ዶ/ር ቴድሮስ አድሀኖም ለአፍሪካ ህብረት ስብሰባ አዲስ አበባ እንደሚገኙ ታወቀ
(መሠረት ሚድያ)- የአለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሀኖም ከሁለት ሳምንት በኋላ በአዲስ አበባ በሚጀመረው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ስብሰባ ላይ እንደሚገኙ ታውቋል።
ከስብሰባው አዘጋጆች ለመሠረት ሚድያ የደረሰው መረጃ እንደሚጠቁመው ዶ/ር ቴድሮስ ከበርካታ የአፍሪካ መሪዎች ጋር በመገናኘት እንደ ወባ፣ ቲቢ፣ ኤች አይ ቪ ኤድስ እና መሰል በሽታዎች ዙርያ የተሰሩ ስራዎችን ይገመግማሉ።
ዶ/ር ቴድሮስ የአለም ጤና ድርጅት ሆነው የዛሬ ሰባት አመት ገደማ ሲመረጡ በወቅቱ የነበረው መንግስት ከፍተኛ ድጋፍ አድርጎላቸው የነበረ ቢሆንም የዛሬ አራት አመት የትግራይ ጦርነት መቀስቀሱን ተከትሎ የመንግስት ሚድያዎች እና አንዳንድ የመንግስት ባለስልጣናት ዘመቻ ከፍተውባቸው ነበር። ዶ/ር ቴድሮስም በጦርነቱ ሲደርሱ ስለነበሩ ጤና ነክ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውሶች በተደጋጋሚ ሲፅፉ እና ሲናገሩ ነበር።
ከዛም አልፎ የዛሬ ሁለት አመት ተኩል ገደማ የአለም ጤና ድርጅት ግለሰቡን ለሁለተኛ ግዜ በዳይሬክተር ጀነራልነት ሲመርጥ የኢትዮጵያ ተወካይ በግልፅ ተቃውሞ አሰምተው ነበር።
የአለም ጤና ድርጅት ሀላፊው ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ ይህ ከአምስት አመት ወዲህ የመጀመርያቸው ይሆናል።
በዚህ ጉዟቸው ከኢትዮጵያ የጤና ሚኒስቴር አመራሮች ጋር ተገናኘተው እንደሚመክሩ ቢጠበቅም ከጠ/ሚር አብይ አህመድ ጋር ውይይት ያደርጉ እንደሆን እስካሁን ማረጋገጫ አልተገኘም።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
(መሠረት ሚድያ)- የአለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሀኖም ከሁለት ሳምንት በኋላ በአዲስ አበባ በሚጀመረው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ስብሰባ ላይ እንደሚገኙ ታውቋል።
ከስብሰባው አዘጋጆች ለመሠረት ሚድያ የደረሰው መረጃ እንደሚጠቁመው ዶ/ር ቴድሮስ ከበርካታ የአፍሪካ መሪዎች ጋር በመገናኘት እንደ ወባ፣ ቲቢ፣ ኤች አይ ቪ ኤድስ እና መሰል በሽታዎች ዙርያ የተሰሩ ስራዎችን ይገመግማሉ።
ዶ/ር ቴድሮስ የአለም ጤና ድርጅት ሆነው የዛሬ ሰባት አመት ገደማ ሲመረጡ በወቅቱ የነበረው መንግስት ከፍተኛ ድጋፍ አድርጎላቸው የነበረ ቢሆንም የዛሬ አራት አመት የትግራይ ጦርነት መቀስቀሱን ተከትሎ የመንግስት ሚድያዎች እና አንዳንድ የመንግስት ባለስልጣናት ዘመቻ ከፍተውባቸው ነበር። ዶ/ር ቴድሮስም በጦርነቱ ሲደርሱ ስለነበሩ ጤና ነክ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውሶች በተደጋጋሚ ሲፅፉ እና ሲናገሩ ነበር።
ከዛም አልፎ የዛሬ ሁለት አመት ተኩል ገደማ የአለም ጤና ድርጅት ግለሰቡን ለሁለተኛ ግዜ በዳይሬክተር ጀነራልነት ሲመርጥ የኢትዮጵያ ተወካይ በግልፅ ተቃውሞ አሰምተው ነበር።
የአለም ጤና ድርጅት ሀላፊው ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ ይህ ከአምስት አመት ወዲህ የመጀመርያቸው ይሆናል።
በዚህ ጉዟቸው ከኢትዮጵያ የጤና ሚኒስቴር አመራሮች ጋር ተገናኘተው እንደሚመክሩ ቢጠበቅም ከጠ/ሚር አብይ አህመድ ጋር ውይይት ያደርጉ እንደሆን እስካሁን ማረጋገጫ አልተገኘም።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia