በዱባይ በተደረገው የፖሊስ SWAT ውድድር ላይ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ 101ኛ መውጣቱ ታወቀ
(መሠረት ሚድያ)- ላለፉት ጥቂት ቀናት በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ፣ ዱባይ ከተማ በተካሄደው እና የ103 ሀገራት የSWAT ፖሊስ ቡድን አባላት በተሳተፉበት ውድድር ላይ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ 101ኛ መውጣቱ ታውቋል።
ይህ Special Weapons And Tactics (የልዩ መሳርያዎች እና ታክቲኮች) የቡድን ውድድር ላይ የቻይና B ቡድን በአንደኝነት ሲያጠናቅቅ፣ የካዛክስታኑ ሱንካር ፖሊስ ሁለተኛ እንዲሁም የቻይና C ቡድን ሶስተኛ ሆነው አጠናቀዋል (ሊንክ: https://uaeswatchallenge.com/?page_id=11727)
በ SWAT ውድድሩ ላይ ሲወዳደር የቆየው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ቡድን ከሁለት ቀን በፊት በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርስ በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ስትራቴጂክ አመራሮች አቀባበል ተደርጎለታል።
በአቀባበል ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል፤ እንደ ሀገር ለመጀመሪያ ጊዜ የፖሊስ ተቋም በተባበሩት ዐረብ ኢምሬቶች SWAT ውድድር ላይ መሳተፉ ለሀገራችን ገጽታ ግንባታ ከፍተኛ ጠቀሜታ ከማስገኘቱም ባሻገር ዓለም አቀፍ የፖሊስ ለፖሊስ ግንኙነትን ለማዳበር ፋይዳው የላቀ ነው ብለዋል።
በኢትዮጵያ የፖሊስ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በዚህ ውድድር ላይ መሳተፍ መቻላችን ልምድና ተሞክሮ እንድናገኝ ያስቻለን ነው ሲሉም ጠቁመዋል፡፡
በቀጣይም እ.ኤ.አ 2026 በሚካሄደው ውድድር ላይ አስፈላጊውን ስልጠና በመውሰድ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ በትጋት እንሠራለን ሲሉም ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወደ ስፍራው ሲጓዝ እና ውድድሩን አጠናቆ ወደ ሀገር ሲመለስ በስፋት በመንግስት ሚድያዎች ቢበገብም ያስመዘገበው አነስተኛ ውጤት ግን ለህዝብ አልተገለፀም።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
(መሠረት ሚድያ)- ላለፉት ጥቂት ቀናት በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ፣ ዱባይ ከተማ በተካሄደው እና የ103 ሀገራት የSWAT ፖሊስ ቡድን አባላት በተሳተፉበት ውድድር ላይ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ 101ኛ መውጣቱ ታውቋል።
ይህ Special Weapons And Tactics (የልዩ መሳርያዎች እና ታክቲኮች) የቡድን ውድድር ላይ የቻይና B ቡድን በአንደኝነት ሲያጠናቅቅ፣ የካዛክስታኑ ሱንካር ፖሊስ ሁለተኛ እንዲሁም የቻይና C ቡድን ሶስተኛ ሆነው አጠናቀዋል (ሊንክ: https://uaeswatchallenge.com/?page_id=11727)
በ SWAT ውድድሩ ላይ ሲወዳደር የቆየው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ቡድን ከሁለት ቀን በፊት በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርስ በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ስትራቴጂክ አመራሮች አቀባበል ተደርጎለታል።
በአቀባበል ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል፤ እንደ ሀገር ለመጀመሪያ ጊዜ የፖሊስ ተቋም በተባበሩት ዐረብ ኢምሬቶች SWAT ውድድር ላይ መሳተፉ ለሀገራችን ገጽታ ግንባታ ከፍተኛ ጠቀሜታ ከማስገኘቱም ባሻገር ዓለም አቀፍ የፖሊስ ለፖሊስ ግንኙነትን ለማዳበር ፋይዳው የላቀ ነው ብለዋል።
በኢትዮጵያ የፖሊስ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በዚህ ውድድር ላይ መሳተፍ መቻላችን ልምድና ተሞክሮ እንድናገኝ ያስቻለን ነው ሲሉም ጠቁመዋል፡፡
በቀጣይም እ.ኤ.አ 2026 በሚካሄደው ውድድር ላይ አስፈላጊውን ስልጠና በመውሰድ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ በትጋት እንሠራለን ሲሉም ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወደ ስፍራው ሲጓዝ እና ውድድሩን አጠናቆ ወደ ሀገር ሲመለስ በስፋት በመንግስት ሚድያዎች ቢበገብም ያስመዘገበው አነስተኛ ውጤት ግን ለህዝብ አልተገለፀም።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia