅዶ ከልቡ እየሰራ ነበር...እርግጥ እንደዚህ እያደረገ መሆኑን ቀድመው ቢደርሱበት ያለምንም ማቅማማት ግንባሩን በጥይት እንደሚነድሉት እርግጠኛ ነው…ግን በህይወት የተሻለ ነገር ማግኘት ሪስክ መውሰድ የግድ እንደሆነ የሚያምን ስለሆነ ነገሩን ልክ እንደቁማር ነው ያየው..‹‹ወይ በላለሁ..ወይ ደግሞ እበላለው››ብሎ ነበር ውሳኔ ላይ ደርሶ በተግባር ሲንቀሳቀስ የከረመው፡፡…አሁን ሰውዬው እንደሚሉት ልጅቷ የገመቱት ቦታ የምትገኝ ከሆነ ያ ሁ እቅዱ ውሀ በላው ማለት ነው፡፡ቦታውን ራሳቸው ቀድመው አውቀው ስለነገሩት ሽልማት የሚሰጡበት ምንም ምክንያት የለም….መኪናውን ወደእዛ ሲያሽከረክር በውስጡ በፀሎት የተባለው ቤት በፍፅም እንዳትገኝ እየፀለየ ነበር፡፡እንደደረሰ ከመንገድ ማዶ አስፓልት ጠርዝ ላይ መኪናውን ፓርክ አደረገና የመኪናው መስኮት በከፊል ከፍቶ ማጊሊያ መነፅሩን ወደእነ አቶ ለሜቻ ግቢ አነጣጠረና ገቢ ወጪውን መመልከትና በመሀከልም የተለየ ነገር ያገኘ ሲመስለው በሞባይሉ ፎቶ ማንሳት ጀመረ…
ስራ የጀመረው ከጥዋቱ 5 ሰዓት አካባቢ ቢሆንም እሰከ 10 ሰዓት ሁለት ሶስት ጊዜ አሮጊት ሴት ስትወጣ ስትገባ ከማየት ውጭ በግቢው ውስጥ አይን የሚስብ ምንም አይነት እንቅስቃሴ አልነበረም…ሰዓቱ እየረዘመ ሲሄድ ተስፋ እየቆረጠና እየተሰላቸ መጣ…ለዛሬ ይበቃኛል ብሎ 11 ሰዓት ላይ አካባቢውን ለቆ ወደቤቱ ሄደ ..
በማግስቱ በጥዋት ማለዳ አንድ ሰዓት ላይ ነበር የመጣው፣እና ሁለት ሰዓት ላይ የሚፈልገውን አገኘ ..ደጋግሞ ፎቶ አነሳው…በቤቱ አንድ ሴት ልጅ ብቻ እንዳላቸው አጣርቷል ..አሁን እየገቡ እየወጡ ያሉት ግን በተቀራራቢ እድሜ ላይ የሚገኙ ሁለት ወጣቶች ናቸው፡፡አንደኛዋ የቤቱ ልጅ እንደሆነች እርግጠኛ ነው…ሁለተኛዋ ግን የሚፈልጋት የባለፀጋው ቅምጥል ልጅ ትሁን አትሁን መለየት አልቻለም…የለበሰችው ልብስ የተለመደ አይነት ነው..በዛ ላይ ፊቷን ጭንቅላቷን ጭምር በሻርፕ ሸፍናለች…ዝም ብሎ ከመኪናው በመውረድና በእግሩ ወደ አጥሩ በመጠጋት ከቅርብ ርቀት በርከት ያለ ፎቶ አነሳና ለአቶ ኃይለ ልኡል ላከላቸው፡፡

አቶ ኃይለልኡል በዚህ ጊዜ ከባለቤታቸው ጋር በሰለሞን በሚሾፈር መኪና ከቢሾፍቱ ወደአዲስ አበባ እየተመለሱ ነበር፡፡ስልካቸው ድምፅ ሲያሰማ ከኪሳቸው አወጡና ተመለከቱት..መልዕክት መሆኑን ሲያዩ ከፈቱት…አይናቸው ተጉረጠረጠ….
‹‹እራሷ ነች ..ልጄ እራሷ ነች….ከጎናቸው ያለችው ሚሳታቸው ላይ ተጠመጠሙና ጉንጮቾን አገላብጠው ይስሙ ጀመር››
‹‹እንዴ ኃይሌ ምን ተፈጠረ..?ምን ተገኘ..አረ ንገረኝ?››
‹‹ይሄውልሽ..እንቺ እይው..ፊቷን ብትሸፋፈንም እራሷ ነች፡፡››ወይዘሮ ስንዱ ስልኩን ከባላቸው እጅ ተቀበሉና አፍጥጠው ተመለከቱ…..ከባላቸው በበለጠ በመደነቅ ኡኡ.አሉ…መኪናዋን በእልልታ አደባላለቁት…ሰለሞን የነገሩ ውል ስላልገባው መሪውን ጠመዘዘና የመንገዱን ዳር አስይዞ መኪናዋን አቆማት…በራፉን ከፍተው ወረዱ….እሱም ተከትሏቸው ወረደ‹‹አረ ለእኔም ንገሩኝ ምንድነው? እንዲህ የሚያስፈነጥዝ ደስታ፡፡››
‹‹ልጃችን የት እንዳለች አወቅን..እያት ተመልከት››ስልኩን ከሚስታቸው ተቀበሉና ለሰለሞን አቀበሉት..አንድ ፊቷ በቅጡ የማይታይ ወጣት ፎቶ ነው…ግን በፀሎት እንደሆነች ወዲያው ነው ያወቃት..ሙሉ ፊቷን ሳያይ እሷ እንደሆነች አንዴት እንዳወቀ አልገባውም…››
‹‹አየህ …ልጃችን እራሷ ነች…ሰው እንዳይለያት ነው ፊቷን የሸፋፈነችው……››
‹‹ለመሆኑ የት ነው ያለችው?››ጠየቀ ሰሎሞን፡፡
‹‹የት እዳለች ቆይ ነግራችኃላው››ብለው ስልኩን ተቀበሉና ደወሉ
‹‹ሄሎ….ፎቶው ደርሶኛል፡፡››
‹‹አዎ ሳስበው እሷ ትመስለኛለች››
‹‹አዎ እሷ እራሷነች…ከቦታው እንዳትንቀሳቀስ..እዛው ጠብቀን…ከቢሾፍቱ እየተመለስን ስለሆነ ከ15 ደቂቃ በኃላ ያለህበት እንደርሳለን››
‹‹ወጥታ ከሄደችስ…?ላስቁማት››
‹‹አይ..ልጄን ቀጥታ እኔው ነኝ የማገኛት..እንዳታስቆማት ትደነግጥብኛለች…ከቤት ከወጣች ዝም ብለህ በርቀት እየተከታተልክ ያለችበትን ታሳውቀኛለህ፡››

‹‹እሺ..ጌታዬ እንዳሉት አደርጋለው››
‹‹ጎበዝ ..እንዳስደሰትከኝ አስደስትሀለው…ቆንጆ ጉርሻ ይጠብቅሀል ››
‹‹እሺ ጌታዬ››ስልኩን ዘጉና‹‹በሉ ጊዜ አናባክን ..ግቡና እንሂድ››
‹‹እንዴ የት አንዳለች ንገረን እንጂ……?››ወ.ሮ ስንዱ ጠየቁ
‹‹ስንድ ልጃችን ሰዎቹ ጋር ነው ያለችው….››
‹‹የትኞቹ ሰዎች››
‹‹እነአቶ ለሜቻ ጋር..ማለቴ የልብ ለጋሾ ቤተሰብ ጋር ነው ያለችው››
‹‹ወይ ጉዴ….አሁን ምንድነው የምናደርገው?››እያሉ ወደመኪናው ገቡ፡፡ አቶ ኃይለልኡልም ተከትለዋቸው ገቡ….ሰለሞን በሰማው ያልተጠበቀ ነገር ግራ እንደተጋባና ምን ማድረግ እንዳለበት እያሰላሰለ ገቢና ገባ፡፡ መኪናውን አንቀሳቀሳት…ባልና ሚስቶቹ በደስታ ሰክረው እሱን ከቁብ ሳይቆጥሩት እርስ በርስ በፈንጠዝያ ሲጎሻሸምና ሲሳሳሙ እሱ ምን ማድረግ እንዳለበትና ይሄንን ያለጊዜው ያጋጠመውን ነገር እንዴት እንደሚፈታ እያሰላሰለ ነበር የሚነዳው….
አቃቂ አቶ ለሜቻ ቤት ለመድረስ 500 ሜትር ያህል ሲቀራቸው የመኪናውን መሪ ወደግራ ጠመዘዘና ፊት ለፊት ከሚታየው ሆቴል ይዞቸው ገባ..ባልና ሚስቶቹ በድንጋጤ እርስ በርስ ተያዩ
‹‹ሰለሞን…ምን እያደረክ ነው?››አቶ ኃይለልኡል ጠየቁ፡፡
‹መነጋገር አለብን››
‹‹ስለምን?››
‹‹አሁን ልጃቹህ ጋር ከመሄዳችሁ በፊት አረፍ ብለን መነጋገር አለብን››
‹‹ምን መነጋገር ያስፈልጋል…?በቃ እኔና እናቷ ሄደን ልጃችንን ወደቤት ይዘን እንሄዳለን….እንደምታየው  አሁን  ሁሉ  ነገር  ውብ  እና  የተስተካለከለ  ነው..አይዞህ

አታስብ…ከንተጋር  ያለንን  ነገር  እንቀጥላለን..ከሶስት  ቀን  በኃላም  ወደአልከው  ቦታ ትወስደናለህ››
መኪናውን  አቆመና  ሞተሩን  አጥፍቶ  ወደኃላ  ዞረ..ፊት  ለፊት  እያያቸው‹‹ይሄ  ነገር እንደምታስብት ቀላል ይመስላችኃላ?››
‹‹ማለት?››
‹‹አሁን ያለችበት ቤት ሄደችሁ በማንኳኳት..ነይ ልጄ በቃ አግኝተንሻል አሁን ወደቤትሽ ተመለሺ ብትሏት ..እሺ ብላ በደስታ ዘላ የምትጠመጠምባችሁ ይመስላችኃላ…እምቢ መሄድ አልፈልግም ብትል ምን ታደርጋላችሁ ?በግድ በጎረምሳ አሳዝላችሁ መኪና ውስጥ በመክተት ወደቤት ትወስዷታላችሁ….?ከዛስ..?አንድ ክፍል ውስጥ ቆልፋችሁባት በራፍ ላይ ሁለት ጠብደል ጠባቂ ታቆማላችሁ?እስኪ ንገሩኝ ምንድነው የምደርጉት?› በድንጋጤ እርስ በርስ ተያዩ‹‹በእውነት እምቢ ብትለን ምንድነው የምናደርገው?›ወ.ሮ ስንዱ በተሰበረ ድምፅ ባላቸውን ጠየቁ፡፡


ጥቅም አልባ ነው። ለፍቅረኛ ወይም ለትዳር አጋር የሚኖር አክብሮት ጥልቅና ሩቅ መሆን አለበት። ከልብ የመነጨ ብቻ ሳይሆን ከነፍስም የተጨለፈ መሆን አለበት።ሚስት ለባሏ ሚስት ብቻ አይደለችም..የሴት ጓደኛ…የእናት ምትክ ዘመድ ጭምር መሆን አለባት..ባልም ለሚስቱ ወንድ ጓደኛ..ከዛም አልፎ የአባት ምትክ ዘመድ መሆን አለበት፡፡የማወራው ግልፅ ነው አይደል?››
‹‹አዎ ..በጣም ግልፅ ነው..ቀጥል››

ትንፋሽ ወስዶ ከንፈሩን በምራቁ አረጠበና ንግግሩን ካቆመበት ቀጠለ‹‹…ከቤት ወጥታችሁ ስትለያዩ የሚኖር ሽኝት እና ከውጭ ውላችሁ ስትመለሱ እርስ በርስ የሚኖር የሞቀ አቀበል በጣም ወሳኝ ኩነት ነው።ተሳሳሞ ደህና ዋል..ደህና ዋይ ተባብሎ መለያየት እና ሲገናኙ እንዴት ዋልሽ…?እንዴት ዋልክ? ተባብሎ በናፍቆት መሳሳም በመሀከል ያለን ግንኙነት ያደረጃል ፍቅርም ግለቱን ጠብቆ እንዲጓዝ ያግዛል።በመጨረሻው ሚቻላችሁ ከሆነ እቤት ከገባችሁ  በኃላ  ለተወሰነ  ሰዓት  ስልክ  የሚጠፋበት  እና  ቲቨ  የሚዘጋበት  ልዩ የሆነ የቤተሠብ የጋራ የመጫወቻና የመወያያ ሰአት ቢኖር እንደቤተሠብ ለሚኖር መስተጋብር ትልቅ ጠቀሜታ ይኖረዋል።
‹እና ሌላው ልጃችሁ ላይ ያላችሁ አቋም ትልቅ ማስተካከያ ሊደረግበት ይገባል፡፡››
‹‹ማለት?››
‹‹በፀሎት ነገሮች ተስተካክለው ወደቤት ስትመለስ..ለምሳሌ ስትወጣ ስትገባ በጋርድ እንድትጠበቅና እንድታጀብ ማድረግ አይገባችሁም..እንደማንኛውም ሰው በነፃነት ከፈለገችው ሰው ጋር ወጥታ ከፈለገችው ጋር የመመለስ መብት ሊኖራት ይገባል፡፡››
‹‹ሰለሞን እዚህ ላይ አንድ ያልገባህ ነገር አለ…እኔ እኮ ልጄን በጋርድ ማስጠብቀው ወድጄ አይደለም…..ልጄ ልብ በሽተኛ ነኝ..የልብ ንቅለ ተከላ ተደርጎላታል …በጣም ጥንቃቄ የምትፈልግ ልጅ ነች..ድንገት መንገድ ላይ ወድቃ አጉል እንዳትሆንብኝ ስለምሰጋ ነው ዘወትር ሰዎች በዙሪያዋ እንዲሆኑ የማደርገው፡፡››ሲሉ ተቃውሞቸውን ያሰሙት አቶ ኃይለልኡል ናቸው

‹‹ቢሆንም ለዛ መፍትሄው ያ አይደለም….ይሄ የልጅቷን ነፃነት ከመንፈጉም በላይ በራስ የመተማመን ችሎታዋን በጣም ይጎዳዋል…በየሄደችበት በሰው መጠበቅ የመታፈን ስሜት እንዲሰማት ነው የሚያደርጋት፣እና የእዛ ውጤት ደግሞ እንዲህ አሁን እንዳደረገችው ራሷን ነፃ ለማውጣት አላስፈላጊ ጣጣ ውስጥ እንድትገባ ትገደዳለች››
‹‹ትክክል ልትሆን ትችላለህ …ግን ያው ነፃ ትሁን… ብቻዋን ትንቀሳቀስ ብዬ ከፈቀድኩላት አንዳንድ አላስፈላጊ ቦታዎች ትሄድና የማይሆን ነገር ትሰራለች፡፡››
‹‹ለምሳሌ የት?››
‹‹ይሄውልህ የልብ ንቅለ ተከላ ሲደረግላት ልብ የሰጠቻት ልጅ ቤተሰቦች እዚሁ አዲስ አበባ አቃቂ አካባቢ ነው የሚኖሩት ..ልጄ አሁን አሁን ተወች እንጂ በፊት ሰሞን ቀንና ሌት እዛ ካልወሰድከኝ እያለች ታስቸግረኝ ነበር፣..እኛ ደግሞ ከልጅቷ አባት ጋር ስንስማማ በምንም አይነት ከእኛ በአካል መገናኘት እንደማይፈልጉ ነው ያነገሩን..እሷ ቤታቸው ሄዳ ቢያገኟት ልጃቸውን ስልምታስታውሳቸው ሀዘናቸውን ክፉኛ ትቀሰቅሳባቸዋለች.. እንደዛ አይነት ውለታ የዋሉልኝን ሰውዬ ደግሞ የማይፈልጉትን ነገር ማድረግ ላሳዝናቸው አልፈልግም..አንድ ለዛ ነው የማስጠብቃት››ንግግራቸውን እየተናገሩ ሳለ የሆነ እስከዛሬ ያላሰብት ገራሚ ሀሳብ በአእምሯቸው ብልጭ አለ….እንዴት እሰከዛሬ ትዝ ሊላቸው እንዳልቻለ ግራ ገባቸው‹‹ልጄ እነሱ ጋር ሄዳ ቢሆንስ?››ሀሳቡን በውስጣቸው አፍነው ያዙት፡፡
‹‹የልጃችሁን ደስተኝነትና ሳቅ የምትፈልጉ ከሆነ ለችግሮች ሁሉ ሌላ መፍትሄ አበጁላቸው..ደግሞ ለበፀሎት በግልፅ ነገሮችን ቢያስረዶት ይገባታል…ብስልና አስተዋይ የ22 ዓመት ወጣት ነች….ይልቅ እናንተ  በመሀከላችሁ ያለውን ችግር ፈታችሁ ሰላም ከሆናችሁና ስትወጣ ስትገባ የሚከታተላት ሰው መመደብ ካቆማችሁ የልጃችሁን ደስታና ሳቅ መመለስ ብቻ ሳይሆን መቼም መልሳችሁ አታጦትም››
ወ.ሮ ስንዱ መለሱ ‹‹እሺ እንዳልክ እናደርጋለን….ኃይሌ እንዲህ ማድረግ ያቅተናል እንዴ?››
‹‹አረ አያቅተንም..ችግር የለውም ሁሉን ነገር እኔ አስተካክለዋልው..አሁን ከፈቀድክልኝ ወደካማፓኒው አንድ አጭር ስልክ መደወል አለብኝ..ከባድ የስራ ጉዳይ ነበረ ..ምን እንዳደረሱት ልጠይቃቸው፡፡››

‹‹ችግር  የለም..በቃ  ጨርሰናል..አሁን  ለጥዋት  ጉዙ  እቃችንን  መሸካከፍ  መጀመር እንችላለን፡፡››
‹‹ጥሩ…››ብለው ቀድመው ከመቀመጫቸው ተነሱና  ወደክፍላቸው በመሄድ ስልካቸውን ካስቀመጡበት አንስትው በጀርባ በኩል ባለው በር ከቤት ወጡ….  ስልክ ደወሉ…
‹‹ስማ አቃቂ ለልጄ ልብ የሰጠቻት ልጅ ቤተሰቦችን ታውቃቸወላህ አይደል..?››
‹‹አዎ አውቀዋለው››
‹‹አሁኑኑ እዛ ሂድና ቀስ ብለህ ማንም ሳያይህ ወደቤታቸው የሚገባውንና የሚወጣውን ሰው ተከታተል…ከተቻለህ ሁሉንም ፎቶ አንሳ››
‹‹እሺ….ግን በቀጥታ ምን ለማጣራት ነው የምንፈልገው…?ነገሩን ማወቄ ስራዬን ያቀልልኛል››
‹‹አዎ….ምን መሰለህ..ለማንም እንዳትናገር..ልጄ ምን አልባት እዛ ቤት ተደብቃ ይሆናል የሚል ጥርጣሬ አድሮብኛል…እና ከአሁኑ ጀምረህ በቃ እስክልህ ደረስ እንዳልኩህ ተከታተለልኝ…እሷን በተመለከተ የሆነ ትንሽም ቢሆን ፍንጭ ካገኘህ ወዲያው አሳውቀኝ፡፡››
‹‹ስልኩን ዘጉና ኪሳቸው ውስጥ ከተው ወደውስጥ ተመለሱ …ወ.ሮ ስንዱ አልጋቸው ላይ አረፍ ብለው አገኞቸው ፡፡በራፉን ዘጉን የራሳቸውን አልጋ ትተው ወደባለቤታቸው ሄዱና ከጎናቸው ተቀመጡ፡

ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
ከመጽሐፍት መንደር
ከመጽሐፍት መንደር
ከመጽሐፍት መንደር

♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ሀያ

‹‹አግብተሀል እንዴ?››
ድንገት ከርዕሳቸው ውጭ የሆነ ጥያቄ ስለጠየቁት ድንግርግር አለው፡፡
‹‹ለምን መሰለህ የጠየቅኩህ..?እንዲሁ ሳስበው አንተን ያገባች ሴት በጣም እድለኛ ትመስለኛለች….፡፡››
‹‹ምን አልባት ልትሆን ትችላለች ..እስከአሁን ግን አለገባሁምም አረ እንደውም ፍቅረኛም የለኝም››
ፈገግ አሉ….‹‹ሸክላ ሰሪ በገል ይበላልል›› አሉ…ብዙ ማወቅም እኮ መጥፎ ነው››
‹‹እንዴት?››
‹‹የምትፈልገውን ሁሉ የምታሟላ ሴት ለማግኘት በጣም ይከብድሀላ…ሁሉን ነገር አሟልታ ጥንቅቅ ያለች ሴት አታገኝም..በዛ እርግጠኛ ሆኜ ልነግርህ እችላለው…ግን ምትወድህና ምትወዳት ልጅ ሆና እራሷን ለመለወጥና ለማሻሻል የምትጥር ከሆነ በቂ ነው…አንተ ጎበዝ አንደበተ ርትኡ ባለሞያ ስለሆንክ መስመር ታስይዛታለህ››
እንዴት ብሎ መምከሩን ትቶ ተመካሪ እንደሆነ አልገባውም፡፡‹‹እሺ…የእናንተን ጉዳይ ከዳር ካደረስኩ በኃላ አስብበታለው….ምን አልባት እናንተ ትሆናላችሁ የምትድሩኝ…››
‹‹ለዛውም ድል ባለ ድግስ ነዋ››

‹‹እሺ..አሁን ይበቃናል…የምሳ ሰዓት ስለደረሰ ወደሳሎን እንሂድ››
‹‹አዎ ..ይበቃናል..ይሄኔ ኃይሌ ብቻውን ደብሮታል››
ፈገግ እለ ….. ከመቀመጫው ተነሳና ወደውጭ መራመድ ጀመረ…ወ.ሮ ስንዱም ተከተሉት፡፡


ከሳምንት በኃላ……..
በቢሾፍቱ ቆይታቸው በባልና ሚስቶቹ መካከል አስገራሚ የሚባል ለውጥ ነው የታየው፡፡ቢያንስ እረስ በርስ በመሀከላቸው ያለ ንግግር የጥሩ ጓደኛሞች መምሰል ከጀመረ ሰነባብቷል…ይሄ ለውጥ ሰለሞንን ይበልጥ እንዲበረታታ እና ሙሉ ኃይሉን ስራው ላይ እንዲያውል አግዞታል፡፡
‹‹እንግዲህ ዛሬ የመጨረሻ ቀናችን ነው ነገ ወደአዲስአባ እንመለሳለን…ሶስት ቀን እረፍት እንወስድና ምን አልባትም ለመጨረሻ ጊዜ ለሌላ 15 ቀን ወደሌላ መዝናኛ ቦታ እንሄዳለን፡፡በቀጣይ የምንሄድበት ከዚህ የተለየ ነው…ሌሎች ሰዎች ማለቴ ጎብኚዎች የሚኖሩበት ቦታ ነው…እዛ ምንሄደው ነፃ ሆናችሁ እንድትዝናኑ ነው..እኔም አብሬያችሁ ኖራለው ግን ነፃ ናችሁ…እዚህ እንዳለው ብዙ ማዕቀብና እገዳ የለም…ስልካችሁን እንደፈለጋችሁ መጠቀም ትችላላችሁ.ሰሻል ሚዲያ ቴሌቪዝን ማየት ትችላላችሁ …ከሰው መተዋወቅና መገባበዝ ትችላላችሁ..አንድ ማትችሉት ነገር መለያየት ብቻ ነው….ለ15 ቀን የምታደርጉትን ሁሉ አብራችሁ ታደርጋላችሁ..››
‹‹ገባን ..ያልከው 15 ቀን የመጨረሻችን ይመስለኛል››
አዎ እኔም እንደዛ ነው የማስበው..በእውነት እዚህ ባሳለፍነው 15 ቀን ሁለታችሁም ካሰብኩት በላይ ከፍተኛ ጥረት አድርጋችኃል …እናም ትልቅ ለውጥ እንዳመጣችሁም ይሰማኛል…እናንሰትስ ምን ይሰማችኃል…?አቶ ኃይለልኡል እስኪ ከእርሶ ልጀምር፡፡

‹‹እኔ በጣም ደስተኛ ነኝ…እስከዛሬ ሚሲቴን ብቻ የምበድል መስሎ ነበር የሚሰማኝ ለካ ልጄንም ራሴንም ጭምር ነበር እያሰቃየው የነበረው….እውነት አንተና ልጄ የእድሜ ልክ ባለውለታዎቼ ናችሁ››
ፊቱን ወደወ.ሮ ስንዱ ዞረና ተመሳሳዩን ጥያቄ ጠየቃቸው፡፡
‹‹አዎ…ኃይሌ እንዳለው ደስተኛ ነን…በፊት ሁሉን ነገር እርግፍ አድርጌ ገዳም ገብቼ መመልኮስ ነበር ምኞቴ ..ምክንያቱም ህይወት አስጠልታኝ ነበር…ቤቴም ኑሮዬም ይቀፈኝ ነበር…ጨለማ የሆነ ሀዘን ውስጥ ገብቼ ነበር..አንድ ያለችኝ አስደሳች ነገር ልጄ ብቼ ነበረች
..እሷም ከጠፋች በኃላ ደግሞ ነገሮች ለእኔ ምን ያህል አስቸጋሪ እንደሚሆኑ መገመት ቀላል ነው…አሁን ግን እንደዛ አይደለም የሚሰማኝ….ደግመኛ እንደመወለድ አይነት የመታደስ ስሜት እየተሰማኝ ነው…የመከራና የሀዘን ቆዳዬን ከላዬ ገፍፌ ጥዬ በአዲስ ተስፋና ፍቅር ተወልጄለሁ..አሁን ቤቴም ባሌም ይናፍቁኛል….ሃይሌን ከዚህ በፊት ለሆነው ሁሉ ይቅር ባዬዋለሁ.. እሱም ይቅር እንደለኝ ገምታለው፡፡››
ኃይለልኡል ተፈናጥረው ከመቀመጫቸው ተነሱና ሚስታቸው ላይ ተጠመጠሙ…ሁለቱም ተቃቅፈው መላቀስ ሲጀምሩ….ሰለሞንንም ስሜታዊ አደረጉት፡፡ተላቀው ወደቦታቸው ለመመለስ..ከ10 ደቂቃ በላይ ፈጅቶባቸዋል፡፡
ሰለሞን ንግግሩን ቀጠለ‹‹ጥሩ እንግዲህ… እዚህ ደረጃ ላይ ከደረስን አንዳንድ አጠቃላይ ስለሆኑ ነገሮች እናውራ፡፡ያው እናንተ በጋብቻ ውስጥ ረጅም እድሜ ስለአሰለፋችሁ ከእኔ የበለጠ ልምድ እንዳላችሁ አውቃለሁ....አሁን የማወራው የምታውቁትን ነገር ነው…ላሳውቃችሁ ሳይሆን ላስታውሳችሁ ፈልጌ ነው››
‹‹ጥሩ እየሰማንህ ነው ….ቀጥል››
‹‹እንግዲህ እቤት የባል ብቻ አይደለም፣የሚስትም ብቻ አይደለም፣ እቤት የልጆችም ጭምር ነው።በዚህ ምክንያት ለሁሉም ኑዎሪዎች እኩል ምቹ መሆን አለበት።እናንተ ከአሁን ወዲያ በቤታችሁ የሚዘረጋው ስርአት ህግና የአኗኗር ዘየ..ሶስታችሁን በእኩል ከግምት ያስገባ መሆን አለበት፡፡ሌላው ንብረታችሁን በተመለከተ የእኔ የሚለውን ቃል ከመጠቀም የእኛ የሚለውን የጋራ ቃል መጠቀም የተሻለ ነው።የእኛ ቲቪ..የእኛ ቤት...የእኛ ጊቢ የእኛ ፋብሪካ፣ብሎ የመናገር ልምድ ሊኖራችሁ ይገባል።እያንዳንድ የቤተሰብ አባል የእዛ ቤተሠብ

የአክሰዬን ባለድርሻ ናቸው።ያንን ደግሞ በተግባርም በስነ-ልቦናም መረጋገጥ አለበት።በቤተሰብ ቢዝነስ ውስጥ ስለሚፈጠር ዋና ዋና ክስተት ስለትርፍም ሆነ ኪሳራ ሁሉም ሰው በተገቢው መጠን መረጃ ሊኖረው ይገባል….ሁሉንም ኃላፊነት አንዱ አካል ብቻ ጠቅልሎ መውሰድ የለበትም…እዚህ ላይ በተለይ አቶ ኃይለልኡል ብዙ ነገር ማስተካከል የሚጠበቅቦት ይመስለኛል››
‹‹ገብቶኛል..እሺ…አስተካክላለው፡፡››

‹‹ሌላውና ወሳኙ … የተለየ ችግር ከሌለ በስተቀር ባልና ሚስት መኝታ ክፍላቸውንም ሆነ አልጋቸውን መለየት የለበቸውም…በተጨማሪም ባልና ሚስት በምንም አይነት ሁኔታ ወደመኝታቸው ሲሄድ አኩርፈውና በውስጣቸው ተበሳጭተው ወይ ቂም ይዘው መሆን የለበትም።መኝታ ክፍል ለባለትዳሮች እንደቤተመቅደስ ነው መሆን ያለበት ። የሚሳሳሙበት... የሚተቃቀፉበት.... የሚዋደድበትና የሚፋቀሩበት ….ስለጋብቻቸው እና ስለልጆቻቸው ደህንነትና ሰላም የሚማከሩበትና የሚፀልዩበት የገመና መክተቻ ቦታቸው ነው መሆን ያለበት ። ስለዚህ ... ቅያሜያቸውን ሆነ ቅሬታቸውን ሳሎን ጨርሰው ለጭቅጭቃቸው መፍትሄ አበጅተውለት እና ይቅር ተባብለው ነው በሳቅና በፈገግታ ወደመኝታቸው መሄድ ያለባቸው። አዎ ወደመኝታ ክፍላቸው ሲያመሩ በፍፁም ሰላምና ፍቅርና መሆን አለበት...የበለጠ ለመፍቀር...የበለጠ ለማረፍና ..የበለጠ ለመታደስ ።ይሄ ሁለታችሁንም በእኩል ደረጃ የሚመለከት ጉዳይ ነው፡፡››
ሁቱም አንገታቸውን እላይ እታች በማነቃነቅ መስማማታቸውን ገለፁ ‹‹ሌላው በቤት ውስጥ አንደኛው ሌለኛውን ማገልገል አለበት...ማገልገል ማለት በፍፅም ፍቃደኝነትና ፍላጎት አንደኛው ሌላኛውን መርዳት ማለት ነው።ባል የቤቱ ንጉስ ከሆነ ሚስት ደግሞ ንግስት ነች ማለት ነው ልጆች ደግሞ ልኡላን ናቸው።ማንም ከማንም የበለጠ አስፈላጊ አይደለም...ማንም ከሌላኛው ያነሰ አይደለም።ለቤቱ ሙሉነትና ፍፁምነት ሁሉም የየራሱ ኃላፊነትና ድርሻ አለው።በፍቅርና በጋብቻ ህይወት ውስጥ እርስ በርስ ያለ መከባበር በጣም ወሳኝ ነው።አንድ ለሌላዎ ጥያቄዎችን አስተያየቶችን ሲኖሩት በትህትና እና ክብር በተሞላ ሁኔታ ጥያቄውን ማቅረብ አለብት።እርስ በርስ ያለ ግንኙነት የማስመስል መሆን የለበትም...እንግዳ ሲኖር የሚደረግ አርቴፊሻል የማስመሰል እንክብክቤ እና አክብሮት


በነጭ ምዕመናን ታቦቷ ታጀበ
ዲያቆኑ ተነሳ ሊቃችን ወረበ

ጭብጫቦ እልልታው
     ዝማሬው ይበልጣል
ማርያም ማርያም ሲባል
      ስምሽ ይጣፍጣል።

ማርያም

ዮኒ
    ኣታን #yonatoz


እያልን ብና እንጠጣ››
‹‹ጥሩ….እንሄድ››ብለው ሶስቱም ከተቀመጡበት ተነሱና እቤቱን ለቀው ወጡ


////




በማግስቱ…….
ሰሎሞን ባለትዳሮችን ቢሾፍቱ ይዞ ከከተመ አራተኛ ቀኑ ነው፡፡የዛሬው ፕሮግራም ሁለቱን በተናጠል ማነጋገር ስለሆነ አሁን ከወ.ሮ ስንዱ ጋር አንድ ክፍል ውስጥ ለብቻ ፊት ለፊት ቁጭ ብለው እያወሩ ናቸው፡፡
‹‹ወ.ሮ ስንዱ አሁን ነገሮች እንዴት እየሄዱ ነው?››
‹‹እድሜ ላንተ …ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ነው…ከስንት ዓመት በኃላ ከኃይሌ አንደበት መልካም ነገር መውጣት ጀምሯል››
‹‹ጥሩ እንግዲህ ሰው ምን ጊዜም ከስህተት ጋር ሚኖር ፍጡር ነው፡፡ከሰው ጋር ስንኖር ስህተት ፈላጊ ከሆን በማንኛውም ሰው ላይ ከመጠን ያለፈ ስህተቶችን በቀላሉ ማግኘት እንችላለን…..ያ ደግሞ ከሰው ጋር አያኖኑረንም…አንዳችን የሌላችንን ክፍተት ለመድፈን መፈጠራችንን እስካላሰብን ድረስ ምንም ነገር ሰላም ሊሆን አይችልም፡፡››

‹‹ትክክል ነህ..በህይወት ዘመናችን አውቀንም ሆነ ሳናውቅ…እርስ በርስ በጣም ተጎዳድተናል…በእልህም በጥፋት ላይ ጥፋት እየደረብን የሁለታችንንም ጣር ስናበዛው ነበር››
‹‹ያለፈው አፏል..አሁን ማሰብ ለነገው ነው፡፡የትናንቱን ጥፋት እያነሳን የምንመረምረው ከልባችን ይቅር እንድትባባሉ እንዲያግዛችሁ እና ዳግመኛው ተመሳሳይ አይነት ስህተት በህይወታችሁ እንዳትሰሩ ነው፡፡››
‹‹ገብቶኛል ልጄ በጣም ገብተኛል..ግን ምን መሰለህ ሀይሌ አንዳንዴ እንዲህ እንደምታየው አይምሰልህ… ህፃን ሆኖ የህፃን ስራ ሲሰራ ታገኘዋለህ ››
‹‹ውቃለው ይሄ የእሷቸው ብቻ ሳይሆን የብዙ ሰዎች ባህሪ ነው….ሰባ አመት ቢሞላን እንኳን ሁላችንም ውስጥ ሳያድግ ህፃን እንደሆነ የሚቀር ማንነት አለ…ሁሌ ውስጣችን ሆኖ ስነልቦናችንን የሚያናውፀው…እናታችን ጉያ ውስጥ እንድንወሻቅ የሚያስመኘን …አባታችን ጭንቅላታችንን እንዲዳብሰንና አይዞህ እንዲለን የሚያስናፍቀን…..አያጂቦ የሚያስፈራን ጭራቅ በህልማችን የሚመጣብን… አዎ ሳያድግ በጮርቃነት የቀረ ማንነት አለን….ለዛ ነው ልጅነት ላይ በሆነ ጎኑ የተሰበረ ሰው አድጎም በቀላሉ ጤነኛ መሆን የማይችለው….ለዛ ነው ጉዳቱ የሚያሳድደው..ለዛነው አንዳንድ ጉድለተችና የህይወት ሽንቁሮች የእድሜ ልክ ህመም ሆነው የሚቀሩት..ልጅነታችን ላይ ተጠጣብቀን እንድንቀር የሚያስገድደን፡፡››
እንግዲህ እኔ አሁን ሁሉን ነገር እርግፍ አድርጌ ትቼ ከእሱ ለመስማማት ነው የምፈልገው…ግን ሰላማችን ምን ያሕል ይቆያል ?የሚለውን በእርግጠኛ ሆኜ ለማንም ማስተማመኛ መስጠት አልችልም››
‹‹ይገባኛል…የእርሶ ግምት ወደፊት በግንኙነታችሁ እንቅፋት ሊሆነ ይችላል ብለው የሚያስብት ወይም የሚያሰጋዎት ነገር ምንድነው?››
‹‹ይሄማ ግልፅ ነው…እንደምታየኝ እኔ እድሜዬ አምሳ ሞልቷል….ልክ እንደሀያ አመት ወጣት ላስደስተውና ፍላጎቱን ሁሉ በሚፈልገው መልክ ላሟላለት አልችልም..እሱ ደግሞ ከእንቡጦች ጋር መቅበጥና መዳራት ለምዶል፡፡››
‹‹ይሄውሎት ወ.ሮ ስንዱ ..ወሲብ ብቻውን ለወንድ ልጅ በቂ አይደለም፣አንድ ሚስት ለባለቤቷ ሌላ ማንኛውም ሴት ልትሰጠው የምትችለውን ነገር ሊኖራት ያስፈልጋል።ወንድ

