መንግስት ንብረታቸውን ሊወስድ እየተዘጋጀ መሆኑን አቶ ልደቱ አያሌው አስታወቁ
(መሠረት ሚድያ)- ባሳለፍነው ሰኞ ጠዋት ከአሜሪካ ወደ ሀገራቸው ኢትዮጵያ ለመጓዝ በአትላንታ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ቢገኙም እንዳይሳፈሩ የተደረጉት ፖለቲከኛው አቶ ልደቱ አያሌው መንግስት ንብረታቸውን ሊወስድ እየተዘጋጀ መሆኑን አስታወቁ።
ፖለቲከኛው ለበርካታ አለም አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ተቋሟት ዛሬ በፃፉት እና ለመሠረት ሚድያ በቀጥታ ባጋሩት ደብዳቤያቸው ላይ "ጠ/ሚር አብይ አህመድ ወደ ሀገር መመለስ እንደማልችል በአንድ ስብሰባ ላይ በይፋ ተናግረዋል" ብለዋል።
አቶ ልደቱ አክለውም ወደ ሀገር ቤት እንዳይመለሱ የታገዱት በኢትዮጵያ አየር መንገድ ብቻ ሳይሆን በሌሎች ወደ ኢትዮጵያ በሚበሩ አየር መንገዶች ጭምር መሆኑን ጠቁመዋል።
"ይህ ድርጊት የሚያሳየው የኢትዮጵያ መንግስት ሁሉንም ተፃራሪ ድምፆች ለማፈን ቁርጠኛ መሆኑን ነው። እነዚህ ድርጊቶች እየተፈፀሙ ያሉት ካለ ምንም የህግ አግባብ ስለሆነ በግዜው ካልተስተካከለ በርካታ ኢትዮጵያውያን ላይ ጭምር ሊፈፀም ይችላል" በማለት በደብዳቤያቸው ላይ አስፍረዋል።
አቶ ልደቱ ከኢትዮጵያ ውጪ ሌላ ዜግነት እንደሌላቸው አፅንኦት ሰጥተው በደብዳቤያቸው ላይ ያስረዱ ሲሆን የኢትዮጵያ ህገ-መንግስትም ሆነ ሌሎች የሀገሪቱ ህጎች ዜጎች ወደ ሀገራቸው መመለስ እንደማይችሉ የሚገልፅ ድንጋጌ እንደሌላቸው አንስተዋል።
የአቶ ልደቱ ደብዳቤ የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን፣ የአፍሪካ ህብረትን፣ አምነስቲ ኢንተርናሽናልን፣ ሂውማን ራይትስ ዋችን እና የአሜሪካ ኤምባሲን ጨምሮ ለ32 ድርጅቶች የተፃፈ ነው።
"ወደ ሀገሬ መሄድ ማንም ሊከለክለኝ አይችልም፣ ሀገሬ ከሄድኩ በኋላ ግን ማሰር ይችላሉ" የሚሉት ፖለቲከኛው ከአመታት በፊት ለህክምና ከሀገር ሲወጡ መንግስት ከልክሏቸው እንደነበር፣ አሁን ደግሞ ሊመለሱ ሲፈልጉ መከልከሉ እንቆቅልሽ እንደሆነባቸው ባሳለፍነው ሰኞ ለመሠረት ሚድያ ተናግረው ነበር።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
(መሠረት ሚድያ)- ባሳለፍነው ሰኞ ጠዋት ከአሜሪካ ወደ ሀገራቸው ኢትዮጵያ ለመጓዝ በአትላንታ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ቢገኙም እንዳይሳፈሩ የተደረጉት ፖለቲከኛው አቶ ልደቱ አያሌው መንግስት ንብረታቸውን ሊወስድ እየተዘጋጀ መሆኑን አስታወቁ።
ፖለቲከኛው ለበርካታ አለም አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ተቋሟት ዛሬ በፃፉት እና ለመሠረት ሚድያ በቀጥታ ባጋሩት ደብዳቤያቸው ላይ "ጠ/ሚር አብይ አህመድ ወደ ሀገር መመለስ እንደማልችል በአንድ ስብሰባ ላይ በይፋ ተናግረዋል" ብለዋል።
አቶ ልደቱ አክለውም ወደ ሀገር ቤት እንዳይመለሱ የታገዱት በኢትዮጵያ አየር መንገድ ብቻ ሳይሆን በሌሎች ወደ ኢትዮጵያ በሚበሩ አየር መንገዶች ጭምር መሆኑን ጠቁመዋል።
"ይህ ድርጊት የሚያሳየው የኢትዮጵያ መንግስት ሁሉንም ተፃራሪ ድምፆች ለማፈን ቁርጠኛ መሆኑን ነው። እነዚህ ድርጊቶች እየተፈፀሙ ያሉት ካለ ምንም የህግ አግባብ ስለሆነ በግዜው ካልተስተካከለ በርካታ ኢትዮጵያውያን ላይ ጭምር ሊፈፀም ይችላል" በማለት በደብዳቤያቸው ላይ አስፍረዋል።
አቶ ልደቱ ከኢትዮጵያ ውጪ ሌላ ዜግነት እንደሌላቸው አፅንኦት ሰጥተው በደብዳቤያቸው ላይ ያስረዱ ሲሆን የኢትዮጵያ ህገ-መንግስትም ሆነ ሌሎች የሀገሪቱ ህጎች ዜጎች ወደ ሀገራቸው መመለስ እንደማይችሉ የሚገልፅ ድንጋጌ እንደሌላቸው አንስተዋል።
የአቶ ልደቱ ደብዳቤ የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን፣ የአፍሪካ ህብረትን፣ አምነስቲ ኢንተርናሽናልን፣ ሂውማን ራይትስ ዋችን እና የአሜሪካ ኤምባሲን ጨምሮ ለ32 ድርጅቶች የተፃፈ ነው።
"ወደ ሀገሬ መሄድ ማንም ሊከለክለኝ አይችልም፣ ሀገሬ ከሄድኩ በኋላ ግን ማሰር ይችላሉ" የሚሉት ፖለቲከኛው ከአመታት በፊት ለህክምና ከሀገር ሲወጡ መንግስት ከልክሏቸው እንደነበር፣ አሁን ደግሞ ሊመለሱ ሲፈልጉ መከልከሉ እንቆቅልሽ እንደሆነባቸው ባሳለፍነው ሰኞ ለመሠረት ሚድያ ተናግረው ነበር።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia