❤ #_የርኩሳን_መናፍስት_ፈተና_በትዳር_ሕይወት ❤
#_ክፉ_መናፍስት_በትዳር_እና_በሩካቤ_ሥጋ_ጣልቃ_መግባት
ወዳጆች ሆይ ክፉ መናፍስት በትዳር ሕይወታችን፣ በሩካቤ ሥጋ ደስታችን እንዴት ጣልቃ እየገቡ እንደሚበጠብጡ እና እንደሚያናውጡ በዝርዝር እናያለን። እኔ ሳልሰለች የጻፍኩትን እናንተ ሳትሰለቹ አንብቡት።
❤ 1ኛ/ ዓይነ ጥላ
ዓይነ ጥላ ገርጋሪ ምቀኛ ክፉ መንፈስ ነው፡፡ ይህ ክፉ መንፈስ አድብቶ በመተናኮል ዕድላችንን በመዝጋት እጃችን ገባ ያልነውን ነገር በማሳጣት ይተናኮላል፡፡ ዓይነ ጥላ አብረውን ከሚወለዱና ተወልደን ከጊዜ በኋላ ከሚጠናወቱን ክፉ መንፈስ አንዱ ነው፡፡
ዓይነ ጥላ ያለባቸው ባል ወይም ሚስት በትዳራቸው ሰላም፣ ፍቅር፣ መግባባት በመሃላቸው በፍጹም አይኖርም፡፡ በተለይ በሩካቤ ሥጋ አይስማሙም፣ አይጣጣሙም፣ አይግባቡም፡፡
የዓይነ ጥላ መንፈስ ተጠቂ ከሆኑ እንኳን ሩካቤ ሥጋን በመፈቃቀድ ሊፈጽሙ ቀርቶ አብሮ መተኛት መተቃቀፍ አይወዱም፡፡ መንፈሱ የባልን ሰውነት ወይም የሚስትን ሰውነት እንደ ባዕድ አካል በማሳየት እንዲቀፈው/እንዲቀፋት በማድረግ ምክንያት የሌለውን ጥላቻ በመሃላቸው ይዘራል፡፡ በሩካቤ ሥጋም ደስታ የሚባል ያሳጣቸዋል፡፡ ሩካቤ ሥጋን የሚፈጽሙት ስለተጋቡ ብቻ እንጂ ወደውና ፈቅደው አይደለም፡፡ ደመ ቀዝቃዛ ያደርጋቸዋል፡፡
ከትዳር በፊት ወደ ሕይወታቸው ሰተት ብሎ የገባው መንፈስ በትዳራቸው ውስጥ ራሱን በተለያየ ጠባይና መልክ በመግለጥ፣ ለትዳራቸው መበጣበጥ እና መናወጥ ምክንያት ይሆናል፡፡ በማግባታቸው የተበሳጨው ዓይነ ጥላ በትዳር ኑሮአቸው ውስጥ የበቀል መርዙን እየረጨ፣ ትዳሩን እያቀጨጨ ለፍቺ ይዳርጋል፡፡
ዓይነ ጥላ በትዳር ሕይወት ሰላም በመንሳት እና በሩካቤ ሥጋ ጊዜ ስሜት በማጥፋት፣ የሩካቤ ሥጋ ደስታን በማበላሸት የተካነ ስለሆነ የመንፈሱን ጠባይ አውቃችሁ ልትነቁበት እና በጾም፣ በጸሎትና በስግደት ልትዋጉት እንዲሁም በቅዱስ ቁርባን ጸጋ ከሕይወታችሁ ልታርቁት ይገባል፡፡ ምክንያቱም መንፈሱ ሸፍጠኛና ከጠባይ ጋር የሚመሳሰል በመሆኑ የብዙዎችን ትዳር ለፍቺ አብቅቷል፡፡
❤ 2ኛ/ ዛሮች፦
ከሁለት አንዳቸው ዛር እና የዛር ውላጅ፣ ወንድ ወይም ሴት ዛር ካለባቸው ትዳራቸው አደገኛ ችግር ውስጥ ይገባል፡፡ ዛሩ ስለሚቀና ባልና ሚስትን ለማተራመስ ኩርፊያን፣ ንትርክን ጭቅጭቅን፣ ብስጭትን፣ አለመግባባትን፣ አለመተዛዘንን፣ ጥላቻን እንደ ግብዓት በመጠቀም ፍቅርን በማቀዝቀዝ ትዳሩን በፍቺ መንገድ እንዲጓዝ ይዳርጋል፡፡