በወሲብ ስለተመቸችው ብቻ ከአንድ ሴት ጋር ለዘላለም አብሯት አይኖርም። ወንድ ልጅ ሚስቱ ክብር እንድትሰጠው ይፈልጋል።››
‹‹አዎ ..እሱስ ትክክል ነህ …በዚህ በዚህ ብዙ ጥፋት አለብኝ..ሁልጊዜ እሱን መከራከርና ንግግሩን ሁሉ በመቃረን ማሸማቀቅ ሆነ ብዬ የማደረገው የዘወትር ድርጊቴ ነው፡፡››
‹‹አዎ…ወንድ ልጅ አንድ ገበያ ህዝብ ቢንቀው መታገስ ይችል ይሆናል ..የምታፈቅረውን ሴት ወይም የባለቤቱ ንቀት እና ችላ ባይነት የሚቋቋምበት ምንም አይነት ፅናት የለውም።‹ሴት የላከው ሞት አይፈራም› የሚባለው ለምን ይመስሎታል…አንድ ሴት የምታፈቅረውን ወንድ አክብራ አበረታታ በትህትና ምንም ነገር እዲያደርግላት ብትጠይቀው አይኑን ሳያሽ
ያደርገዋል ለማለት ተፈልጎ ነው››
‹‹ገባኝ ልጄ ይሄ የእኔ ትልቁ ስህተት ነው..እንደማርመው ቃል ገባልሀለው››
‹‹ጥሩ…እንግዲህ ቅድም እንዳሉት ወሲብ ላይ ያሎትን ነገር ብዙም አይጨናነቁበት …በመሀከል ያለ ጥልና ጭቅጭቅ ሲወገድ..ፍቅርና መተሳሰብ በቦታው ሲተካ የወሲብ ችሎታውም ሆነ አምሮቱ አብሮ ይመጣል…ደግሞ ያው ሁላችንም እንደምናውቀው ወሲብ እርካሽና ገንዘብ ያለው ሁሉ ሊገዛው የሚችል ነገር ነው።አንድ ሚስት  ስብዕናዋን ከወሲብ በላይ በሆኑ ነገሮች መገንባትና ማነፅ አለባት። ወንድ ልጅ እራሷን በሜካፕ ዲኮር ከምታደርግ ሴት ይልቅ ለችግሮች መፍትሄ የማመንጨት ብልሀት ባላት ሴት ይሳባል።አንድ ሴት ወንዶች የሚፈልጉትን ነገር ሳይሆን ሁል ጊዜ ባሏ የሚፈልገውን ነገር ማድረግ አለባት፡፡" በፍቅር የተሠራ ኃጢአት ፍቅር ከሌለበት አምልኮ ይበልጣል›ይባላል፡፡››
‹‹አልገባኝም ይህ ደግሞ ምን ማለት ነው?››
‹‹ይህ ማለት ወንዶች ሁሉ ወንድ በመሆናቸው ብቻ አንድ አይነት አይደሉም ለማለት ነው…አንድ ሚስት የባለቤቷን ልዩ ባህሪዎች ጥንቅቅ አድርጋ ማወቅ አለባት…ምን ይወዳል..?ምን ይጠላል…?ምን አይነት ምግቦች ይመቹታል…?ምንአይነት መጠጥ ያስደስተዋል…?ሚስቱ ምን አይነት ልብስ ስትለብስ ፊቱ ይፈካል…?የመሳሰሉትን ዝርዝር ባህሪዎችኑ ማወቅና ያንን ታሳቢ አድርጎ መንቀሳቀስ ይጠበቅባታል…ይሄ ለወንዱም ይሰራል፡፡ አንድ ሚስት እሷ ሴት ስለሆንች ባለቤቷም ሌላ ሴት እንደሆነ ማሰብ የለባትም።በሁለቱ መሀከል የማይካድ የጻታ ልዩነት አለ፡፡የፃታ ልዩነት ማለት ደግሞ የባህሪ እና የፍላጎትም ልዩነትም ጭምር ማለት ነው።

‹‹አዎ ..እሱስ እውነትህን ነው››
‹‹አዎ..ለምሳሌ ባሎች ቢያንስ በሳምንት አንድ ቀን ሚስታቸው በቀጥታ በእጆቾ ያበሰለችውን ምግብ መመገብ በጣም ያስደስታቸዋል… ሌላው ሁል ጊዜ ችግር እያወራች
ከምታማርር እና ሁሉን የውጭ ስራዎች ባሏ እንዲሰራቸው ከምትጠብቅ ሴት ይልቅ ጀግና እና ችግርን ፊት ለፊት ለምትጋፈጥ ሴት ክብር አለው። ››
‹‹አሁን  ምን  እንደተረዳሁ  ታውቃለህ..አንዳንድ  ጥቃቅን  ናቸው  ብለን  ትኩረት የማንሳጣቸው ነገሮች በህይወታችን ትልቅ ዋጋ እንደሚያስከፍሉን ነው፡፡››
‹‹አዎ ትክክል ብለዋል››
‹‹አግብተሀል እንዴ?››
ድንገት ከርዕሳቸው ውጭ የሆነ ጥያቄ ስለጠየቁት ድንግርግር አለው

ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
ከመጽሐፍት መንደር
ከመጽሐፍት መንደር
ከመጽሐፍት መንደር

♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-አስራዘጠኝ

ሰሎሞን ሁለቱን ባለትዳሮች ፊት ለፊት አስቀምጦ እያወራ ነው፡፡‹‹የፈለገ ጥረት ብናደርግ ለእያንዳንዱ ብሎን የራሱን ትክክለኛ መፍቻ ካልተጠቀምን ልንፈታው አንችልም!! በህይወታችንም ውስጥ ችግሮች ሲያጋጥሙን ተረጋግተን ለችግሩ ትክክለኛ የመፍትሄ ሀሳብ ማስቀመጥና ለተግባራዊነቱ መንቀሳቀስ ካልቻልን እንዲሁ ስንባክን እና በችግሩ ውስጥ ስንዳክር ነው የምንኖረው፡፡ይሄንን በስራ አለም በትክክል እየተገበራችሁ ውጤታማ እንደሆናችሁ አውቃለው…በትዳር ህይወታችሁስ?ዋናው ጥያቄ እሱ ነው፡፡››
አቶ ኃይለልኡል ተቀበሉት‹‹ገብቶናል…እንደምንም ብለን በመሀከላችንን የተፈጠረውን ክፍተት በማስወገድ እና ፍቅራችንን መመለስ እንዳለብን በደንብ ተረድተናል…አዎ እንደምታየውም ጥሩ መሻሻል እያሳየን ይመስለኛል፡፡››
ሰለሞን ቀጠለ‹‹ጥሩ ግን ፍቅር ብቻውን በሰላም ለመኖር በቂ አይደለም፡፡በመሀከላችው ምንም አይነት ጥል የሌለ ጥንዶች በመሀከላቸው ፍቅር እንዳለ እርግጠኛ መሆን አይቻልም…እንደዛውም ዘወትር በነጋ በጣባ የሚጣሉና የሚጨቃጨቁ ጥንዶችም በመሀከላቸው ያለው ፍቅር አልቋል ወይም ቀዝቅዞል ማለት አይደለም….ከዛ ይልቅ እንዴት እርስ በርስ እንደሚግባቡ እና አንዱ የአንዱን ፍላጎት እንዴት እንደሚረዳ አልገባቸውም ማለት ነው፡፡ስለዚህ አሁን መልሳችሁ ማደስ የሚገባችሁ ፍቅራችሁን ብቻ ሳይሆን እርስ በርስ የመግባባት ችሎታችሁንም ጭምር ነው፡፡አንዳችሁ ሌላችሁን በጥልቀት ለመረዳት እስከምን ድረስ ለመጓዝ ትፈቅዳላችሁ?ይሄ ወሳኝ ጥያቄ ነው፡፡››

ወ.ሮ ስንዱ ለመጀመሪያ ጊዜ ተናገሩ‹‹ትክክል ነህ ልጄ… ለፍቀራችን መበላሸት ዋናው ምክንያት እንደውም እርስ በርስ የመግባባት ችሎታችን ስለተበላሸ ነው….እሱም እኔን እኔም እሱን ለመረዳት ምንም የምናደርገው ጥረት አልነበረም…ሁለታችንም እርስ በርስ እንከን ነበር የምፈላለገው….ያንን በደንብ ተረድቼለው፡፡››
‹‹አዎ ይሄ ችግር የእናንተ ብቻ ሳይሆን የአብዛኛው ባለትዳር ችግር ነው…አንድ ሰው በፍቅር ሲወድቅ በመጀመሪያ ስለራሱ ምቾና ደስታ እንጂ ስላፈቀረው ሰው ደህንነት አይደለም የሚጨነቀው…ሁለቱም ተጣማሪዎች በጋብቻ ጥምረት ውስጥ ለእነሱ የሚመች ሰፋ ያለ ግዛት ቶሎ ብሎ ለመያዝ ይጣጣራሉ…ሁለቱም ተመሳሳይ ፍላጎት ስላላቸው ፍትጊያ ይፈጠራል…አንዱ የሌለኛውን ድምበር ማለፍ…ይሄኛው የዛኛውን ቀይ መስመር መደፍጠጥ ይጀምራል……ከሁለት አንዱ በፍጥነት ነቅቶ ወደኃላ በመመለስ መረጋጋት ውስጥ ካልገባ ችግሩ መስመር ይስታል፡፡
እኔ 25፡50፡25 የሚል ፕሪንስፕል አለኝ፡፡በትዳር ውስጥ እሷ(ሚስትዬው) እሱ(ባልዬው) እና እነሱ (ባልና ሚስቶቹ)አሉ፡፡እና ስሜታቸው፤ፍላጎታቸው፤የህይወት አላማቸው ወ.ዘ.ተ ተጠቅልሎ መቶ ፐርሰን ቢሰጠው፡፡እሷ የግሏ ፍላጎት በግሏ የሚያስደስታት ነገር፤ መዝናኛ ቦታ፤ጓደኞች፤ 25 ፐርሰንት ትይዛለች….እሱም ለብቻው 25 ፐርሰንት ይይዛል፡፡50 ፐርሰንቱ ግን የጋራቸው ነው፡፡በጋራ የሚያቅዱበት፤በጋራ የሚሰሩበትና የሚለፉበት ቤት መስራት፤ልጆች መውለድና ማሳደግ…ወዘተ፡፡ሁል ግዜ ተሰፍሮ 25፤50፤25 ላይሆን ይችላል፡፡በተለይ ሴቶች ከእነሱ 25ፐርሰንት 10ሩን ወይም 15 ቱን ቆርሰው ለጋራቸው ያውሉታል…ወንዶች ደግሞ ከሞላ ጎደል አውቀውም ሆነ ሳያውቁ ከጋራቸው ላይ ቆረስ አደርገው የእነሱን 25 ፐርሰንት 30 እና 40 አንዳንዴም ከ50 በላይ ያደርሱታል..የዛን ጊዜ የጋብቻው ባላንስ ይናጋል፡፡ምሰሶው መነቃነቅ ይጀምራል..እርማት ካልተደረገለት ጋብቸውን እያከሳ ይሄድና መጨረሻ ያከትምለታል፡፡…የምናገረው ግልፅ ነው አይደል››
‹‹አዎ..በጣም ግልፅ ነው፡፡››
‹‹በምሳሌ ይበልጥ ለማስረዳት አንድ ገጠር የምትኖር አክስቴ ከአስር በላይ ባሎች አግብታለች፡፡ግማሹን እነሱ ናቸው የፈቷት ግማሾቹን እራሷ ነች ያደረገችው፡፡ከሁሉም ግን የሳበኝን አንደኛውን ልንገራችሁ፡፡አገባሁት አለች..በጣም ሰላማዊ ..ምንም አይነት ክፉ ነገር ማይናገር…የጠየቅኩትን ሁሉ የሚያሞላልኝ ሰላማዊ ሰው ነበር አለች፡፡በፊት ከለመደቻቸው ተደባባዳቢ እና ተጨቃጫቂ ባሎች ጋር የትኛውም ፀባዩ የሚገጥም

አልነበረም፡፡ግን ብዙም ሳይቆይ ሰለቻት….ሁሉ ነገር ዝም እና ጭጭ ያለ ሆነባት…በቃ ግንኙነታቸው ውስጥ ነፍስ አጣችበት ፡፡አንድ ቀን በለሊት ተነሳና በሬዎቹንና ሞፈር ቀንበሩን ይዞ ወደማሳ ወጣ …ሲሄድ ቁርስም አልሰጠችውም..ምሳም ይዛ መሄድ ቢገባትም አልወሰደችለትም..ጭራሽም አልሰራችም…በጣም የባሰው ነገር ደግሞ የቤቱን እቃ ብረትድስት ፤ሰሀን ፤ብርጭቆ አንድም ሳታስቀር ከቤት ጀምራ የቤቱን መግቢያ ደጃፍ…ወለሉን ጠቅላላ አዝረክርካ እና ሞልታ ኩርሲ ላይ ቀጭ ብላ ትጠብቀው ጀመር ፡፡.
ከዛ መጣ…ከውጭ ጀምሮ ያዝረከረከችውን እቃ አንድ በአንድ ጎንበስ ብሎ እየለቀመ…‹‹እታዋቡ …ሰላም ነሽ….?ምንም አልሆንሺብኝም አይደል….?››እያለ ሁሉንም እቃ ወደመደርደሪያ መልሶ ስሯ ቁጭ ብሎ በልምምጥ ጭንቅላቷን መዳበስ ጀመረ..
ከዛ ይህቺ አክስቴ ምን ብታደርግ ጥሩ ነው‹‹ ብድግ አለችና ሻንጣዋን ይዛ‹‹እንዴት ቁርስ አላበላሁህ ..ምሳ አለመጣሁልህ….ቤቱን እዲህ አዝረክርኬ ነው የጠበቅኩህ..ምን እስካደርግህ ነው የምትጠብቀው…?ምንም አይነት የወንድነት ወኔ የለህም እንዴ…?ሁለት ሴት አንድ ቤት አይኖርም… ነውር ነው››ብላ ጥላው ወጣች..በዛው ፈታችው ፡፡አያችሁ ትዳር በጣም ውስብስብ ግንኙነት ነው፡፡የበዛ ጭቅጭና ጥል ብቻ ሳይሆን የበዛ ሰላምና ፀጥታም ሊያፈርሰው ይችላል፡፡፡ዋናው በሁሉም ነገር ሚዛን ጠብቆ መጓዝን መልመድ ነው፡፡››
የተወሰነ ትንፋሽ ወሰደና ፊትለፊቱ ካለ የታሸገ ውሀ በማንሳት አንዴ ተጎንጭቶለት ከንፈሩን አረጣጠበና ንግግሩን ቀጠለ፣እነሱም ልክ በቅርብ ፈተና እንደደረሰበት ቸካይ ታማሪ በጥሞናና በትኩረት እየተከታተሉት ነው‹‹አሁን ልብ በሉ፣ ጥረታችን በመካለላችሁ ያላውን ግጭትና ጭቅጭቅ ሙሉ በሙሉ ማስወገድ አይደለም..አይ እንደዛማ አይሆንም እናንተ ሰው ናቸው፣ሁለት ሰዎች ደግሞ በአንድ ጣሪያ ስር አብረው እስከኖሩ ድረስ በሆነ ነገር መነጋገራቸውና በነገሩ ላይ የተለያየ ተቃራኒ ሃሳብ ማንፀባረቃቸው አይቀርም…ስለዚህ መነጋገርና መጨቃጨቅ ኖርማል ነው…አሁን ምንድነው ምናደርገው.. በማንኛውም ጉዳይ ላይ አለመግባባት ተከስቶ ስትነጋገሩ በምን መልኩ ነው ኮምንኬት የምታደርጉት..?ነገሩን ማስረዳትና ማሳመን ላይ ነው ትኩረታችሁ ወይስ ያንን ምክንያት አድርጎ በስድብና በዘለፋ ማጥቃትና ልብ መስበር…አያችሁ ትልቁ ችግር መጋጨታችን ሳይሆን በያንዳንዱ ግጭታችን አንዳችን ለሌላቸውን የልብ ቁስለትና የነፍስ ህመም መስጠታችን ነው፡፡ማጥፋት ያለብን እርስ በርስ መወጋጋቱን ነው…አንዳችን ሌላችን ላይ በምንም አይነት ሰበብ የሚያቆስል ነገር ጦር አስበን አይደለም አምልጦን እንኳን መወርወር ለብንም፡፡እርስ በርስ ከፍ ባለ ቃላት በተነጋገራችሁ ቁጥር ደግሞ እየተጣላችሁ መሆኑን አታስቡት..መጣላት ቃሉ እራሱ አሉታዊ ነው፡፡እየተጣላችሁ ሳይሆን በጋለ ስሜት እየተነጋገራችሁ ነው፡፡በቃ እንዲህ ነው ማሰብ ያለባችሁ፡፡እንደዛ ካሰባችሁ ቀጥታ ችግሩ በጋለ ስሜት መነጋገራችን ብቻ ስለሆነ ስሜታችሁን በማረጋጋት ነገሩን ትፈታላችሁ፡፡እየተጣላን ነው ብላችሁ ካሰባችሁ ግን ጋና ይቅርታ የሚጠይቅ ሰው ወይም ሽማግሌ ልትፈልጉ ነው፡፡ልብ በሉ ጮክ ብሎ መናጋገር ሁል ጊዜ መጣላት አይደለም አብዛኛውን ጊዜ በጋለ ስሜት መነጋገር ነው፡፡ለዘሬው ይበቃናል…አሁን ወደመናፈሻው እንሂድና ትንሽ ዘና


የአባቶች ቀን ..እወድሀለው… ዘላለም ኑርልኝ› ብላ የለጠፈችውን ሰው አሳየኝ…አየሽ እኔ ጎስቆላ አባቷን አለም ፊት በአደባባይ ይዛ ለመውጣት አልተሳቀቀችም..እንደውም በኩራት ነበር ያደረገችው…..ከአራት አመት በፊት ምን ሆነ መሰለሽ..እኔ አባትሽ የተቀደደና ያደፈ ቱታ ለብሼ አንድቤት ጣሪያላይ ወጥቼ ቆርቆር እየጠገንኩ ነበር…ስራዬን ጨርሼ ከጣሪያው በመሰላል በመውረድ ላይ እያለሁ እታች ትላልቅ ሱፍ ለባሽ ሰዎች ቤቱን እየተመለከቱት ነው…ከመሀከላቸው ልጄ በሬዱ ነበረችበት…ለካ ያ ቤት የባንክ እዳ ኖሮበት ጫረታ ላይ ሊያወጡት ከባንክ የመጡ የስራ ኃላፊዎች ነበሩ ..የልጄ ሀለቃዎች…ልክ ልጄን እንዳየኋት ተመልሼ ወደላይ መውጣት ጀመርኩ..ለካ ልጄም በዛው ቅፅበት አይታኝ ኖሮ‹‹…አባዬ
..አባዬ ና አንዴ ውረድ››ስትል የት ልግባ….ምርጫ ስላልነበረኝ ወደታች ወረድኩ…ቆሻሻዬን ሳትጠየፍ ጉስቁልናዬን ከቁም ነገር ሳጥቆጥር አገላብጣ እየሳመች ወደሀለቆቾ ይዛኝ ሄደችና…‹‹አባቴ ነው ..ተዋወቁት ብላ አስተዋወቀችኝ…አክብራ አስከበረችኝ››እነሱን ከሸኘሁ በኃላ ለብቻዬ ገለል ብዬ እንደህፃን ልጅ አለቀስኩ…እና ምን ልልሽ ነው እኔ ነኝ እድለኛው፡፡››
‹‹አይ ጋሼ…እኔ አንተ አባቴ ብትሆን በጀርባዬ አዝዬ ድፍን አዲስአበባን እዞር ነበር….››
‹‹አይ አንቺ…አሁንም አባትሽ ነኝ ..አይደል እንዴ?››
‹‹እሱስ እውነትህን ነው ..አንተ ያደረክልኝ…ግማሹን አባቴ አድርጎልኝ አያውቅም፡፡ማለቴ አሁን እየተነፈስኩ ያለሁት ባንተ ደግነት ነው››
‹‹አይ አንቺ ልጅ….››
‹‹ጋሼ››
‹‹አቤት ልጄ››
‹‹አንድ ነገር ልጠይቅህ ነበረ.. ግን ፈራሁ››
‹‹እንዴ ..እኔ እኮ አባትሽ ነኝ ምን ያስፈራሻል?››
‹‹እንተን.ማለቴ ያው በህመሜ ምክንያት ረጅም ጊዜ ስተኛና ከቤት ሳልወጣ ስለቆየሁ ተጨናንቄያለው…ለተወሰነ ቀን ከለሊሴ ጋር ላንጋኖ ወይም የሆነ ቦታ ሄደን ትንሽ ተዝናንተን ብንመጣ ብዬ ነበር››
‹‹ከለሊሴ ጋር ስራዋስ ልጄ?››

‹‹አልሰማህም እንዴ….ሀለቃዋ እኮ ለስራ ሌላ ሀገር ለአንድ ወር ስለሄደ ፍቃድ ሰጥቶታል፡፡››
‹‹እንደዛ ነው››፣አሉና መልስ ሳይሰጡ ወደትካዜ ውስጥ ገቡ…ምን ብለው ሁለት የደረሱ ሴቶችን እንደሚፈቅዱላቸው ምን ብለውስ እንደሚከለክሎቸው ግራ ገባቸው››
‹‹በፀሎትም መልሱን ለመስማት አፏን ከፍታ በጉጉት መጠበቋን ቀጠለች››
‹‹የእኔ ልጅ ያልሽው ትክክል ነሽ..አየር መቀየርና ትንሽም ዘና ማለት አለብሽ…ግን ሁለታችሁም ሴቶች ናችሁ …ለምን ወንጪ አትሄዱም››
‹‹እንዴ ጋሼ..ደስ ይለኛል….ቦታው አሪፍ ይመስለኛል››
‹‹አዎ ቦታውማ ገነት በይው..ግን ከቦታውም በላይ ትውልድ አካባቢዬ ነው..አሁንም ዘመዶቼ እዛ አሉ..ወንድሞቼ እህቶቼ ብዙ ናቸው..ለሊሴም ቦታውን በደንብ ታውቀዋለች..እዛ ከሄዳችሁ እኔ አባታችሁ ምንም አላስብም….የፈለጋችሁትን ያህል ቀን መቆየት ትችላላችሁ..ግን የእናትሽ የጽዋ ማህበር የዛሬ ሳምንት ነው..ከዛ በፊት እንድትሄዱ አትፈቅድላችሁም››
‹‹አመሰግናለው ጋሼ..››ከመቀመጫዋ ተነሳችና አቅፋቸው ግንባራቸውን ሳመቻቸው፡፡››
‹‹ልጄ አመሰግናለው››
‹‹እኔ ነኝ እንጂ ማመሰግነው››
‹‹አይ አመሰግናለው ያልኩሽ ሁል ጊዜ በድርጊቶችሽ ልጄ በሬዱን ስለምታስታዊሺን ነው..አፈሩን ገለባ ያድርግላትና እሷም እንደእዚህ አንደአንቺ የሆነ ነገር ጠይቃኝ እሺ ካልኳት አቅፋ ትስመኝ ነበር….››
‹‹ይቅርታ ጋሼ እሷን እንድታስታውስ ስላደረኩ››
‹‹አይ…እንዳስታውሳት ስለምታደርጊኝ ሚከፋኝ መሰለሽ….?ልጄን መቼም መርሳት አልፈልግም…ደግሞ የምትረሳም ልጅ አይደለችም…የእኔ በሬዱ ቶሎ ተወልዳ በፍጥነት አድጋ…በጮርቃነቷ በስላ..በችኮላ ጥሩጥሩ ነገሮችን ሰርታ እኔ አባቷን አስደስታ የሞተች ድንቅ ልጅ ነች.…በይ የሆነች ለቅሶ ቢጤ አለችብኝ፣ደረስ ብዬ ልምጣ..እስከዛ ከእናትሽ ጋር

ተጫወቺ…››አሉና የሚተናነቃቸውን እንባ እንደምንም ተቆጣጥረው ወደውስጣቸው በመመለስ ከመቀመጫቸው ተነሱ፡፡
‹‹እሺ ጋሼ…እንዳትቆይ››
‹‹አልቆይም ልጄ..››አሉና ኮፍያቸውን ከጠረጴዛ ላይ አንስተው ጭንቅላተቸው ላይ አስተካከለው እያደረጉ ቤቱን ለቀው ወጡ

ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
መጽሐፍት መንደር
ከመጽሐፍት መንደር
ከመጽሐፍት መንደር

♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-አስራስምንት

ሰለሞንና በፀሎት በስልክ እያወሩ ነው፡፡
‹‹ለመሆኑ የት ነው ያለሽው?››ሲል ጠየቃት
‹‹ምነው ጠየቅከኝ?››
‹‹አይ ..እንዲሁ ደህንነትሽ አሳስቦኝ ነው….ምን አልባት የማይመች ቦታ ካለሽ ልረዳሽ እችላለው፡፡››
‹‹ምነው ወደቤትህ ወስደህ ደብቀህ ልታኖረኝ አሰብክ››

‹‹ምነው ..ችግር አለው.?.የእውነት የማይመች ቦታ ካለሽ ንገሪኝ››
‹‹አሁን ካለሁበት ቦታ የተሻለ ሊመቸኝ የሚችለው ምን አልባት ገነት ነው….እሱንም ደግሞ ስላላየሁት እርግጠኛ አይደለሁም››
‹‹እንዴ…ከእናትና  አባትሽም  ቤት  የተሻለ  ቦታ  ነኝ  ነው  የምትይኝ…ይሄንን  ማመን አልችልም፡ ››
‹‹ነገርኩህ እኮ…››
‹‹‹እ ..ገባኝ››
‹‹ምኑ ነው የገባህ?››
‹‹ከእናትና አባት ቤት በበለጠ የሚመች ቦታ የፍቅረኛ ቤት ነው››
‹‹በጣም ተሳስተሀል..አዲስ ቤተሰብ አግኝቼለሁ…አራት ናቸው..ሽማግሌ አባትና እናት፣አንድ ዋንድ ሴትና ወንድ ልጅ አላቸው..ሀለት ክፍል ሰርቢስ ውስጥ ነው የሚኖሩት፣ኑሮቸው ከእጅ ወደአፍ ነው… ፍቅራቸው ግን ሞልቶ የፈሰሰ ነው….ለዘላለም ልጃቸው አድርገው ተቀብለውኛል…ከአሁን ወዲህ ባለው ህይወቴ ሙሉ አነሱ ወላጆቼ እና ቤተሰቦቼ እንደሆኑ እንዲቀጥሉ ምንም ነገር አደርጋለው››
‹‹የሚገርም ነው….እናትና አባትሽ ይሄንን ንግግርሽን ቢሰሙ ልባቸው የሚሰበር ይመስለኛል፡፡››
‹‹እንግዲህ ምንም ማድረግ አልችልም…በእነሱ ስህተት ነው ከቤት የወጣሁትና እነሱን ያገኘሁት…አሁን አግኝቼ በደንብ አጣጥሜቸዋለው…እና ወደቤት ብመለስ እንኳን ወላጆቼን ከእነሱ ጋር ነው ማነፃፅራቸው…እና ለእነሱ ቀላል የሚሆንላቸው አይመስለኝም››
‹‹….ለመሆኑ ማንነትሽን ያውቃሉ?›
‹‹አይ አያውቁም.. እኔ ለእነሱ እናቷ የሞተችባት እና የእንጀራ አባቷ ሰክሮ በለሊት ሊደፍራት ሲል አምልጣ የወጣች ሚስኪን ሴት ነኝ››
‹‹ይሄንን ታሪክ አንቺ ነሽ የፈጠርሽው?››

