አንዳንዴ ሊወልዱ ጥቂት ወራት እና ጥቂት ቀናት ብሎም ዕለቱን ለፅንስ ክትትል ምርመራና ለመውለድ ሆስፒታል ሲሄዱ በሐኪሞች ‹‹ፅንሱ ልክ አይደለም፣ ጠፍቷል›› ተብሎ ጆሮ ጭው፣ ልብ ክው የሚያደርግ መርዶ የሚሰሙት በዛር፣ በዓይነ ጥላና በመተት ድግምት በሚፈጠር አሳዛኝ ክሥተት ነው፡፡
ልብ ካላችሁ እህቶቼ ብዙ ፅንሱ ከመጨናገፉ በፊት አንዳንዶች ሕልም ያያሉ፡፡ የሆነ ጥቁር ሰው ሲታገላችሁ፣ ማኅፀናችሁን ሲረግጣችሁ፣ ሲመታችሁ፣ የምትወዱትን ነገር ታግሎ ሲነጥቃችሁ፣ የሆነ ሰው እላያችሁ ላይ ሲከመርባችሁ፣ ሲያንቃችሁ እና ሲተናነቃችሁ ወዘተ ታልማላችሁ፡፡
ይህ የሚሆነው ከእርግዝናችሁ የቀና የቤተሰብ ዛር፣ ዓይነ ጥላ እና በተለይ በትዳራችሁ፣ በእርግዝናችሁ የሚቀናባችሁ ሰው የመተት አጋንንት ሲያስልክባችሁ እና ክፉ መናፍስቱ ሲዋጋችሁ ነው፡፡ ይህን ሕልም ስታዩ የዛኑ ቀን አልያም በጥቂት ቀናት ውስጥ ምንም ሳትሆኑ በድንገት ደም ይፈሳቹኃል ከዛም ፅንሱ ይቋረጣል፡፡
❤ 5ኛ/ መስተፋቅር ፦
መስተፋቅር ማለት አንድ ወንድ አንዲትን ሴት ያለ ፍላጐትዋ በአጋንንት ጥበብ እንድትወደው ማድረግ ነው፡፡ መስተፋቅር የተደረገበት ሰው ከፍተኛ ፍቅር ውስጥ በመግባት በቤተሰብ እንኳን ተው/ተይ ቢባሉ ከቤተሰብ እስከ መለያየት ተወራርደው እንቢኝ ይላሉ፡፡
በመስተፋቅር የተጀመረ ትዳር ትልቁ ችግር እግዚአብሔር የመሠረተው ሳይሆን በሰይጣን ጥበብ የተመሠረተ ስለሆነ አይጸናም፡፡ በጊዜ ሂደት ምስጢሩ ይወጣል አልያም መስተፋቀሩ ይከሽፋል፡፡ ያኔ በመናፍስት ጥበብ ያዋረሱት ፍቅር እንደ ጉም ይተንና የተደረገበት ሰው እንደ ሰመመን መርፌ ከነቃ ሁሉም ነገር ይበላሻል፡፡
በመስተፋቅር በተመሠረተ ትዳር የሚወለዱትም ልጆች የመናፍስቱ ሰለባ ይሆናሉ፡፡ ጤና ከማጣት እስከ መደንዘዝ ይደርሳሉ፡፡ በመስተፋቅር በተመሠረተ ትዳር የሚወለዱት ልጆች የአጋንንቱ ግብር ናቸው፡፡
ትዳሩ የተመሠረተው እና ልጆቹም የሚመጡበት መንገድ በእግዚአብሔር ዘንድ ስለማይወደድና ብሎም ስለማይባረኩ የእናት ወይም የአባታቸው አጋንንት እየተጠናወታቸው ለሀገር እና ለወገን በተለይም ለቤተ ክርስቲያን የማይጠቅሙ፣ ከጥቅማቸው ጥፋታቸው ያመዘነ ልጆች ይሆናሉ፡፡
❤ 6ኛ/ ቡዳ ፦
ወዳጆቼ እንደ ቀልድ የምንሰማውና የምናየው የቡዳ መንፈስ ጣጣው ብዙ ነው፡፡ አንዲት ሴት በውበቷ፣ በጸጉሯ፣ በቁመናዋ የአጋንንት ጥርስ ውስጥ ገብታ፤ በቡዳ መንፈስ ተበልታ ከሆነ በትዳር ሕይወቷ እጅጉን ልትቸገር ትችላለች፡፡
በተለይ በጸባይ እና በልጅ ማጣት ትቸገራለች፡፡ የቡዳ መንፈስ ያለባት ሴት አመሏ ንጭንጭ ይላል፣ ሆድ የሚብሳት እና ለቅሶ የሚቀድማት ናት፡፡ በተለይ መልከኛ ከሆነች ራስዋን የምትጥል፣ ለውበቷ ግድ የሌላት ዝርክርክ ትሆናለች፡፡
እንዲሁም የቡዳ መንፈሱ በማኅፀኗ ውስጥ አሸምቆ በመደበቅ ፅንስ ሊያጨናግፍባት እና ሊያጠፋባት ይችላል፡፡ በቡዳ ዓይኗን ከተበላች ዓይኗን ያቃጥላታል፣ አጥርቶ የማየት ችግር ይገጥማታል፣ ውበቷ ይበላሻል ለምሳሌ ፊቷ እንደ ማድያት ባለ ሁኔታ ይበልዛል፣ በወጣትነቷ ፊቷ የአሮጊት ፊት ይመስላል፣ ያለ እድሜዋ ፊቷ ይሸበሸባል፡፡ ማኅፀኗን ይቆርጣታል የሚገላበጥ እና ውስጡ የሆነ ነገር ያለ መስሎ ይሰማታል፡፡
ወዳጆቼ ስለ ቡዳ ካነሳን እንደው እርግዝና በቡዳ እንደሚበላ ታውቃላችሁ? ብዙዎቻችን የቡዳ መንፈስ በውበት በደም ግባት ወዘተ የሚገባ ብቻ ይመስለናል፡፡ ግን እርግዝናም በቡዳ ይበላል፡፡ እናቶቻችን ሲያረግዙ ማርገዛቸውን ለሰው የማያሳውቁት፣ እርግዝናቸውን በልብስ ደረብረብ አድርገው የሚሸፍኑት ከዓይነ ወግ ቡዳ ራሳቸውን ለመጠበቅ ብለው ነው፡፡ ልብ ካላችሁ አንዳንድ ሴቶች እርግዝናቸው ያምራል፡፡ ከቁመናቸው ጀምሮ እስከ ፅንሱ አቀማመጥ ላያቸው ለዓይን ደስ ይላሉ፡፡
የቡዳ መንፈስ ደግሞ ከዓይን ተነስቶ ወደ ሰው የሚገባ መንፈስ ስለሆነ እርግዝናቸውን በቡዳ ይበላል፡፡ ከዛማ ብዙም ሳይቆዩ አቅለሸለሸኝ፣ አመመኝ፣ ማኅፀኔን ቆረጠኝ ወዘተ በማለት ደም ሊመታቸውና ፅንሱ ሊጨናገፍ ብሎም ሊጠፋ ይችላል፡፡
ስለዚህ እባካችሁ እርጉዝ ስትሆኑ ፅንሱን ሰው ይይልኝ፣ ማርገዜን ምቀኞቼ ይወቁልኝ፣ ዓይናቸው ደም ይልበስ እያላችሁ ስስ ልብስ በመልበስ አትታዩ፡፡ በተለይ የመውለጃ ጊዜያችሁ ሲደርስ ሰው የሚበዛበት ቦታ በመታየት እና በመዝናናት ስም ዞር ዞር ከማለት ታቀቡ፡፡
ቤቢ ሻወር እያላችሁ እርግዝናችሁን በቡዳ አታስበሉ፡፡ ቤቢ ሻወር ብላችሁ እዩልኝ እንዳላችሁ በቡዳ የተበላ፣ ጤና ያጣ ልጅ ወልዳችሁ ልጄን አትዩብኝ፣ ደብቁልኝ እንዳትሉ ተጠንቀቁ፡፡
ወዳጆቼ ከላይ ያየናቸው ርኩሳን መናፍስት፣ በትዳራችን ላይ ጣልቃ በመግባት፣ ካለመግባባት እስከ መለያየት ሊያደርሱን ስለሚችሉ በትዳራችን ውስጥ የሚፈጠሩትን ነገሮች ረጋ ብሎ፣ አስተውሎ ማየት ያስፈልጋል፡፡
በተረፈ ትዳራችሁ በክፉ መናፍስትም ይሁን በሰው ተንኮል ችግር ውስጥ ከገባ፣ የወለድናቸውም ልጆች እክል ከገጠማቸው ንስሐ ገብተን፣ በጸሎት በርትተን በአምልኮት ሕይወት ፊታችንን ወደ እግዚአብሔር ከመለስን ምህረቱን፣ ቸርነቱን ወደ እኛ ይመልሳል፣ መፍትሔም ይሰጠናል፡፡
ቀናችሁን በጸሎት ጀምሩ፣ ማታ በጸሎት እደሩ!
መርጌታ አምደብርሃን ይትባረክ !!!
ልብ ካላችሁ እህቶቼ ብዙ ፅንሱ ከመጨናገፉ በፊት አንዳንዶች ሕልም ያያሉ፡፡ የሆነ ጥቁር ሰው ሲታገላችሁ፣ ማኅፀናችሁን ሲረግጣችሁ፣ ሲመታችሁ፣ የምትወዱትን ነገር ታግሎ ሲነጥቃችሁ፣ የሆነ ሰው እላያችሁ ላይ ሲከመርባችሁ፣ ሲያንቃችሁ እና ሲተናነቃችሁ ወዘተ ታልማላችሁ፡፡
ይህ የሚሆነው ከእርግዝናችሁ የቀና የቤተሰብ ዛር፣ ዓይነ ጥላ እና በተለይ በትዳራችሁ፣ በእርግዝናችሁ የሚቀናባችሁ ሰው የመተት አጋንንት ሲያስልክባችሁ እና ክፉ መናፍስቱ ሲዋጋችሁ ነው፡፡ ይህን ሕልም ስታዩ የዛኑ ቀን አልያም በጥቂት ቀናት ውስጥ ምንም ሳትሆኑ በድንገት ደም ይፈሳቹኃል ከዛም ፅንሱ ይቋረጣል፡፡
❤ 5ኛ/ መስተፋቅር ፦
መስተፋቅር ማለት አንድ ወንድ አንዲትን ሴት ያለ ፍላጐትዋ በአጋንንት ጥበብ እንድትወደው ማድረግ ነው፡፡ መስተፋቅር የተደረገበት ሰው ከፍተኛ ፍቅር ውስጥ በመግባት በቤተሰብ እንኳን ተው/ተይ ቢባሉ ከቤተሰብ እስከ መለያየት ተወራርደው እንቢኝ ይላሉ፡፡
በመስተፋቅር የተጀመረ ትዳር ትልቁ ችግር እግዚአብሔር የመሠረተው ሳይሆን በሰይጣን ጥበብ የተመሠረተ ስለሆነ አይጸናም፡፡ በጊዜ ሂደት ምስጢሩ ይወጣል አልያም መስተፋቀሩ ይከሽፋል፡፡ ያኔ በመናፍስት ጥበብ ያዋረሱት ፍቅር እንደ ጉም ይተንና የተደረገበት ሰው እንደ ሰመመን መርፌ ከነቃ ሁሉም ነገር ይበላሻል፡፡
በመስተፋቅር በተመሠረተ ትዳር የሚወለዱትም ልጆች የመናፍስቱ ሰለባ ይሆናሉ፡፡ ጤና ከማጣት እስከ መደንዘዝ ይደርሳሉ፡፡ በመስተፋቅር በተመሠረተ ትዳር የሚወለዱት ልጆች የአጋንንቱ ግብር ናቸው፡፡
ትዳሩ የተመሠረተው እና ልጆቹም የሚመጡበት መንገድ በእግዚአብሔር ዘንድ ስለማይወደድና ብሎም ስለማይባረኩ የእናት ወይም የአባታቸው አጋንንት እየተጠናወታቸው ለሀገር እና ለወገን በተለይም ለቤተ ክርስቲያን የማይጠቅሙ፣ ከጥቅማቸው ጥፋታቸው ያመዘነ ልጆች ይሆናሉ፡፡
❤ 6ኛ/ ቡዳ ፦
ወዳጆቼ እንደ ቀልድ የምንሰማውና የምናየው የቡዳ መንፈስ ጣጣው ብዙ ነው፡፡ አንዲት ሴት በውበቷ፣ በጸጉሯ፣ በቁመናዋ የአጋንንት ጥርስ ውስጥ ገብታ፤ በቡዳ መንፈስ ተበልታ ከሆነ በትዳር ሕይወቷ እጅጉን ልትቸገር ትችላለች፡፡
በተለይ በጸባይ እና በልጅ ማጣት ትቸገራለች፡፡ የቡዳ መንፈስ ያለባት ሴት አመሏ ንጭንጭ ይላል፣ ሆድ የሚብሳት እና ለቅሶ የሚቀድማት ናት፡፡ በተለይ መልከኛ ከሆነች ራስዋን የምትጥል፣ ለውበቷ ግድ የሌላት ዝርክርክ ትሆናለች፡፡
እንዲሁም የቡዳ መንፈሱ በማኅፀኗ ውስጥ አሸምቆ በመደበቅ ፅንስ ሊያጨናግፍባት እና ሊያጠፋባት ይችላል፡፡ በቡዳ ዓይኗን ከተበላች ዓይኗን ያቃጥላታል፣ አጥርቶ የማየት ችግር ይገጥማታል፣ ውበቷ ይበላሻል ለምሳሌ ፊቷ እንደ ማድያት ባለ ሁኔታ ይበልዛል፣ በወጣትነቷ ፊቷ የአሮጊት ፊት ይመስላል፣ ያለ እድሜዋ ፊቷ ይሸበሸባል፡፡ ማኅፀኗን ይቆርጣታል የሚገላበጥ እና ውስጡ የሆነ ነገር ያለ መስሎ ይሰማታል፡፡
ወዳጆቼ ስለ ቡዳ ካነሳን እንደው እርግዝና በቡዳ እንደሚበላ ታውቃላችሁ? ብዙዎቻችን የቡዳ መንፈስ በውበት በደም ግባት ወዘተ የሚገባ ብቻ ይመስለናል፡፡ ግን እርግዝናም በቡዳ ይበላል፡፡ እናቶቻችን ሲያረግዙ ማርገዛቸውን ለሰው የማያሳውቁት፣ እርግዝናቸውን በልብስ ደረብረብ አድርገው የሚሸፍኑት ከዓይነ ወግ ቡዳ ራሳቸውን ለመጠበቅ ብለው ነው፡፡ ልብ ካላችሁ አንዳንድ ሴቶች እርግዝናቸው ያምራል፡፡ ከቁመናቸው ጀምሮ እስከ ፅንሱ አቀማመጥ ላያቸው ለዓይን ደስ ይላሉ፡፡
የቡዳ መንፈስ ደግሞ ከዓይን ተነስቶ ወደ ሰው የሚገባ መንፈስ ስለሆነ እርግዝናቸውን በቡዳ ይበላል፡፡ ከዛማ ብዙም ሳይቆዩ አቅለሸለሸኝ፣ አመመኝ፣ ማኅፀኔን ቆረጠኝ ወዘተ በማለት ደም ሊመታቸውና ፅንሱ ሊጨናገፍ ብሎም ሊጠፋ ይችላል፡፡
ስለዚህ እባካችሁ እርጉዝ ስትሆኑ ፅንሱን ሰው ይይልኝ፣ ማርገዜን ምቀኞቼ ይወቁልኝ፣ ዓይናቸው ደም ይልበስ እያላችሁ ስስ ልብስ በመልበስ አትታዩ፡፡ በተለይ የመውለጃ ጊዜያችሁ ሲደርስ ሰው የሚበዛበት ቦታ በመታየት እና በመዝናናት ስም ዞር ዞር ከማለት ታቀቡ፡፡
ቤቢ ሻወር እያላችሁ እርግዝናችሁን በቡዳ አታስበሉ፡፡ ቤቢ ሻወር ብላችሁ እዩልኝ እንዳላችሁ በቡዳ የተበላ፣ ጤና ያጣ ልጅ ወልዳችሁ ልጄን አትዩብኝ፣ ደብቁልኝ እንዳትሉ ተጠንቀቁ፡፡
ወዳጆቼ ከላይ ያየናቸው ርኩሳን መናፍስት፣ በትዳራችን ላይ ጣልቃ በመግባት፣ ካለመግባባት እስከ መለያየት ሊያደርሱን ስለሚችሉ በትዳራችን ውስጥ የሚፈጠሩትን ነገሮች ረጋ ብሎ፣ አስተውሎ ማየት ያስፈልጋል፡፡
በተረፈ ትዳራችሁ በክፉ መናፍስትም ይሁን በሰው ተንኮል ችግር ውስጥ ከገባ፣ የወለድናቸውም ልጆች እክል ከገጠማቸው ንስሐ ገብተን፣ በጸሎት በርትተን በአምልኮት ሕይወት ፊታችንን ወደ እግዚአብሔር ከመለስን ምህረቱን፣ ቸርነቱን ወደ እኛ ይመልሳል፣ መፍትሔም ይሰጠናል፡፡
ቀናችሁን በጸሎት ጀምሩ፣ ማታ በጸሎት እደሩ!
መርጌታ አምደብርሃን ይትባረክ !!!