ባስ ሲልም ደም የለመደ ዛር ከሆነ ጸብ በማንሳት ደም ያፋስሳል ከተቻለም ነፍስ ያዋድቃል፡፡ ዛሩ በአባትና በእናት ላይ ካለ በግንኙነት ወቅት ከዘር ጋር በመዋሐድ በማኅፀን ከፅንሱ ጋር አድጐ በመወለድ ደባል ሆኖ ያድጋል፡፡ ዛር እስከ ሰባት ትውልድ ድረስ በመውረድ ቤተሰብን በማፈራረስ ሰላማቸውን በመደምሰስ ቤተሰብን ይዘበራርቃል፡፡
ዛር ልጆች ከተወለዱ በኋላ በልጆች እእምሮ በማደር አእምሮአቸውን በመዝጋት ትምህርት እንዳይገባቸው በማድረግ ቤተሰብንና ተማሪውን ተስፋ ያስቆርጣል፡፡ በዚህም ልጁ በቤተሰብ እንዲጠላ ያደርገዋል፡፡ ፍራቻን እያስተማረ ያሳድገውና በራስ መተማመኑን በማጥፋት ለቤተሰቡ ለሀገሩ ደንታ ቢስ በማድረግ ውድ ሕይወቱን በመውረስ ለራሱ ለጥፋት ዓላማ ይጠቀምበታል፡፡
ሌብነትን፣ ወንጀልን፣ ክፉ ሱስን፣ መጠጥን፣ ዝሙትን፣ ጠበኛነትን እና ነውጠኝነትን በማስለመድ ምግባረ ቢስነትን በማላበስ የእርግማን ትውልድ እንዲሆን ያደርገዋል፡፡ ስለዚህ ወላጆች ሆይ ልጆች የሚታነጹት በእናንተ መልካምና እኩይ መሠረት ላይ ስለሆነ ዛሬ እንደ ቀልድ የዘራችሁትን ነገ መከመር እስኪያቅታችሁ ድረስ ስለምታጭዱ ልትጠነቁና በእውነተኛው መንገድ ልትሄዱ ይገባል፡፡ ዛሬ ‹‹የተረገመ ያልተባረከ›› እያላችሁ የምትረግሙት ልጅ ትላንት የናንተ ወይም የቤተሰባችሁ ጠንቅ ተርፎት ነውና ልታዝኑላቸው ይገባል፡፡
የዛር መንፈስ አንዱ መጥፎ መገለጫው በዓል በመጣ ቁጥር ለምሳሌ በዘመን መለወጫ፣ በገና እና በትንሣኤ በዓላት የቤተሰቡን ደስታ ለማጥፋት እና ሰላም ለመንሳት የማይረባ እና ውኃ የማያነሳ አለመግባባትንና ጠብን ተጠቅሞ ቤተሰቡን በማተራመስ፣ የበዓሉን ዐውድ ያጠፋባቸዋል፡፡
ወዳጆቼ በባል ወይም በሚስት ላይ የራሳቸው አልያም የዛር መንፈስ ካለ ካላወቁበት እና ካልነቁበት መቼም ቢሆን በዓል በመጣ ቁጥር መጣላታቸው፣ በዓልን በኩርፊያ ማሳለፋቸው አይቀርም፡፡ እንዲሁም ከሁለት አንዳቸው ላይ በሕመም ተመስሎ በመቀመጥ ለበዓል የደስታ መዋያ ያሰቡት ገንዘብ የሐኪም ቀለብ ያደርጋል፡፡
ከላይ እንደጠቀስኩላችሁ በተለይ የወንድ ዛር በሴቷ ላይ ካለ ከባሏ ጋር ሩካቤ ሥጋ መፈጸም ቀርቶ አብሮ መተኛት እና ማውራት ያስጠላታል፡፡ ሌሊት ከባሏ አጠገብ ተኝታ በእንቅልፍ ልቧ የወንድ ዛሩ ይገናኛታል፡፡ በደመ ነፍስም በተኛችበት የሚጫናት፣ የሚነካት፣ ሰውነቷን የሚዳስሳት ሰው መሰል ነገር ይሰማታል፡፡