‹‹አዎ…..››
‹‹የምትገርሚ ልጅ ነሽ ..እኔጋም መጥተሸ ተመሳሳይ ታሪክ ብትነግሪኝ አምኜ ልረዳሽ መሞከሬ አይቀርም ነበር››
‹‹የእነሱ እኮ መርዳት አይደለም….እናትና አባት መሆን ነው…..እንደልጃቸው መቀበል››
‹‹ የእውነት አዲሶቹን ቤተሰቦችሽን እኔ እራሱ ለመተዋወቅ ጓጓሁ› ›
‹‹መጓጓትህ ትክክል ነህ››
‹‹ነገሮች ከተስተካከሉ በኃላ ታስዋውቂኛለሽ ብዬ ገምታለው››
‹‹መጀመሪያ እስኪ እኛ ለመተዋወቅ ያብቃን››
‹‹እንዴ እኛኮ በደንብ ተዋወቅን፣ለአመታት የማውቅሽ እንደሆነ ነው የሚሰማኝ››
‹‹እሱስ እውነትህን ነው..ያው አካል ለአካል አልተገናኘንም ብዬ ነው፡፡››
‹‹ባክሽ የስልኬ ጋላሪ ባንቺ  ፎቶዎ ተጨናንቆል  ››ብሎ ያልጠበቀችውን አስደንጋጭ ነገር ነገራት፡፡
‹‹እንዴ በምን ምክንያት?››
‹‹እንዴ ..ደንበኛዬ አይደለሽ?››
‹‹እና የሁሉንም ደንበኞችህን ፎቶ ትሰበስባለህ ማለት ነው?››
‹‹ቆንጆ እና የተለየ የሆኑትን ..አዎ››
‹‹በቻይንኛ ቆንጆ ነሽ እያልከኝ ነው፡፡››
‹‹እ..ምነው አይደለሽም እንዴ?››
‹‹እኔ እንጃ ….ለማንኛውም ደስ የሚል ስሜት እንዲሰማኝ አድርገሀል…እና እኔስ የአንተን ፎቶ የማግኘት መብት ያለኝ አይመስልህም?››

‹‹አይ..አዲሶቹን ቤተሰቦችሽን እንድምታስተዋውቂኝ ቃል ካልገባሽ የምታገኚ አይመስለኝም››
‹‹አዲሶቹን ቤተሰቦቼን….እኔ እንጃ ..ስለምሰስታቸው የማደርገው አይመስለኝም››
‹‹‹ትገርሚያለሽ…፣ዋናዎቹን ቤተሰቦችሽን እኮ ተቆጣጥሬቸዋለው…..ለማንኛውም ይህን የመሰለ ቤተሰብ ስላገኘሽ ደስ ብሎኛል….ይሄውልሽ በህይወት ውስጥ ሶስት አይነት ሰዎች አሉ፡፡ቅጠል የሆኑ ሰዎች… ቅርንጫፍ የሆኑ ሰዎችእና… ስር የሆኑ ሰዎች።ቅጠል የሆኑ ሰዎች ወቅትንና ሁኔታዎችን ጠብቀው ወደ ህይወትሽ የሚገብ ናቸው።ደካሞች ስለሆኑ በእነሱ ተፅዕኖ ስር ፈፅሞ እንዳትወድቂ። ከአንቺ የሚፈልጉትን የሆነ ነገር ስላለ ነው ወደህይወትሽ የሚመጡት... የመከራ ንፍስ በህይወት ዙሪያ ሲነፍስ መርገፍ ይጀምራሉ።እነዚህ ሰዎች አንቺን ማፍቀር የሚቀጥሉት በዙሪያሽ ያሉ ነገሮች ጥሩ እስከሆኑ ጊዜ ብቻ ነው።ንፋስ እንደመታው የወየበ ቅጠል ከላይሽ ላይ ተዘንጥለው ይረግፋሉ። ቅርንጫፍ ሰዎች ደግሞ በአንፃራዊነት ጠንካሮች ናቸው ግን ልትጠነቀቂያቸው ይገባል።ህይወት ጨከን ስትል መገንጠላቸው አይቀርም። ምክንያቱም ጠንከር ያለ የህይወት ጫና የመሸከም አቅም የላቸውም።ነገሮች ጨለምለም ሲሉ እና ተስፋም የሌላቸው ሲመስሉ ጥለውሽ ዞር ለማለት አያመነቱም። ሌሎቹ ልክ እንደአንቺ አዲሶቹ ቤተሰቦች ስር የሆኑ ሰዎች ናቸው። እነዚህ በህይወትሽ በጣም አስፈላጊ ሰዎች ናቸው።ለመታየት ብለው የሚሰሩት ስራ የለም።በመከራሽም በደስታሽም ጊዜ አብረውሽ ናቸው።አስከሞት የታመኑሽ ናቸው።ሲያፈቅሩሽ በነፃ ምንም መልስ ካንቺ ሳይጠብቁ ነው፣እንደዚህ አይነት አንድ ወይም ሁለት ሰው ከጎንሽ ማግኘት የህይወት ዘመን ሽልማት ነው፡፡
‹‹ጥሩ አድርገህ ገልጸኸዋል፡፡እነሱ ብቻ ሳይሆኑ፣አንተም ለእኔ ስር ነህ…በቃ ቸው…ነገ እንደዋወላለን፡፡››
‹‹ቸው …..ደህና ሆኚ››ብሎ ስልኩን ከዘጋ በኃላ …ባለበት ቆሞ ትካዜ ውስጥ ገባ..ይህቺን ልጅ በተመለከተ የተለየ አይነት ኬሚስትሪ በሰውነቱ እየተረጨ ነው….ነገሮች ወዴት እያመሩ ነው?››ሲል እራሱን ጠየቀ፡፡

በማግስቱ……
በፀሎት ከሞላ ጎደል ጤንነቷ እየተመለሰ ነው…አረ እንደውም ድናለች ማለት ይቻላል..የእግሯ ስብራት ሙሉ በሙሉ ተጠግኖ በደንብ መራመድ ችላለች..የፊቷ ቁስለትም ሙሉ በሙሉ ጠጓል..አሁን ብቸኛ ችግሯ ፊቷ ላይ ተሸነታትሮ የሚገኘው ጠባሳ ብቻ ነው….እንግዲህ ግማሽ ፊቷን ባደረሰው በተበታተነው ጠባሳ ውስጥ ምን ያህሉ እንድሚጠፋና ከበፊት ቆዳዋ በቦታው እንደሚመለስ ምን ያህሉ ደግሞ እንዳዛው እንደሚቀር ምንም የምታውቀው ነገር የለም…ያንን ለማወቅ በርከት ያሉ ተጨማሪ የማገገሚያ ቀኖች ያስፈልጋታል…ከዛ በኃላ የቆዳ ስፔሻሊስቶች ጋር ሔዳ ሰርጀሪ መሰራትም የግድ ያስፈልጋት ይሆናል….ለጊዜው ያ እያሳሰባት አይደለም…‹‹እሱን ጊዜው ሲደርስና ሁሉ ነገር ተስተካክሎ ወደቤት ከተመለስኩ በኃላ አስብበታለው››ብላ ወስናለች….አሁን ከጎኗ አቶ ለሜቻ ቁጭ ብለው እያጫወቷት ነው፡፡
‹‹ለልጆቾህ ያለህ ፍቅር ያስገርመኛል››
‹‹አይ ልጄ ሁሉም ወላጆች እኮ ልጆቻቸውን አብዝተው ይወዳሉ…››በትህትና መለሱላት፡፡
‹‹እሱን ማለቴ አይደለም..የእናንተ የተለየ ነው…አይኖችህ ከልጆቾህ ላይ አይነቀሉም….ሙሉ ትኩረትህ ልጆቾህ ላይ ነው..ስለእለት ውሏቸው ታውቃለህ….ጥዋትና ማታ አብረሀቸው ባንድ መሶብ ቀርበህ ሁለቱንም እያጎረስክ ነው የምትበላው፣ብዙ ብዙ ነገር…››
‹‹ልጄ ወድጄ አይደለም እኮ…. እንደምትይው እኔ አባትሽ በብዛት ተትረፍርፎ ያለኝ ፍቅር ነው…ገንዘብ ኖሮኝ ይሄን ስሩ ብዬ መቋቋሚያ..ወይም መነገጃ ጥሪት አልሰጣቸው….ሁል ጊዜ ታዲያ ይሄንን ነገር በምንድነው የማካክሰው ብዬ ሳስብ አንድ የማገኘው መልስ…ጊዜዬንና ፍቅሬን ሳልሰስት መስጠት ነው..አዎ ቢያንስ በዛ ነው ልክሳቸው የምችለው፡››
‹‹ግን እንሱ ምን ያህል እድለኞች መሆናቸውን ያውቃሉ?›› ‹‹አይ እነሱ ሳይሆኑ እኔ ነኝ እድለኛ….ምንም ባላደርግላቸው እንኳን ማንም ፊት በኩራት አባዬ ብለው ይጠሩኛል፡፡በቀደም ለሊሴ ይሄ ፌስቡክ ነው ምን በምትሉት ነገር ላይ በተንዠረገገ ፂሜንና በጎፈረ ፀጉሬ የተነሳሁትን የተጎሳቆለ ፎቶ ለጥፋ አባዬ መልካም


ባል ካገባች ብዙ ግዜ የሆናት አንዲት ልጅ ባሏ ትንሽ የበጬነት ችግር አለበት እና ምንም ሳይነካት አመታት ስትኖር ቆየችና ሲሰለቻት የሆነ መላ መዘየድ አለብኝ ብላ አስባ አስባ.... ለምን ክፍት ፍት ብዬ ተኝቼ አልጠብቀውም ደንግጦ መሞከሩ አይቀር ብላ ባሏ ጅል ቢጤ ነው ...ከስራ ሲመጣ እንዳለችው ሆና ብልቅጥ ብላ ስጠብቀው ደንግጦ
ባል ፦ " በሬ ነው እንዴ እንዲህ በቀንዱ የቀደደሽ "
ሚስትም ፦ " በሬ አይደለም የቀደደኝ ተፈጥሮ ነው ና ንካዉ ብላ ስታስነካዉ ፍም መስሎ ተነርቶ አብጦ ፍንትዉ ብሎ እሰተ ጎመራ መስሏል “ ወዲያዉ ብድግ አለበት ጎትታ እራሷ አስተካክላ ከታ አቀመሰችው በቃ ጣመው ማታም ቀንም እዛው መጣድ ሆነ ስራው... "እንደው ፈጣሪ ካልጠፋ ቦታ ከፍ አርጎ በበሳው ይል ጀመር" 🤣
ታዲያ አንድ ቀን የልጅቷ አባት በንግድነት መጡ
ባል ደፋ ቀና ብሎ አስተናገዳቸውና እንደው የውዴታው የአክብሮቱን ሚስቱን ጠርቶ
"እረ ከዚያ ከሚጥመው ነገር ሳይቀምሱ እንዳይሄዱ አቅመሻቸው " እያለ አዛ ሲያረጋት ሚስትየው ገልመጥ ብታረገውም አልገባው አለ
በቃ አባት ከፋቸው ብዙም ሳይቆዩ ቤታቸው ተመለሱ
በርላይ ሚስታቸውን ሲያገኙ

" ልጅሽ ከዚያ ነገር አቅምሻቸው እያለ ትከልክለኝ” 🤣🤣🤣🤣


በቃ አሁን ቀጥታ ወደማዳመጡ እንግባ ››አለና ኮምፒተሩን ከፈተና ለ.ወሮ ስንዱ አቀበላት…አቶ ኃይለልኡል ያለምንም ንግግር ከተቀመጠበት የራሱ አልጋ ተነሳና ሄዶ ወ.ሮ ስንዱ አልጋ ላይ ከጎኗቸው ተቀመጠና በኮምፒተር የሚታየውን የራሳቸውን ንግግር ለማደመጥ ዝግጁ ሆነ…ሰለሞን በፀጥታ ከተቀመጠበት ተነሳና ክፍልን ለቆ በራፍን ዘጋላቸውና ወጥቶ ሄደ


ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
ከመጽሐፍት መንደር
ከመጽሐፍት መንደር
ከመጽሐፍት መንደር

♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️


‹‹የተለየ ስትል?› ‹‹እስከአሁን ወደእኔ መጥተው የሚያናግሩኝ ከሁለት አንዱ ማለቴ ባልዬው ወይም ሚስትዬው ናቸው….የእናንተ ግን ልጃችሁ ነች ያናገረችኝም የቀጠረችኝም፡፡››
‹‹አዎ እሱስ ትክክል ነህ››
‹‹ስለዚህ አሁን ስራችንን ስንጀምር እሷን እያሰብን መሆን አለበት ፡፡በፍቅር የታነፀ ትዳር ውስጥ ያላደጉ ልጆች በመጨረሻ በስነ-ልቦናም ሆነ አካላዊ በሽታ እንደማያጣቸው የተረጋገጠ ነው። ልጅ ስናሳድግ ጥሩ ልብስ ፣ጥሩምግብና ጥራቱን የጠበቀ ትምህርት እንዲያገኙ መጣር ብቻ ሳይሆን የተሞላ ፍቅርም እየመገብን ማሳደግ እንዳለበት እንደወላጅ ግንዛቤው ሊኖረን ይገባል።የመፈቀር እና የመፈለግ ስሜት ማጣት በከፍተኛ ሁኔታ የልጆችን በራስ የመተማመን ችሎታን ከመሸርሸሩም በላይ ለአእምሮ ውጥረትና ድብርትም እንዲዳረጉ ያደርጋቸዋል።ለልጆች በፍቅርና በእንክብካቤ ማደረግ ደስተኛ ሆኖ ለመኖር ብቻ ሳይሆን ጤነኛም ሆኖ ለመኖር በጣም አስፈላጊ ነገር ነው።በወላጆቹ የሚወደድ እና ወላጆቹም የሚወድት ልጆች በጣም ደስተኛ ናቸው።በፍቅር ውስጥ መኖር ጤነኛ ሆኖ ለመኖር እና የበሽታ የመከላከል አቅማችንን ለመጨመር እንደሚያግዝ በሳይንስ የተረጋገጠ ነው።ስለዚህ ልጆቻችን በፍቅር ታንፀው የመፈለግና የመወደድ ስነልቦና ኖሮቸው ማደግ አለባቸው፡፡ለዚህም ወላጆች ሁሉ ትኩረት ሰጥተው መስራት አለባቸው፡፡፡ እንደውም እናንተ እድለኛ ናችሁ፡
‹‹እድለኛ ናችሁ ስትል?››
‹‹እንዴ በፀሎት እኮ በጣም የምትገርም ብስልና በቀላሉ የማትሰበር ልጅ ነች፣አብዛኞቹ በእሷ እድሜ ያሉ ልጆች በእንደዚህ አይነት ችግሮች ውስጥ ሲያልፉ ከፍተኛ ድብርት ውስጥ ይገቡና ለተለያዩ ሱሶች ይጋለጣሉ ..ከዛም አልፈው በህይወት ተስፋ መቁረጥ ውስጥ ይገቡና እራሳቸውን ወደማጥፋት ይሄዳሉ….በፀሎት ግን ያደረገችው ከውጥረቱ ራሷን ዞር አድርጋ እናንተን ለመርዳትና ወደመስመር ለመመለስ መጣር ላይ ነው ያተኮረችው››
‹‹አዎ እውነትህን ነው …በልጄ ታላቅ ኩራት ተሰምቶኛል….ምንም ጭረት ሳይነካት ወደቤቷ እንድትመለስ ማድረግ ያለብኝን አደርጋለሁ..ማለት ሁለታችንም ማድረግ ያለብንን እናደርጋለን አይደል ስንዱ?››
‹‹አዎ ትክክል ነህ…ለዛም አይደል እዚህ የተገኘነው››

‹‹እንግዲያው ጀመርን …ከአሁን በኃላ የምናወራውና የምንናገረው ሁሉ እየተቀዳ ነው.››.ብሎ አይፓዱን አስተካክሎ ተጫነውና ቦታውን ይዞ ተቀመጠ…››
ለሶስት ሰዓት ቀጠለ…..በመጀመሪያ ወ.ሮ ስንዱ አቶ ኃይለመለኮት ላይ ያላቸውን ቅሬታ እስከአሁን በደሉኝ የሚሉትን ነገር እንዲያወሩና አቶ ኃይለመለኮት ደግሞ ለደቂቃ እንኳን ሳያቆርጡ እንዲሰሙ አደረገ…በቀጣዩ ሰዓት ደግሞ አቶ ኃይለልኡል በተራቸው ሚስታቸው ላይ ያላቸውን ቅሬታ በዝርዝር እንዲናገሩ አደረገ……..ቀጣዩን አንድ ሰዓት ደግሞ እራሱ ሰሎሞን ጥያቄ እየጠየቃቸው ሁለቱም ተራ በተራ እዲመልሱ ተደረገና የጥዋቱ ክፍለጊዜ አለቀና ሶስቱም ተያይዘው ወደሳሎን ሄዱ ..ምሳው በስርአት ተዘጋጅቶ ስለጠበቃችው ሶስቱንም ጠረጴዛውን ከበው ፀጥታ በተጫነው ና እርስ በርስ በተፈራራ በሚመስል ሁኔታ ምሳቸው ተበልጦቶ አለቀ..ብና ተፈልቶ ስለነበረ በረንዳ ላይ ቁጭ ብለው ንፋስ እየተቀበሉ ጠጡ
‹‹አሁን ለአንድ ሰዓት ያህል መኝታ ክፍላችሁ ገብታችሁ አረፍ በሉ….ሰዓት ሲደርስ እኔ መጥቼ ቀሰቅሳችኃላው››
እሺ ብለው ሁለቱም ከመቀመጫቸው ተነሱ..ሰለሞን ከኃላ ተከተላቸው….››መኝታ ቤታቸው እንደደረሱ ሊከፍቱ ሲታገሉ‹‹ይቅርታ ሳልነግራችሁ መኝታ ቤታችሁ ተቀይሮል..ተከተሉኝ››ብሎ ቀደማቸው፡፡
‹‹የማ…? የእኔም ነው የተቀየረው?››
‹‹አዎ ወ.ሮ ስንዱ….ሁለታችሁም ተከተሉኝ..››
ግራ በማገባት ሁለቱም በዝምታ ከኃላው ተከተሉት …የኮሪደሩ መጨረሻ ላይ ካለው በራፍ ሲደርስ ቆመና ከፈተው….‹‹ግቡ ››
‹‹ማ እኔ ነኝ እሷ?››
‹‹ሁለታችሁም››
እርስ በርስ ተያዩ…ቀጥሎ በጋራ እሱ ላይ አፈጠጡበት…አንድ ክፍል ውስጥ አብረው ከተኙ አስር አመት አልፏቸዋል..አሁን በአንዴ እንዴት….?ጉዳዩ ሁለቱንም እኩል ነው ያስበረጋጋቸው፡፡

ጫን ባለ የአዛዥነት ቃና‹‹እባካችሁ ግቡ››አላቸው
ምርጫ ስላልነበራቸው አቶ ኃይለልኡል ቀድመው ገቡ…ወ.ሮ ስንዱ ተከተሏቸው….ሁለቱም ጎን ለጎን ቆመው ክፍሉን ዙሪያ ጋባ ቃኙት …ሻንጣቸው ሆነ ጠቅላላ እቃቸው በየቦታው ተቀምጦል…ሁለት አልጋ ማዶ ለማዶ ግድግዳ ተጠግቶ ይታያል…፡፡
ያው ..ሁለት አልጋ አለ …ተነጋገሩና አንዳንደ አንድ ተካፈሉ …በቃ መልካም እረፍት..ሰዓቱ ሲደርስ መጥቼ ቀሰቅሳችኃላው››አለና ከክፍሉ ወጥቶ በራፉን መልሶ ዘግቶላቸው ወደገዛ ክፍሉ ሄደ፡፡
///
የሁለት ሰዓት የረፍት ጊዜ ከሰጣቸው በኃላ በጥዋቱ ጊዜ ባለው ፕሮግራም የቀረጸውን ወደኮምፒተሩ ገለበጠና ይዞ ወደእነሱ ክፍል አመራ…በስሱ ቆረቆረ…ወዲያውን ነበር የተከፈተለት፡፡
‹‹መጣህ ..?እየጠበቅንህ ነበር››
‹‹አዎ መጥቻለው››
‹‹ስንዱ ተነሽ..እንሂድ››አቶ ኃይለልኡል ተናገሩ፡፡
‹‹አይ ቆይ መሄድ አያስፈልግም ….እዚሁ እናድረግው››
‹‹ይሻላል ..እሺ ግባ..››ብለው በራፉን ለቀቁለትና ወደውስጥ በመመለስ አልጋቸው ጠርዝ ላይ ተቀመጡ ፡፡ወ.ሮ ስንዱም የራሳቸው አልጋ ላይ እንደተቀመጡ ነው፡፡
ወንበር ሳባና ከሁለቱ መካከል ተቀመጠና ኮምፒተሩን ጠረጳዛ ላይ አስቀመጠው፡፡
‹‹ይሄውላችሁ በትዳር ውስጥ ችግር መፈጠርና አለመስማማት የእናንተ ብቻ ሳይሆን የሚሊዬን ጥንዶች ችግር ነው..እመኑኝ ያልተስማማንበት ነገር ይህ ነው ያ ነው ብላችሁ ቀኑን ሙሉ ስትዘረዘሩ ብትውሉ የእናንተ ከሌላው ትዳር ውስጥ ከተፈጠረው ችግር የተለየ ሊሆን ይችላል እንጂ የባሰ ግን አይደለም፡፡ስሙኝ አብዛኛውን ጊዜ በትዳር ውስጥ ችግር ሲከሰት በትዳር ውስጥ ችግር የፈጠረውን ነገር ከማየት ይልቅ እራሱ ትዳርን እንደችግር የመውሰድ  አዝማሚያ  ይታያል።ያ  ደግሞ  ከትዳራቸው  ውስጥ  ሾልኮ  ስለመውጣት

ስለመፋታት እንዲያስብ ያደርጋቸዋል።እንደሀሳባቸው ትዳራቸውን ፈተው የተሻለ ወዳሉት ወደሌላ ትዳር መሸጋገር ቢችሉም ችግሩም አብሯቸው ነው ወደአዲሱ ትዳራቸው የሚሸጋገረው።
መፍትሄው ትዳሩን እንደችግር ወስዶ ያልሆነ ድምዳሜ ላይ ከመድረስ ይልቅ ትዳሩ ውስጥ የተከሰቱ ችግሮች ምን ምን ናቸው ብለው በመለየት እነሱን ለማስወገድ መጣር እና በዛ ሂደት የጋብቻውን ህልውና ማስቀጠል ይበጃል።ምክንያቱም የመኪናህ ጓማ ቢያልቅ ጎማውን ትቀይራለህ እንጂ መኪናዋን ሙሉ በሙሉ አታስወግድም።አይደለም ጎማ ሞተሩ ቢነክስ እንኳን ሞተር አስወርደህ ከእንደገና ተፈቶና ተበታትኖ ችግሩ ተለይቶ ከተወገደ በኃላ መልሶ ይገጣጠምና መኪናው እንደነበረ ይቀጥላል... ጋብቻም እንደዛ ነው የሚደረገው።እና አሁን እያደረግን ያለነው በመሀከላችሁ ያለውን ችግር የመቃቃራችሁን መንሴ መለየት ነው፡፡አሁን በጥዋቱ ክፍለ ጊዜ ሁለታችሁም የተናገራችሁትን እዚህ ኮምፒተር ላይ ከፍትላችኃላው በጋራ አብራችሁ ታዩታላችሁ…ይሄ መልሳችሁ የተናገራችሁትን እንድታዳምጡና የትኛው ትክክል ነው..የትኛው ንግግራችሁ ተጋኗል የሚለውን መልሳችሁ እንድታስበቡበት ይረዳችኃላ…


