📚👳‍♂ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት👳‍♂📚


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


ይህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ የሆነውን የህይወት ቃል ጌታ እግዚአብሔር በገለጠልን ፀጋ መጠን የምንካፈልበት ሲሆን!
" ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና፤"ቲቶ ፩÷፲፩

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


🙏ኦርቶዶክሳዊ ዝማሬ🙏 dan repost
‼️‼️‼️‼️‼️‼️‼️‼️‼️
ሁሉም ክርስቲያን ፖስት ያድርገው አሁኑኑ 
እዚህ page ላይ የምትገቡ ሁሉ ይህንን ሳታዮ እንዳታልፉ!!

‼️‼️‼️‼️‼️‼️‼️‼️‼️

በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ግለሰብ በቲክቶክ ስሙ ሳላህ በትክክለኛው ስሙ ቶፊቅ በመባል የሚታወቅ ሲሆን ቪዲዮ ላይ እንዳያችሁት ከሆነ በመጽሐፍ ነው ያለማስረጃ አናወራም የክርስትናን መጽሐፍ እኛ እናውቅላችዃለን በማለት መጽሐፍቶቻችንን እና አስተምህሮታችንን በመዘባበት  ፈጣሪያችንን በመሳደብ ለፈጣሪያችን የማይገባ ከአስተምህሮታችን ውጪ የሆነ አፀያፊ ቃልን በማድረግ ተማሪዎችን የሚያሰለጥኑ ኡስታዞች በፈለግ በመከተል እንግዲ በዚህ መልኩ ለኃልዎተ እግዚአብሔር በማይገባ በማይመጥን አማርኛ ቃል በመሰንጠቅ እና በማጣመም ሲሳለቅ ሲሳደብ የሚያሳይ አሳዛኝ ምስል ነው።

በጣም የማዝነው ከሚመለከታቸው አካላት ዝምታ ብቻ ሳይሆን ህዝቡ በፍቅር አክብሮ ወደ ዝና ማማ ያወጣቸው ግለሰቦች ናቸው።

የሚሰደበው ፈጣሪያችሁ አይደለምን ⁉️

ካለመኖር ወደ መኖር አምጥቶ እድሜ ጤና ሰጥቶ የሰው ፍቅር እና መውደድን ጨምሮ ጨማምሮ በነገራችሁ ሁሉ ያልተለየ አምላካችሁ በአደባባይ መሳለቂ ሲሆን እያያችሁ እንዴትስ ልባችሁ እሺ አለ⁉️

እንዴትስ አእምሮቹ ፈቀደ⁉️

“ከጥፊው በላይ የወዳጄ ዝምታ ልቤን አደማው “ አለ ባለቅኔው።

😭😭😭😭😭😔😔😔😔😔
እፎይ እና ጰልድዮስ እውነት አላቸው

@Efoyewnetalew
@Efoyewnetalew

#ድምፀ_ተዋህዶ
#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ


🙏ኦርቶዶክሳዊ ዝማሬ🙏 dan repost
Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
በጣም አስደንጋጭ መረጃ አስቸኳይ መረጃ ‼️


ይድረስ ለጠቅላይ ቤተ ክህነት ይድረስ ለማህበረ ቅዱሳ ይድረስ ለሰንበት ትምህርት ቤት ማዳረጃ እና መምሪያ።

እስከመቼ ዝምታ ነገሩ ከእቅበት እምነት ሳይሆን በቤተክርስቲያናችን በሀገረ እና በዘር ላይ ያነጣጠረ ጭፍን ጥላቻ ሲሰበክ በአደባባይ እንዴት ዝም ይባላል?

አሁንም እንደዚህ አይነት ዘርን እና ሃይማኖትን ያነጣጠረ ጠብ እና አመጽ ቀስቃሽ አደገኛ የሆነ መልእክት እየተላለፈ አሁን ሁሉም የሚመለከት አካላት ይድረስልን ይህ በማሕበረሰባችን ያለውን ትስስር አደጋ ላይ የሚጥል ጸያፍ እና አስደንጋጭ የሆነ መልእክት ልትቃወሙት ይገባል። በሃይማኖት ሰበብ የጥላቻን እና የህዝብን ሉዐላዊነት አደጋ ላይ የሚጋርጥ መልእክት የምታዮት ሰዎች በሙሉ ይህ የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ በሀገራችነ‍እ ሉዓላዊነት ለዘመናት ተከባብረው ዜጎች የሚኖሩባት ሀገረን አደጋ ላይ የሚጥ አፀያፊ ጽንፈኛ አስተሳሰብነ‍እ ሁሉም የሃይማኖት አባቶች ሁሉም የእምነት ተቋማት እና የህግና የመንግስት አካላት ልታወግዙ እና ልታስቆሙ ይገባል ።

ስለዚህ ይህንን መልእክት የምታዩት ቢያንስ ለ20 ሰው ሼር በማረግ ለመንግስት እና የህግ አካላት ተጨማሪም ሀይማኖቶች ጉባኤ እንድታደርሱልን ስንል እንጠይቃለን !!!

እፎይ እና ጰልድዮስ እውነት አላቸው።
ትክለኛ የቴሌግራም ቻናላቸው ነው ተቀላቀል አንተ ባለማህተብ ክርስቲያን የሆንክ
👇👇👇👇
@Efoyewnetalew
@Efoyewnetalew

#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ


🙏ኦርቶዶክሳዊ ዝማሬ🙏 dan repost
ወንድማችን እፎይ የ63+ ሚሊዮን ኦርቶዶክሳዊያን አደራ ነው ይህ ይሰመርበት !!

ጌታ ኢየሱስ ይጠብቀው ጸልዩለት፣ ብዙኀናችን አብሮነታችንን እናሳየው !!


✝️ለባለ ማህተቦች✝️ሼር ያድርጉ↗️

✨✨✨✨✨✨✨
✝️#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ✝️
✨✨✨✨✨✨✨


🎤✨ድምፀ ተዋህዶ✨🎤 dan repost
🗓ትጾማለህን?
በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

☦️ትጾማለህን❓ እንግዲያውስ በሥራህ አረጋግጥልኝ!
በምን ዓይነት ሥራ ካልከኝ?
☦️ደሃውን ካየህ እዘንለት (ቸርነትን አድርግለት)!
☦️የተጣላኸውን ካየህ ታረቀው!
☦️ጓደኛህ ክብርን ሲያገኝ ካየህ አትቅናበት!
☦️መልከኛ ሴት ካየህ እለፋት!
☦️አፍህ ብቻ ከምግብ አይከልከል፤ አይንህም፣ ጆሮህም፣ እግርህም፣ እጆችህም፣ ሁሉም  የሰውነትህ ክፍሎች ይጹሙ።

እጆችህ ከንጥቂያና ስግብግብነት (ንፉግነት) ይጹሙ። እግሮችህ የማይገቡ ትእይንቶችን ለመመልከት ከመንደርደር ይጹሙ። አይኖችህ ውብ መልኮች ላይ ያልተገቡ እይታዎችን መቼም መች ከማሳረፍ መከልከልን ይማሩ እና ቁንጅና ላይ ከመጠመድ ይጹሙ።

ማየት ለዐይን ምግብ ስለሆነ ያልተገባ እና የተከለከለን እይታ ካደረግህ ጾምህን ያፈርሰዋል፣ የነፍስህንም ሙሉ ደህንነት ያነዋውጣል፤ ነገር ግን የተገባና ጥንቁቅ ከሆነ ጾምህን ያስጌጣታል።

የተከለከለውን በዓይን እየነካህ ነገር ግን በጾም ምክንያት ከማያረክስ ምግብ መጾሙ ከንቱ ከሆኑ ነገሮች መካከል ይቆጠራል። ሥጋን አትበላም አይደል? ስለዚህ በዐይኖችህ አማካኝነት ፍትወትን አትመገብ። ጆሮም ይጹም።

የጆሮ ጾም ክፉ ወሬን እና ሐሜትን አለመቀበልን ያካትታል። “ሐሰተኛ ወሬ አትቀበል” እንዲል። (ዘጸ. 23፥1)   አፍም እንዲሁ ከመጥፎ እና ከጥላቻ ንግግሮች ይጹም።  ከአዕዋፋትና አሳዎች ብንከለከል ነገር ግን ወንድማችንን ብንበላው ምን ይጠቅመናል? ክፉ ተናጋሪ የወንድሙን ሥጋ ይበላል የባልንጀራውንም ሰውነት ይነክሳልና።