እንዲሁም ሴት ዛር በወንዱ ላይ ካለች በተለይ በስንፈተ ሩካቤ ይጠቃል፡፡ በሕልመ ሌሊትም እጅጉን ይመታል፡፡ ጠባዩ እየተቀያየረ በውኃ ቀጠነ ይጨቃጨቃል፣ እንደ ሕፃን ይነጫነጫል፡፡ ሚስቱ ታስጠላዋለች፡፡ አብሯት ቢተኛም ሩካቤ ሥጋ ለመፈጸም እጅጉን ይቸገራል፡፡ በባል ላይም ሴት ዛር ካለች በሚያውቃት እና በማያውቃት፣ በቤተሰብ እየተመሰለች ሌሊት በተኛበት ትገናኘዋለች፡፡
❤ 3ኛ/ ፅንስን የሚያጨናግፉ እና በማሕፀን የሚገድሉ ክፉ መናፍስት/ሾተላይ ፦
ብዙዎች በተደጋጋሚ የፅንስ መጨናገፍ እና በማኅፀን ውስጥ የፅንስ መጥፋት ያጋጥማቸዋል፡፡ በተለይ በማኅፀን ውስጥ ፅንስ ሲጠፋ በሕክምናው ሾተላይ ተብሎ ስም ይሰጠዋል፡፡
ሕክምናው የሕክምናውን ጥበብ እንጂ የክፉ መናፍስቱን ተንኮል ስለማያውቅ ከቤተሰቦቻችን በወረስናቸው፣ በራሳችንም ባመጣናቸው የዛር መንፈስ እንዲሁም በዓይነ ጥላና እና በመተት በድግምት ፅንስ እንደሚጨናገፍ እና በማኅፀን እያሉ እንደሚጠፋ አያውቅም፡፡ ስለዚህ የተጨናገፈውና በማኅፀን የሚጠፋው ፅንስ ሁሉ ሾተላይ ይባላል፡፡
አጅሬም በሾተላይ ስም ራሱን ሰውሮ ሥራውን በገሃድ ይሠራል፡፡
በነገራችን ላይ ሕክምናው በተደጋጋሚ ፅንስ የመጨናገፍ ችግር የሚገጥማቸውንና የፅንሱን የመጨናገፍ ምክንያት በውል የማያውቃቸውን ‹‹መንስኤው የማይታወቅ›› ወይም በሕክምናው ቋንቋ ‘አይድዮ ፓቲክ’ ይለዋል፡፡
በሕክምናው ሾተላይ የሚባለው አንዲት ሴት የደም ዓይነቷ አር ኤች ኔጌቲቭ /Rh-/ ሆኖ ከዚህ በፊት አር ኤች ፖዘቲቭ /Rh +/ የሆነ ደም ወደ ሰውነቷ ሲገባ አር ኤች ፓዘቲቭ የሆኑ የደም ሕዋሶችን የሚያጠፋ ንጥረ-ነገር በደሟ ውስጥ ይመረታል፡፡ ይህ ንጥረ-ነገር አንዴ ከተመረተ በደሟ ውስጥ እስከ ሕይወት ፍጻሜ ድረስ ይኖራል፡፡
በዚህም በማኅፀንዋ ውስጥ የያዘችውን ፅንስ የደም ዓይነቱ አር ኤች ፖዘቲቭ ከሆነ የተመረተው ንጥረ-ነገር ፅንሱን እንደ ባዕድ አካል ስለሚቆጥረው ያጠቃዋል ፅንሱም ይጠፋል በማለት ይገልጻል፡፡
ወዳጆቼ ከላይ እንዳየነው ሾተላይን ወደ መንፈሳዊው ዓለም ስናመጣው ፅንስን የሚያጨናግፍ እና በማኅፀን እንዳለ የሚያጠፋው የቅድመ አያቶቻችን፣ የአያቶቻችን፣ የእናት አባታችን ዛር እንዲሁም ዓይነ ጥላና እና መተት ድግምት ነው፡፡ አጋንንት፣ ሰይጣን፣ ዛር፣ ዓይነ ጥላ ፅንስን ተዋሕደው በማጨናገፍ ይታወቃሉ፡፡
#_ክፉ_መናፍስት_በትዳር_እና_በሩካቤ_ሥጋ_ጣልቃ_መግባት
ወዳጆች ሆይ ክፉ መናፍስት በትዳር ሕይወታችን፣ በሩካቤ ሥጋ ደስታችን እንዴት ጣልቃ እየገቡ እንደሚበጠብጡ እና እንደሚያናውጡ በዝርዝር እናያለን። እኔ ሳልሰለች የጻፍኩትን እናንተ ሳትሰለቹ አንብቡት።
❤ 1ኛ/ ዓይነ ጥላ
ዓይነ ጥላ ገርጋሪ ምቀኛ ክፉ መንፈስ ነው፡፡ ይህ ክፉ መንፈስ አድብቶ በመተናኮል ዕድላችንን በመዝጋት እጃችን ገባ ያልነውን ነገር በማሳጣት ይተናኮላል፡፡ ዓይነ ጥላ አብረውን ከሚወለዱና ተወልደን ከጊዜ በኋላ ከሚጠናወቱን ክፉ መንፈስ አንዱ ነው፡፡
ዓይነ ጥላ ያለባቸው ባል ወይም ሚስት በትዳራቸው ሰላም፣ ፍቅር፣ መግባባት በመሃላቸው በፍጹም አይኖርም፡፡ በተለይ በሩካቤ ሥጋ አይስማሙም፣ አይጣጣሙም፣ አይግባቡም፡፡
የዓይነ ጥላ መንፈስ ተጠቂ ከሆኑ እንኳን ሩካቤ ሥጋን በመፈቃቀድ ሊፈጽሙ ቀርቶ አብሮ መተኛት መተቃቀፍ አይወዱም፡፡ መንፈሱ የባልን ሰውነት ወይም የሚስትን ሰውነት እንደ ባዕድ አካል በማሳየት እንዲቀፈው/እንዲቀፋት በማድረግ ምክንያት የሌለውን ጥላቻ በመሃላቸው ይዘራል፡፡ በሩካቤ ሥጋም ደስታ የሚባል ያሳጣቸዋል፡፡ ሩካቤ ሥጋን የሚፈጽሙት ስለተጋቡ ብቻ እንጂ ወደውና ፈቅደው አይደለም፡፡ ደመ ቀዝቃዛ ያደርጋቸዋል፡፡
ከትዳር በፊት ወደ ሕይወታቸው ሰተት ብሎ የገባው መንፈስ በትዳራቸው ውስጥ ራሱን በተለያየ ጠባይና መልክ በመግለጥ፣ ለትዳራቸው መበጣበጥ እና መናወጥ ምክንያት ይሆናል፡፡ በማግባታቸው የተበሳጨው ዓይነ ጥላ በትዳር ኑሮአቸው ውስጥ የበቀል መርዙን እየረጨ፣ ትዳሩን እያቀጨጨ ለፍቺ ይዳርጋል፡፡
ዓይነ ጥላ በትዳር ሕይወት ሰላም በመንሳት እና በሩካቤ ሥጋ ጊዜ ስሜት በማጥፋት፣ የሩካቤ ሥጋ ደስታን በማበላሸት የተካነ ስለሆነ የመንፈሱን ጠባይ አውቃችሁ ልትነቁበት እና በጾም፣ በጸሎትና በስግደት ልትዋጉት እንዲሁም በቅዱስ ቁርባን ጸጋ ከሕይወታችሁ ልታርቁት ይገባል፡፡ ምክንያቱም መንፈሱ ሸፍጠኛና ከጠባይ ጋር የሚመሳሰል በመሆኑ የብዙዎችን ትዳር ለፍቺ አብቅቷል፡፡
❤ 2ኛ/ ዛሮች፦
ከሁለት አንዳቸው ዛር እና የዛር ውላጅ፣ ወንድ ወይም ሴት ዛር ካለባቸው ትዳራቸው አደገኛ ችግር ውስጥ ይገባል፡፡ ዛሩ ስለሚቀና ባልና ሚስትን ለማተራመስ ኩርፊያን፣ ንትርክን ጭቅጭቅን፣ ብስጭትን፣ አለመግባባትን፣ አለመተዛዘንን፣ ጥላቻን እንደ ግብዓት በመጠቀም ፍቅርን በማቀዝቀዝ ትዳሩን በፍቺ መንገድ እንዲጓዝ ይዳርጋል፡፡
ባስ ሲልም ደም የለመደ ዛር ከሆነ ጸብ በማንሳት ደም ያፋስሳል ከተቻለም ነፍስ ያዋድቃል፡፡ ዛሩ በአባትና በእናት ላይ ካለ በግንኙነት ወቅት ከዘር ጋር በመዋሐድ በማኅፀን ከፅንሱ ጋር አድጐ በመወለድ ደባል ሆኖ ያድጋል፡፡ ዛር እስከ ሰባት ትውልድ ድረስ በመውረድ ቤተሰብን በማፈራረስ ሰላማቸውን በመደምሰስ ቤተሰብን ይዘበራርቃል፡፡
ዛር ልጆች ከተወለዱ በኋላ በልጆች እእምሮ በማደር አእምሮአቸውን በመዝጋት ትምህርት እንዳይገባቸው በማድረግ ቤተሰብንና ተማሪውን ተስፋ ያስቆርጣል፡፡ በዚህም ልጁ በቤተሰብ እንዲጠላ ያደርገዋል፡፡ ፍራቻን እያስተማረ ያሳድገውና በራስ መተማመኑን በማጥፋት ለቤተሰቡ ለሀገሩ ደንታ ቢስ በማድረግ ውድ ሕይወቱን በመውረስ ለራሱ ለጥፋት ዓላማ ይጠቀምበታል፡፡
ሌብነትን፣ ወንጀልን፣ ክፉ ሱስን፣ መጠጥን፣ ዝሙትን፣ ጠበኛነትን እና ነውጠኝነትን በማስለመድ ምግባረ ቢስነትን በማላበስ የእርግማን ትውልድ እንዲሆን ያደርገዋል፡፡ ስለዚህ ወላጆች ሆይ ልጆች የሚታነጹት በእናንተ መልካምና እኩይ መሠረት ላይ ስለሆነ ዛሬ እንደ ቀልድ የዘራችሁትን ነገ መከመር እስኪያቅታችሁ ድረስ ስለምታጭዱ ልትጠነቁና በእውነተኛው መንገድ ልትሄዱ ይገባል፡፡ ዛሬ ‹‹የተረገመ ያልተባረከ›› እያላችሁ የምትረግሙት ልጅ ትላንት የናንተ ወይም የቤተሰባችሁ ጠንቅ ተርፎት ነውና ልታዝኑላቸው ይገባል፡፡
የዛር መንፈስ አንዱ መጥፎ መገለጫው በዓል በመጣ ቁጥር ለምሳሌ በዘመን መለወጫ፣ በገና እና በትንሣኤ በዓላት የቤተሰቡን ደስታ ለማጥፋት እና ሰላም ለመንሳት የማይረባ እና ውኃ የማያነሳ አለመግባባትንና ጠብን ተጠቅሞ ቤተሰቡን በማተራመስ፣ የበዓሉን ዐውድ ያጠፋባቸዋል፡፡
ወዳጆቼ በባል ወይም በሚስት ላይ የራሳቸው አልያም የዛር መንፈስ ካለ ካላወቁበት እና ካልነቁበት መቼም ቢሆን በዓል በመጣ ቁጥር መጣላታቸው፣ በዓልን በኩርፊያ ማሳለፋቸው አይቀርም፡፡ እንዲሁም ከሁለት አንዳቸው ላይ በሕመም ተመስሎ በመቀመጥ ለበዓል የደስታ መዋያ ያሰቡት ገንዘብ የሐኪም ቀለብ ያደርጋል፡፡
ከላይ እንደጠቀስኩላችሁ በተለይ የወንድ ዛር በሴቷ ላይ ካለ ከባሏ ጋር ሩካቤ ሥጋ መፈጸም ቀርቶ አብሮ መተኛት እና ማውራት ያስጠላታል፡፡ ሌሊት ከባሏ አጠገብ ተኝታ በእንቅልፍ ልቧ የወንድ ዛሩ ይገናኛታል፡፡ በደመ ነፍስም በተኛችበት የሚጫናት፣ የሚነካት፣ ሰውነቷን የሚዳስሳት ሰው መሰል ነገር ይሰማታል፡፡
እንዲሁም ሴት ዛር በወንዱ ላይ ካለች በተለይ በስንፈተ ሩካቤ ይጠቃል፡፡ በሕልመ ሌሊትም እጅጉን ይመታል፡፡ ጠባዩ እየተቀያየረ በውኃ ቀጠነ ይጨቃጨቃል፣ እንደ ሕፃን ይነጫነጫል፡፡ ሚስቱ ታስጠላዋለች፡፡ አብሯት ቢተኛም ሩካቤ ሥጋ ለመፈጸም እጅጉን ይቸገራል፡፡ በባል ላይም ሴት ዛር ካለች በሚያውቃት እና በማያውቃት፣ በቤተሰብ እየተመሰለች ሌሊት በተኛበት ትገናኘዋለች፡፡
❤ 3ኛ/ ፅንስን የሚያጨናግፉ እና በማሕፀን የሚገድሉ ክፉ መናፍስት/ሾተላይ ፦
ብዙዎች በተደጋጋሚ የፅንስ መጨናገፍ እና በማኅፀን ውስጥ የፅንስ መጥፋት ያጋጥማቸዋል፡፡ በተለይ በማኅፀን ውስጥ ፅንስ ሲጠፋ በሕክምናው ሾተላይ ተብሎ ስም ይሰጠዋል፡፡
ሕክምናው የሕክምናውን ጥበብ እንጂ የክፉ መናፍስቱን ተንኮል ስለማያውቅ ከቤተሰቦቻችን በወረስናቸው፣ በራሳችንም ባመጣናቸው የዛር መንፈስ እንዲሁም በዓይነ ጥላና እና በመተት በድግምት ፅንስ እንደሚጨናገፍ እና በማኅፀን እያሉ እንደሚጠፋ አያውቅም፡፡ ስለዚህ የተጨናገፈውና በማኅፀን የሚጠፋው ፅንስ ሁሉ ሾተላይ ይባላል፡፡
አጅሬም በሾተላይ ስም ራሱን ሰውሮ ሥራውን በገሃድ ይሠራል፡፡
በነገራችን ላይ ሕክምናው በተደጋጋሚ ፅንስ የመጨናገፍ ችግር የሚገጥማቸውንና የፅንሱን የመጨናገፍ ምክንያት በውል የማያውቃቸውን ‹‹መንስኤው የማይታወቅ›› ወይም በሕክምናው ቋንቋ ‘አይድዮ ፓቲክ’ ይለዋል፡፡
በሕክምናው ሾተላይ የሚባለው አንዲት ሴት የደም ዓይነቷ አር ኤች ኔጌቲቭ /Rh-/ ሆኖ ከዚህ በፊት አር ኤች ፖዘቲቭ /Rh +/ የሆነ ደም ወደ ሰውነቷ ሲገባ አር ኤች ፓዘቲቭ የሆኑ የደም ሕዋሶችን የሚያጠፋ ንጥረ-ነገር በደሟ ውስጥ ይመረታል፡፡ ይህ ንጥረ-ነገር አንዴ ከተመረተ በደሟ ውስጥ እስከ ሕይወት ፍጻሜ ድረስ ይኖራል፡፡
በዚህም በማኅፀንዋ ውስጥ የያዘችውን ፅንስ የደም ዓይነቱ አር ኤች ፖዘቲቭ ከሆነ የተመረተው ንጥረ-ነገር ፅንሱን እንደ ባዕድ አካል ስለሚቆጥረው ያጠቃዋል ፅንሱም ይጠፋል በማለት ይገልጻል፡፡
ወዳጆቼ ከላይ እንዳየነው ሾተላይን ወደ መንፈሳዊው ዓለም ስናመጣው ፅንስን የሚያጨናግፍ እና በማኅፀን እንዳለ የሚያጠፋው የቅድመ አያቶቻችን፣ የአያቶቻችን፣ የእናት አባታችን ዛር እንዲሁም ዓይነ ጥላና እና መተት ድግምት ነው፡፡ አጋንንት፣ ሰይጣን፣ ዛር፣ ዓይነ ጥላ ፅንስን ተዋሕደው በማጨናገፍ ይታወቃሉ፡፡