ሊከተለኝ የሚወድ… መስቀሉን ተሸክሞ ይከተለኝ
የእግዚአብሔር ፍቅር በመስቀል እንደተገለጠ ሁሉ የሰው ልጆችም እርሱን የመውደዳችን መገለጫ መስቀሉን በመሸከም መከተል እንደሆነ በአምላካዊ ቃሉ አስተምሮናል፡፡ ይህም ማለት እንደ ጌታችን ረጅምና ክብደት ያለው ዕፀ መስቀልን በትከሻችን ተሸክመን ቀራንዮ እንድንጓዝ ሳይሆን መከራ መስቀሉ ስለ እኛ ሲል የፈጸመልን መሆኑን በማመን እና ተከታዮቹ በመሆናችን የሚመጣብንን መከራ በመታገሥ መኖር እንደሚገባን ሲያመለክተን ነው፡፡ በዚህም መሠረት “መስቀል መሸከም” የተባለው በዓለም ስንኖር በክርስትና ምክንያት የሚገጥመንን መከራ ነው፡፡ “በዓለም ግን መከራ ትቀበላላችሁ ነገር ግን ጽኑ እኔ ዓለሙን ድል ነስቼዋለሁና” እንዲል /ዮሐ.16÷33/፡፡ በወቅቱ ይህ ቃል የተነገራቸው ቅዱሳን ሐዋርያት መስቀሉን በመሸከም ማለትም ስለ ክርስትና ኑሮ የመጣባቸውን መከራ በመታገሥ እና ድል በመንሳት ኑረዋል ለዚህም ነው፡፡ “መንግሥተ ሰማያት በብዙ መከራ እንገባ ዘንድ ያስፈልገናል” በማለት በቃልም በተግባርም የገለጹት /ሐዋ.14÷22/፡፡ የክርስትና ጉዞ እንደ ቀራንዮ ጉዞ መከራ የበዛበት ነው፡፡ ፈቃደ ሥጋን እየታገሱ ለፈቃደ ነፍስ እየኖሩ ዓለምን፣ ዲያብሎስን እየተዋጉ እስከ ሞት በመጽናት ተጉዘው የክብር አክሊል የሚቀዳጁበት ሕይወት ነውና “እስከ ሞት ድረስም የታመንህ ሁን የሕይወት አክሊልንም እሰጥሀለሁ” ተብሎ እንደተጻፈ /ራእ.2÷10/፡፡
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @Wisecomment_bot ይላኩልን
የእግዚአብሔር ፍቅር በመስቀል እንደተገለጠ ሁሉ የሰው ልጆችም እርሱን የመውደዳችን መገለጫ መስቀሉን በመሸከም መከተል እንደሆነ በአምላካዊ ቃሉ አስተምሮናል፡፡ ይህም ማለት እንደ ጌታችን ረጅምና ክብደት ያለው ዕፀ መስቀልን በትከሻችን ተሸክመን ቀራንዮ እንድንጓዝ ሳይሆን መከራ መስቀሉ ስለ እኛ ሲል የፈጸመልን መሆኑን በማመን እና ተከታዮቹ በመሆናችን የሚመጣብንን መከራ በመታገሥ መኖር እንደሚገባን ሲያመለክተን ነው፡፡ በዚህም መሠረት “መስቀል መሸከም” የተባለው በዓለም ስንኖር በክርስትና ምክንያት የሚገጥመንን መከራ ነው፡፡ “በዓለም ግን መከራ ትቀበላላችሁ ነገር ግን ጽኑ እኔ ዓለሙን ድል ነስቼዋለሁና” እንዲል /ዮሐ.16÷33/፡፡ በወቅቱ ይህ ቃል የተነገራቸው ቅዱሳን ሐዋርያት መስቀሉን በመሸከም ማለትም ስለ ክርስትና ኑሮ የመጣባቸውን መከራ በመታገሥ እና ድል በመንሳት ኑረዋል ለዚህም ነው፡፡ “መንግሥተ ሰማያት በብዙ መከራ እንገባ ዘንድ ያስፈልገናል” በማለት በቃልም በተግባርም የገለጹት /ሐዋ.14÷22/፡፡ የክርስትና ጉዞ እንደ ቀራንዮ ጉዞ መከራ የበዛበት ነው፡፡ ፈቃደ ሥጋን እየታገሱ ለፈቃደ ነፍስ እየኖሩ ዓለምን፣ ዲያብሎስን እየተዋጉ እስከ ሞት በመጽናት ተጉዘው የክብር አክሊል የሚቀዳጁበት ሕይወት ነውና “እስከ ሞት ድረስም የታመንህ ሁን የሕይወት አክሊልንም እሰጥሀለሁ” ተብሎ እንደተጻፈ /ራእ.2÷10/፡፡
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
@wiseholyfathers
አስተያየት ካላቹ በ @Wisecomment_bot ይላኩልን