✨✨✨✨✨✨
✝️#ድምፀ_ተዋህዶ✝️
✨✨✨✨✨✨


🙏ኦርቶዶክሳዊ ዝማሬ🙏 dan repost
🗓☦️​​ዘወረደ

የመጀመሪያ የዐቢይ ጾም መግቢያ እሁድ ዘወረደ ይባላል ደግሞም ጾመ ሕርቃል ይባላል፡፡ «ዘወረደ» ማለት «የወረደ» ማለት ነው፡፡ አምላክ ሰው ሆነ፤ ሰው አምላክ ሆነ ማለት ነው። ይህም ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ለማዳንና ፍቅሩን ሊገልጽልን ከሰማያት መውረዱን ከድንግል ማርያም የእኛን ሥጋ መዋሐዱን የሚያዘክር፤ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ከቅድስት ድንግል ማርያም መወለዱን የሚያመላክት፣ የሚታወስበት፣ የሚነገርበት የዐቢይ ጾም አንደኛው ሳምንት ነው፡፡ ዮሐ.3-13

እግዚአብሔር አምላክ ለአዳም በገባዉ ቃልኪዳን መሰረት “ የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ልጁን ላከ”ገላ 4፥4 እንዳለ ሐዋርያዉ ቅዱስ ጳዉሎስ ፡ የጠፋዉን አዳም ፍለጋ ከአባቱ እሪና ሳይጎድል ሳይለይ ከሰማይ መዉረዱን የምናዘክርበት በዓል ነዉ።

ይህ ጾም የጾም መግቢያ የመጀመሪያ ሳምንት የምንጾመው ጾም ሲሆን ሕርቃል የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ለአዳም “ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ በመልዕልተ መስቀል ተሰቅየ አድንኃለሁ” ብሎ ለአዳም ቃል ገባለት ፡፡ ዘፍ. ፫ ፥ ፲፭ ይህ ኪዳነ አዳም ይባላል የቃል ኪዳን ሁሉ መሠረት ነው፡፡


ሁለቱን ኪዳናት (ብሉይ ወሐዲስ) በፅኑዕ ተስፋ ያስተሳሰረ የረጅም ዘመናት የድኅነት ሰንሰለት ነው ፡፡ ዘወረደ እርቀ አዳም ፤ ተስፋ አበው ፤ ትንቢተ ነቢያት ፤ ሱባኤ ካህናት መፈፀሙ ፤ ኪዳነ አዳም መሲህ መወለዱ የሚነገርበት የፍቅር አዋጅ ነው። እኛም በዚህ በዐብይ ፆም የለመነውና የጠየቅነው ነገር ሁሉ ከኃጢአት በስተቀር እንዲከናወንልን ፆምን ገንዘባችን እናድርግ።

ጾም ጸሎታችን የቅዱሳን አምላክ እግዚአብሔር ይቀበልልን አሜን

✝️ለባለ ማህተቦች✝️ሼር ያድርጉ↗️

✨✨✨✨✨✨✨
✝️#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ✝️
✝️#ድምፀ_ተዋህዶ ✝️
✨✨✨✨✨✨✨


🙏ኦርቶዶክሳዊ ዝማሬ🙏 dan repost
🗓 ነገ ማለትም
ዕለት:- ረቡዕ
#ቀን:- ጥር ፲፬ ፳፻፲፯ ዓ.ም
በቅድስት ቤተክርስቲያናችን


አቡነ አረጋዊ (አመታዊ)
አባ ጳኩሚስ ፣ ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ፣ አቡነ ተስፋ ጽዮን ፣ ሰማዕቱ አብሮኮሮስ ፣ አባ ዘሚካኤል ፣ ሙሴ ጸሊም


አክብረን እና አስበን እንውላለን

እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )


✝️ለባለ ማህተቦች✝️ሼር ያድርጉ↗️

✨✨✨✨✨✨✨
✝️#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ✝️
✨✨✨✨✨✨✨


ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ dan repost
+ ንስሐ ግቡ +

የጌታቻን የኢየሱስ ክርስቶስ መጠመቅ አሰቀድሞ በዮሐንስ ለሀጥያት ስርየት ማጥመቅ መንገድ ጠራጊነት የተጀመረ ነው እርሱም እኔስ ለጠጅ ፡ ቢረሌን ፡ ለልብስ ፡ ገላን ፡ እንዲያጥቡለት ፡ ለሱ ፡ ጥምቀት በሚያበቃ ጥምቀት አጠምቃቹሀለው ይል ነበር እንዲሁም እርሱ የሚያጠምቀው ጥምቀት ክርስቶስ ከሚያጠምቀው ጥምቀት ልዩ መሆኑን ሲገልፅ "በመንፈስ : ቅዱስ : እሳትነት" ክፍውን : ሕሊና : ከበጎው : ሕሊና የሚለይበት ስልጣነ ክህነት ገንዘቡ የሚሆንለት በማለት ይገልፃል ። ዮሐንስ ትንቢት የተነገረለት ያለነቀፌታ ይኖሩ ከነበሩ በእግዚአብሔር ፈት ጻድቃን ከነበሩ ከካህኑ ዘካርያስ እና ከኤልሳቤጥ የተወለደ ነው ። በሉቃ 8-11"

***
በእግዚአብሔር ፈት በቤተ መቅደስ ገብቶ የማጠን ተራ በመዓት አንድ ጊዜ የደረሰበት ካህኑ ዘካርያስ በመሰዊያው ቀኝ የእግዚአብሔር መልአክ ተገልጦለት ታየው ። ይህም በዓመት አንዴ ሳይሆን አንድ ጊዜ በፈሰሰ ደሙ አለምን የሚያድን አምላክ ሊወለድ መሆኑን ሲነግረው ነው አንድም ካለመታዘዝ ወደ መታዘዝ የሚመልስ ከጣኦት አምላኪነት ወደ እግዚአብሔር አምላኪነት የሚመልስ ልጅ ትወልዳለህ ሲለው ነው በተጨመሪም በቀኝ እጁ አምላክን የሚያጠምቅ ልጅ ትወልዳለህ እያለ መንገሩ ነው ("ጸያሔ ፍኖት" ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ ) ።

ለዚህም ነበር በሰፈው ፈት ፃድቃን መስለው ይታዩ ለነበሩት በእግዚአብሔር ፈት ፅድቃቸው ከተመሰከረላቸው ቤተሰብ የተገኘው ዮሐንስ እርሱ በጌታ ፈት ታላቅ የሆነ ሉቃ 1፡15 በህሊና የተሰወረውን ክፍ ግብራቸውን ሳይፈራ እግዚአብሔር ገልጦለት ይገስፃቸው ነበር ፈሪሳውያንን "መልካም ፍሬ የማያፈራ ይጣላል " ማቴ 3-10 እያለ የነብያት ልጆች መሆናቸው ብቻ ንስሃ ካለመግባታቸው የሚመጣባቸውን ቅጣት እንደማያስመልጣቸው ክቡዳነ አእምሮ ለሆኑት ለእነርሱ "ንስሀ ግቡ" እያለ ያስተምራቸው ነበር ። ምንመካባቸው ብዙ የተከማቹ ሀብት ይዘን ሊሆን ይቻላል በዘመንድ ብዛት የእከሌ ዘመድ የእከሌ ዘር እያልን ምንመፃደቅባቸው በሰው ፈት ከሁሉ የተሻልን ለመምሰል የምናቀርባቸው ቁሶች ከመቃብር አይሻገሩም ያለን ግዙፍ ቤት በሁሉ ፈት ለመመካት ይዘነው አንዞርም አንድ ቦታ እንደተተከለ ይቀራል የሰማይ መንግስት እንወርስ ዘንድ ዮሐንስ ዛሬም "እንግዲህ ለንስሐ የሚያበቃቹሁን በጎ ስራ ስሩ" ይለናል " ማቴ 3-8 ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ ይለናል " ጸጋስ ይሉሃል የኃጥያት ስርያት ማግኘት "

እንኳን አደረሳቹሁ ። !!!

(ዲያቆን ፍፁም ከበደ)

#ኦርቶዶክሳዊ_አእምሮ


ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ dan repost
#እንኳን_አደረሳቹ #ታኅሳስ_19

"እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ" (ሉቃ 1:19) እና ስለ ነቢዩ ሙሴ "... ስለ ሕዝቡ ባይቆም ኖሮ ሊያጠፋቸው ተናገረ።" (መዝ 125) ... ሁለቱን አነጋገሮች እናስተውላቸው። አንዱ በዚህች ምድር የተደረገ "ስለ ሕዝብ መቆም" (ምልጃ) ነው። ሌላው ደግሞ በመንፈሳዊው ዓለም በቅዱሳን መላእክት የሚደረግ "መቆም" (ምልጃ) ነው። አንዱ በእስንፋሰ እግዚአብሔር ዘመድ በሆነ (በሰው) የተደረገ ነው።... ሌላው ደግሞ በፍቅር እና በመንፈሳዊ ኅብረት አዛማጅነት የሚደረግ ነው።... ሰው ከክርስቶስ በተቀበላት ቤተ ክርስቲያን እና ቤተ ክርስቲያንነት በእርሱም ትክክለኛ እውነታ (Reality) ቅዱሳን ምልጃን ያደርጋሉ። ... በሌሎች ሰዎች የሕይወትና ሞትን መንፈሳዊ ትርጉም ባላገናዘበ፣ ክርስቶስ መጥቶ የ3 ዓመት ትምህርትን "በግል ለግል ያስተማረ" ይመስል ቤተ ክርስቲያንን "ግል" (individual) ብቻ ባደረገው አስተሳሰብ፣ የእውነት ውሏን በትሕትና ከመፈለግ ከማግኘትም ይልቅ በቲፎዞነት፣ "ከእኔ (ከእኛ) በላይ አዋቂ" በሚል የኅሊና ጥመት ባደከመው ዘንድ ቅዱሳን አይማልዱም። ሰው "ጌታ ይበቃኛል" በማለት ራሱን ያታልላል እንጂ "እኔ ለራሴ እበቃዋለሁ" እያለ መሆኑን ከመረዳትም የዘገየ ነው።

የመልአኩን ረድኤት አይለይብን። በቅዱሳን ጸሎት ይማረን።

(ዲያቆን ሚኪያስ አስረስ)

#ኦርቶዶክሳዊ_አእምሮ


🙏ኦርቶዶክሳዊ ዝማሬ🙏 dan repost
🗓🌴
ከአንድ የሾላ ዛፍ ሥር ስትቃርም የነበረችን አይጥ ከነነፍሷ ለመያዝ ከወደሰማይ የነበረው አሞራ ቁልቁል ተምዘግዝጎ ይወርዳል። ሙከራው ለጥቂት በሚባል ሁኔታ ተሳክቶ የአይጧን ጭራ ይይዛል።

: አካሏ ግን ከዛፋ ሥር ካለ ጉድጓድ ገብቶ በልቀቀኝ ዐይነት መታገል ጀምራለች ጉልበቷን ያልተማመነችው አይጥ አሞራውን ለማጃጃል ጥበብ የተሟላ ንግግሯን ተጠቀመች።

: በዚህ መሰረት "አያ አሞራ! የእኔን ጭራ የያዝክ መስሎህ ከሾላው ሥር ጋር ስትታገል መንቁርህ እንዳይሰበር። ይልቅስ የሾላውን ሥር ልቀቅ አትልፉ"አለችው።

:  ቂላቂሉ አሞራም የያዛትን የአይጥ ጭራ ለቀቀ ይባላል

🦅🦅🦅🦅🦅🦅🦅🦅🦅🦅🦅
🇺🇿🇺🇿🇺🇿🇺🇿🇺🇿🇺🇿🇺🇿🇺🇿🇺🇿
እኛ ክርስቲያኖች ብልህ ልንሆን ይገባል ጠላት ዲያቢሎስ ሊያጠቃን ሲያደባ የአባቶችን ጥበብ በመጠቀም ልናመልጥ ይገባናል
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
የጥበብ አምላክ እግዚአብሔር ማስተዋልና ጥበቡን ያድለን


ለባለ✝️ ማህተቦች ሼር ያድርጉ⁉️
📣📣📣📣📣📣📣
#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ
📣📣📣📣📣📣📣


#ማንም የለኝም ማንም ስለኔ ግድ አይሰጠውም ለምን እንላለን ?

#ከሰው በላይ የሚገዝፈውና የሚበልጠው ስለእኛ የሚያስበው አምላካችንን ለምን እንዘነጋዋለን?

#ስለምን ሲቸግረንና ስንበደል ብቻ ፈጣሪን እናስታውሳለን?

#በተድላም በሃዘንም ጊዜና ቦታ ሳይመርጥ የሚያግዘንና የሚረዳን እርሱ እያለ ስለምን በአላፊ ጠፊ እንታለላለን

#በተሰጠን ነገር አመስንነን ሳንጨርስ ለምን የሩቁን እናልማለን?