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-አስራ ሰባት

ይዘውት የሄዱት ቦታ ከቢሾፍቱ ከተማ በባቦጋያ ሀይቅ አካባቢ ከከተማው ወጣ ብሎ የሚገኝ ቪላ ነው፡፡ይህ ቪላ ቤተሰቡ ከውጥረት ረገብ ለማለት ሲፈልግ የሚገለገልበት ስፋራ ነው፡፡ለአለፉት አንድ አመት ከግማሽ ማንም ዝር ብሎበት አያውቅም ነበር፡፡ሰለሞን ስፍራውን ሲያይ ከውበትም ሆነ ከፀጥታ አንፃር ሲታይ ሙሉ በሙሉ እሱ እንደሚፈልገው አይነት ሆኖ ነው ያገኘው፡፡አንድ ሺ ካሬ ሜትር በላይ የሚሆን ቅፅር ግቢ ነው፡፡መሀከል ላይ ግዙፍና ባለግርማ ሞገስ ጥንታዊ ግን ደግሞ ጥሩ ይዞታ ላይ ያለ ግዙፍ ቪላ ቤት አለበት…ግቢው ውስጥ እድሜ ጠገብ ግዙፍ ባለግርማ ሞገስ የባህር ዛፍና የጥድ ዛፎች ስብስባ ላይ እንደተቀመጠ ታዳሚ እዚህም አዛም ዙሪያውን ተሰራጭተው ይታያሉ…ገና ግቢውስጥ ገብተው እንዳቆሙ የቤት ጠባቂዎች በልና ሚስቶች በፍጥነት መጥታው መኪናዋ አጠገቡ ቆሙ፡፡መኪናዋን ሲነዳ የነበረው እራሱ ሰሎሞን ስለነበረ….ሞተሩን

አጠፋና ቀድሞ ወረደ…አቶ ኃይለመለኮትን ወ.ሮ ስንዱም ወረዱና ከጠባቂዎቹ ጋር ሰላምታ መለዋወጥ ጀመሩ…ከዛ ቀጥታ ወደ ቤት ነው የገቡት….ቀድመው ደውለው ስለነበር..እቤቱ ምሉ በሙሉ ፀድቶና የእነሱም መኝታ ክፍል ተዘጋጅቶ ነበር የጠበቃቸው….
ታፈሰ ‹‹ጋሼ ባዘዙኝ መሰረት ሶስት ክፍል ለመኝታ አዘጋጅቼያለው…ይሄው እርሶ እዚህ ግቡ….እትዬ ደግሞ ቀጥሎ ያለው …ወንድም አንተ ደግሞ የፊት ለፊተኛው ክፍል…..ድንገት ስለሆነብን ሁሉንም ነገር ማዘጋጀት አልቻልንም….የጎደለውን ንገሩኝና ከተማ ወጣ ብዬ ገዝቼ አሟላላሁ››
አቶ ሃይለመለኮት ወደሰለሞን እያመለከቱ‹‹ተፈሰ…ይሄውልህ እዚህ 15 ቀን ነው የምንቆየው….በዚህ 15 ቀናት ውስጥ የእኛም ሆነ የአንተ ሀለቃ እሱ ነው….ምንም ነገር ቢያዝህ እሱ ያለውን ነው የምታደርገው…እኛም እንደዛው››ሲሉ መመሪያ አስተላለፉ፡፡
ታፈሰ…የአቶ ኃይለልዕልን ንግግር ከበፊት ቆፍጣና ባህሪያቸው ጋር አልሄድ ስላለው ..ግራ በመጋባት አፍጥጦ ያያቸው ጀመር…እሱ እንደሚየውቀው እኚ ግዙፍ አዛውንት ለሰው ምንም ሊሰጡ ይችላሉ የአዛዥነት ቦታቸውን ግን ፈፅሞ ሸርፈው እንኳን ለሌላ ሰው ይሰጣሉ ብሎ ማመን ይከብደዋል፡፡
‹‹ታፈሰ ..ሰምተኸኛል…የሁሉ ነገር አዛዣችን እሱ ነው››ደገሙለት፡፡
‹‹አዎ ..ገባኝ ጌታዬ…እንዳሉት ይደረጋል››
‹‹አሁን ሁላችንም ወደክፍላችን እንግባና ትንሽ አረፍ እንበል ..አይደል?››ወ.ሮ ስንዱ የሰለሞንን አይኖች በልምምጥ እያዩ ጠየቁ፡፡
ቆይ አንዴ ክፍላችሁን ልይ ብሎ..ለአቶ ኃይለልኡል የተመደበውን ከፍቶ አየው፡፡ቀጥሎ የወ.ሮ ስዱን ከፈተና አየው፡፡‹‹ጥሩ በቃ ግቡና እረፉ››
ሁለቱም ገቡና የየራሳቸውን ክፍል ዘጉ
‹‹አንተም ወደክፍልህ ግባ ጌታዬ..እኔ ደግሞ እቃችሁን ከመኪና ላውርድ››
‹‹ቆይ አብሬህ ልምጣ››ብሎ ተከተለው፡፡የታፈሰ ባለቤት ለእንግዶቹ ምግብ እያበሰለች ስለነበር ታፈሰ እቃዎቹን ማለት ይዘው የመጡትን አስቤዛ እና ሻንጣዎች ሲያወርድና ወደቤት ሲያስገባ ሰሎሞን አገዘው፡፡እንደጨረሱ፡፡‹‹ተለቅ ያለ ክፍል የለም?››ሲል ጠየቀው፡፡

‹‹ምን አይነት ክፍል…ማለቴ ለምን የሚሆን?››
‹‹ለመኝታ ቤት የሚሆን ..ሁለት አልጋ የሚያዘረጋ››
‹‹ቆይ ..ኮሪደሩ መጨረሻ ላይ ያለው ክፍል ሰፋ ይላል››
‹‹ማየት እችላለሁ?››
‹‹አዎ ይቻላል….››ብሎ ይዞት ሄደና ከፈተለት…ሰለሞን ወደውስጥ ዘልቆ ሳይገባ በራፉ ላይ በመቆም አንገቱን ወደውስጥ አስግጎ ተመለከተው….አቦራ የጠጣና ለብዙ ጊዜ ጥቅም ላይ ያልዋለ ቢሆንም የሚፈልገው አይነት ክፍል ነው፡፡››
‹‹ታፈሰ ይሄንን ክፍል በአስቸኳይ ልታስፀዳልኝ ትችላለህ….?››
‹‹እችላለሁ..አፀዳዋለው››
‹‹አይ ብቻህን ይከብድሀል..ሰው ቅጠርና በፍጥነት ወለሉም ግድግዳውም ይፅዳ….ውስጥ ያሉት እቃዎችም ወደሌላ ክፍል ይዘዋወሩ››
‹‹እሺ››
ተሰናብቶት ንፁህ አየር ሊቀበልና እግረመመንገዱን አካባቢውን ለመቃኘት ወጥቶ ሄደ፡፡
///
በማግስቱ ጥዋት 3 ሰዓት ላይ ሁለቱንም የማይጣጣሙ ባለትዳሮችን አንድ ክፍል ጎን ለጎን እንዲቀመጡ አደረገና እሱ ከፊት ለፊታቸው ተቀመጠ..ጉሮሮውን አፀዳዳና የመግቢያ ንግግሩን ጀመረ
‹‹በሰዎች መካከል ለተለያየ አለማ ተብለው የሚደረጉ የእርስ በርስ ጉድኝቶችና ቁርኝቶች አሉ፡፡ከነዛ መካከል ግን በጣም ውስብስቡ የጠበቀውና የጠለቀው ግንኙነት በአንድ ወንድ እና ሴት መካከል የሚፈጠር የጋብቻ ጉድኝት ነው፡፡በጋብቻ ውስጥ የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት ሁሉ ጊዜ ቀላል የተባለ መንገድ አይገኝም….አንዱ ጋብቻ ውስጥ የሚፈጠረው ችግር ከሌላው ጋብቻ ችግር በአይነትም በይዘትም ፍፁም የተለየ በመሆን ችግሩን ለማስተካከል የሚወሰደውም እርምጃ የዛኑ ያህል የተለያ ነው፡፡በዛ ላይ ሁሉም ችግሮች እዲፈቱ  በጥንዶቹ  መካከል  ስክነት፣  ትዕግስትን፣ጥረትን  እና   እራስ  መግዛትን

ይጠይቃል፡፡አሁን ልብ በሉ ፣ጥረታችን በመካለላችሁ ያላውን ግጭትና ጭቅጭቅ ሙሉ በሙሉ ማስወገድ አይደልም..አይ እንደዛማ አይሆንም እናንተ ሰው ናቸው፣ሁለት ሰዎች ደግሞ በአንድ ጣሪያ ስር አብረው እስከኖሩ ድረስ በሆነ ነገር መነጋገራቸውና በነገሩ ላይ የተለያየ ተቃራኒ ሃሳብ ማንፀባረቃቸው አይቀርም…ስለዚህ መነጋገርና መጨቃጨቃችሁ ኖርማል ነው…አሁን ምንድነው ምናደርገው በማንኛውም ጉዳይ ላይ አለመግባባት ተከስቶ ስትነጋገሩ በምን መልኩ ነው ኮምንኬት የምታደርጉት..?ነገሩን ማስረዳትና ማሳመን ላይ ነው ትኩረታችሁ ወይስ ያንን ምክንያት አድርጎ በስድብና በዘለፋ ማጥቃትና ልብ መስበር…አያችሁ ትልቁ ችግር መጋጨታችን ሳይሆን በያንዳንዱ ግጭታችን አንዳችን ለሌላቸውን የልብ ቁስለትና የነፍስ ህመም መስጠታችን ነው፡፡ማጥፋት ያለብን እርስ በርስ መወጋጋቱን ነው…አንዳችን ሌላችን ላይ በምንም አይነት ሰበብ የሚያቆስል ጦር አስበን አይደለም አምልጦን እንኳን መወርወር የለብንም፡፡
እርስ በርስ ከፍ ባለ ቃላት በተነጋገራችሁ ቁጥር ደግሞ እየተጣላችሁ መሆኑን አታስቡት..መጣላት ቃሉ እራሱ አሉታዊ ነው፡፡እየተጣላችሁ ሳይሆን በጋለ ስሜት እየተነጋገራችሁ ነው፡፡በቃ እንዲህ ነው ማሰብ ያለባችሁ፡፡እንደዛ ካሰባችሁ ቀጥታ ችግሩ በጋለ ስሜት መነጋገራች ብቻ ስለሆነ ስሜታችሁን በማረጋጋት ነገሩን ትፈታላችሁ፡፡እየተጣላን ነው ብላችሁ ካሰባችሁ ግን ገና ይቅርታ የሚጠይቅ ሰው ወይም ሽማግሌ ልትፈልጉ ነው፡፡ልብ በሉ ጮክ ብሎ መናጋገር ሁል ጊዜ መጣላት አይደለም ..አዎ አብዛኛውን ጊዜ በጋለ ስሜት መነጋገር ነው፡፡ሌላው በምንም አይነት ሁኔታ ንግግራችሁ ሰው ፊት አይሁን፡፡የምንወደው ሰው ላይ ያለንን ቅሬታ ብቻውን በሆነበት ጊዜ ነው መናገር ያለብን…እንደዛ ሲሆን ነው ውጤታማና ጥፈቱን ለማረም ፍቃደኛ የሚሆነው…ወቀሳው..ሰው ፊት ሲሆን ግን ሰውዬው የበለጠ በእኛ ቅሬታ እንዲያድርበት መንገድ ያመቻቻል፡፡
‹‹እንግዲ ሁላተችሁም እንደምታውቁት አሁን ለእኛ እዚህ መገኘት ዋናዋ ምክንያት በፀሎት ነች፡፡እኔ በስራ በተለይ ከሀገር ውጭ በነበርኩበት ጊዜ በጣም ብዙ ባለትዳሮችን አማክሬያለሁ ትዳራችውም መካከል ያለውን ችግር በመተጋገዝ ለመፍታት ችያለሁ....በብዙዎችም ረክቼለው..ከብዙ ቤተሰቦች ጋርም እቤተሰብ ለመሆን ችያለው….ግን እመኑኝ እንዲህ እንደእናነተ የተለየ ጉዳይ ገጥሞኝ አያውቅም››


ስርዝ ድልዝ ደብዳቤ
(

እዚህ ደብዳቤ ላይ....
ልነግርሽ ያሰብኩት
አስቤ የፃፍኩት
ፅፌ የሰረዝኩት
ሰርዤ የላኩት
ስርዝ ድልዝ ሆኖ አልነበብ ካለሽ
ሳልሰርዘው በፊት …
ሀሳቡ መልእክቱ - ምን ይላል መሰለሽ
.
.
.
.

መግቢያው
መደምደሚያው - ሀተታው በሙላ
ሌላ አይናገርም….
ከናፈቅሽኝ እና - ካፈቀርኩሽ ሌላ፡፡

በላይ በቀለ ወያ


ሰላም ሰላም ዉድ አንባቢያን እንዴት ናችሁ ሰዉ ሲጠፋ አጠይቁማ😔 
ለማንኛዉም 😁ይቺን ጥያቄ ካነበብኩት ላካፍላችሁ እስቲ ተሳተፉ👇👇👏👏👏
አባባሉን ጨርሱት 
1. የግዜ እንጂ የሰው....... 
2. የሚያልፍ ቀን.......
3. እንዲህ ልጠግብ....
4. መሸጥ የለመደ..  
5. ሁሉን ቢናገሩት.....

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.