^#ለምን#




🎤✨ድምፀ ተዋህዶ✨🎤 dan repost
የቀድሞው ዘማሪ ሐዋዝ ተገኝ ወደ ቀደመው የአባቱ ቤት ወደሆነችው ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት መቅደስ ተመልሷል
***

በተ*ዶሶ እንቅስቃሴ ላይ የነበረው የቀድሞ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ዘማሪ የነበረው ሐዋዝ ተገኝ

ቀድሞ ያገለግልባት ወደነበረችው ቅድስት እና ንጽሕት ወደሆነችው ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ መቅደስ በንሰኃ ጥምቀት ተመልሷል።

እግዚአብሔር ይመስገን !!!

#ድምፀ_ተዋህዶ


🎤✨ድምፀ ተዋህዶ✨🎤 dan repost
+++ድንቅ ልዩነት ተመልከቱ+++

በዓለም ለመጀመሪያ ጊዜ ፈርዲናንድ ማጄላን ዓለምን በመርከብ ዞረ።

👉ሐዋርያቱ ደግሞ መርከባቸውን ጥለው ዓለምን ዞሩ!

ዛሬ ይዘንባል እያሉ ትንቢት የሚተነብዩ ሜትሮሎጂስቶች ሞልተዋል።

👉እንደ ኤልያስ ዝናብ እንዳይዘንብ ሰማይን የዘጋ ዳግመኛም ዝናብን ያዘነበ ከቶ የለም።

በላብራቶሪው ተመራምሮ ህሙማንን የፈወሰ ሞልቷል።

👉እንደ ጴጥሮስ ጥላው ድውይ የፈወሰ ከቶ አላየሁም።

በዘፈኑ አጋንንትን የጠራ እንደ ማይክል ጃክሰን ሞልቷል።

👉እንደ ዳዊት በበገና መዝሙሩ አጋንንትን ያስወጣ እስከ ዛሬ አልተገኘም።

ከረቫትና ሱፉን ለብሰን የምንጎራደድ ሞልተናል።

👉የልብሱ ቁጨት አጋንንት ያስወጣ እንደ ጳውሎስ ከቶ አልተገኘም።

የግብጽ ነገሥታት አጽማቸው በክብር ይቀመጣል።

👉ዐጥንቱ ሙት ያስነሳ እንደ ኤልሳዕ ከቶ አላየንም።

በአሜሪካ የነገሥታትን ምሥጢር የሚሰልሉ ድርጅቶች ሞልተዋል።

👉እንደ ኤልሳዕ በእስራኤል ሆኖ በሶሪያ ቤተመንግሥት የሚደረገውን ምሥጢር ያወቀ አልተገኘም።

ለመጀመሪያ ጊዜ ጨረቃን በእግሩ የረገጠ ዩሪ ጋጋሪ ዛሬ ብዙዎቹ አድርገውታል።

👉እንደ ኢያሱ ፀሐይን ያቆመ ከቶ አልተገኘም።

በነገራችን ላይ በተፈጥሮ ሕግ መሰረት ፀሐይ በመሃል ቆማ መሬት ዙሪያውን ትዞራለች። በፀሐይ ፊት ያለው የመሬት ክፍል ቀን ሲሆን ሌላኛው ጎን ደግሞ ማታ ይሆናል።

እነ ኢያሱ በሚዋጉበት ጊዜ መሬት ከፀሐይ ፊቷን አዙራ ቀኑ ሊጨልም ነበር።

👉ኢያሱ ግን መሬት እንዳትዞር አደረጋት! ፀሐይን በገባኦን አቆመ ተባለ! መጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ

ሕዝቡም ጠላቶቻቸውን እስኪበቀሉ ድረስ ፀሐይ ቆመ፥ ጨረቃም ዘገየ። ይህስ በያሻር መጽሐፍ የተጻፈ አይደለምን? ፀሐይም በሰማይ መካከል ዘገየ፥ አንድ ቀንም ሙሉ ያህል ለመግባት አልቸኰለም።

👉 እግዚአብሔር ለእስራኤል ይዋጋ ነበርና ((እግዚአብሔር የሰውን ቃል የሰማበት እንደዚያ ያለ ቀን ከዚያም በፊት ከዚያም በኋላ አልነበረም።))
የዓለም መሪዎች ከአስር በላይ ቋንቋ መናገራቸውን እንጃ፤

👉ሐዋርያቱ ግን 72 ቋንቋ ተገለጠላቸው።

ኃያላን ነገሥታት ድውይ እንኳን መፈወስ አይችሉም።

👉ቅዱሳኑ ግን የ70 የ80 ዘመን ሬሳ አስነሱ።

👉ጠቢባን ነን የሚሉ ጸሐፍት ፈሪሳዊያንን ምላሽ ያሳጣቸው ዘንድ ጥበብ ያልነበራቸውን ዓሳ ወጋሪ የነበሩ ሐዋርያትን መረጠ።

ኃያላን ነገሥታት የመሰሉ መሪ ዳዊትን የመሰሉ ነገሥታትን የወለዱ የከበሩ እናቶች ሞልተዋል።

👉የነገሥታትን ንጉሥ ክርስቶስን የወለደች እናት ግን አንድ ብቻ ናት።

ይህችውም ከሴቶች መካከል ተለይታ የተባረከችው ድንግሊቱ 👉 ማርያም ናት 👈

           
ስብሐት ለእግዚአብሔር!

#ድምፀ_ተዋህዶ

https://t.me/dmtse_tewaedo


ኦርቶዶክሳዊ አእምሮ dan repost
ጾመ ነብያት ነገ እሑድ ኅዳር 15 ይገባል ።

ነቢያት ጌታ "ይወርዳል ይወለዳል" ብለው የተናገሩት ትንቢት እንዲፈጸም ተመኝተው ጾሙ ጸለዩ:: እኛ ስለምን እንጾማለን? ክርስቶስ ተወልዶ ፣ ተጠምቆ ፣ አስተምሮ ፣ ተሰቅሎ ፣ ሞቶ ፣ ተነሥቶ ፣ ዐርጎ ፣ በአባቱ ቀኝ አይደለምን? አሁን ለምን እንጾማለን? ብለን እናስባለን::

ጌታ በእኔና አንተ ልብ ውስጥ እውነት ተወልዶአልን? እውነት የእኛ ልብ እንደ ቤተልሔም ግርግም ለክርስቶስ ማደሪያ ሆኖአል? ማደሪያ አሳጥተን ከእናቱ ጋር አልመለስነውም?

የጥምቀቱ ትሕትና በእኛ ልብ መቼ ደረሰ? የስቅለቱ ሕማም መች በእኛ ሕሊና ተጻፈ? የትንሣኤው ተስፋ የዕርገቱ ልዕልና በእኛ ልቡና መቼ ዐረፈ?

ስለዚህ ነቢያት "ውረድ ተወለድ" ብለው የጾሙትን ጾም እንጾማለን:: ጌታ ሆይ በእኔ ሕይወትም ውስጥ ውረድ ተወለድ የእኔን ሰውነት ማደሪያህ አድርገው:: ሕዋሳቶቼ ከኃጢአት አርፈው እንደ ቤተልሔም ግርግም ማደሪያህ ይሁኑ::

(ዲያቆን ኄኖክ ኃይሌ )

#ኦርቶዶክሳዊ_አእምሮ


🎤✨ድምፀ ተዋህዶ✨🎤 dan repost
ጾም በእግዚአብሔር ታዟል፤ተፈቅዷልም ።
++++++++++++++++++++++++++
ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጾምን እንድንጾም ባርኮ የሰጠን እሱ ነው ።ለዚህም ማረጋገጫ ፦
"ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፦ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን? ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል፥ በዚያ ጊዜም ይጦማሉ።"
ማቴ 9:15
በዚህ መሰረት ፦
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የራሷ የሆነ የጾም ህግና ስርዓት አላት ።
"ነገር ግን ሁሉ በአግባብና በሥርዓት ይሁን ።"እንዲል
1ኛ ቆሮ 14፥40
በቤተክርስቲያናችን ህግና ሥርዓት ተሰርቶላቸው
ከሚጾሙ 7 የአዋጅ አጽዋማት መካከል አንዱ ጾመ ነብያት ይባላል ።የጾሙ ጊዜ ከህዳር 15-እስከ ጌታ ልደት ታህሳስ 28 ድረስ ያለው ነው ።ይህን ጾም የምንጾመው ነቢያት በየዘመናቸው ስለክርስቶስ መምጣት ንጽህት ከምትሆን ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም መወለዱን በናፍቆት ይጾሙና ይጸልዩ ስለነበር የእነርሱን አርአያ ተከትለን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ልደት ከማክበራችን ቀደም ብለን ይህን ጾም እንድንጾም በሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ሥርዓት ተሰርቷል። (ፍት.መ.ን.አንቀጽ 15)
ስለሆነም እኛም ክርስቲያኖች ይህን ተከትለን ብልቶቻችንን ሁሉ(አይን ይጹም ፤እጅ ይጹም፤ እግር ይጹም ፤አንደበት ይጹመ...እንዳለ ቅዱስ ያሬድ) ከኃጢአት ጠብቀን፤እግዚአብሔርን ከማያስደስቱ ማናቸውም ነገሮች ራሳችንን አርቀንና ፤በወንድሞቻችን በማናቸውም ላይ ቂም በቀልን በማስወገድ ይቅርም በመባባል ፤ጸሎትን ስግደትን ምጽዋትንም በመጨመር በንጹህ ልቦና መጾም ይገባናል።ይህን ካደረግን ዘወትር የሚዋጉንና የሚፈታተኑን የአጋንንት ሰራዊት በሙሉ ይደመሰሳሉ፤ኃይላቸውም ይደክማል ።ከእግዚአብሔር ከአምላካችን ፍቅርን ሰላምና በረከትንም እንቀበላለን ።
"የጌታ ቃል የታመነ ነውና።"ቲቶ 3:8
".....ይህ ዓይነት ግን ከጸሎትና ከጦም በቀር አይወጣም አላቸው።"
ማቴ 17:21

#ድምፀ_ተዋህዶ

        📹📹📹📹
   ✨ፊላታዎስ ሚዲያ✨
               👇👇
https://youtu.be/PYhgHxupzLI?si=pQaqogjyj_DUcNXW


🎤✨ድምፀ ተዋህዶ✨🎤 dan repost
በሶሪያ ኦርቶዶክስ  ያዕቆባዊት ቤተክርስቲያን የሕንድ ሜትሮፖሊታን የነበሩት ብፁዕ አቡነ ሞር ባስልዮስ ቶማስ ቀዳማዊ ከዚህ ዓለም ድካም ዐረፉ

  ብፁዕ አቡነ ሞር ባስልዮስ ቶማስ ቀዳማዊ እ.ኤ.አ ሐምሌ 22 ቀን 1929 ዓ.ም ቡቸንክሩዝ በተባለ የሕንድ ግዛት የተወለዱ ሲሆን እ.ኤ.አ ከሐምሌ 26 ቀን 2002 ዓ.ም ጀምሮ በሶርያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሥር የምትተዳደረውን የሕንድ ቤተ ክርስቲያን ለበርካታ ዓመታት በሊቀ ጵጵስና መርተዋል።

ብፁዕነታቸው በዕድሜና በሕመም ምክንያት ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ዕረፍት በማድረግ ሕክምናቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆን በዛሬው ዕለት አመሻሽ ላይ በሕንድ ኮቺ በተወለዱ በ95 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፈዋል።

በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ሞር አግናጢዮስ ኤፍሬም ዳግማዊ፣ ለሶርያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፣ ለመላው የቤተ ክርስቲያን አባላት፣ ቀሳውስትና ምእመናን በሙሉ መጽናናትን እንመኛለን። 

የብፁዕነታቸው በረከት አይለየን !!!

© ተሚማ

#ድምፀ_ተዋህዶ

https://t.me/dmtse_tewaedo


🎤✨ድምፀ ተዋህዶ✨🎤 dan repost
መምህራችን መምህር ኤርሚያስ ታሟል።
አንድ ሰላም ለኪ ድገሙለት እግዚአብሔር በጤና ይመልሰው።

ሰላም ለኪ
ሰላም ለኪ፤ እንዘ ንሰግድ ንብለኪ ፤ ማርያም እምነ ናስተበቊዐኪ ፤ እምአርዌ ነዓዊ ተማሕፀነ ብኪ ፤ በእንተ ሐና እምኪ ፤ ወኢያቄም አቡኪ ፤ ማኅበረነ ዮም ድንግል ባርኪ ።

ጸሎተ እግዝእትነ ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ : -
ታዐብዮ ነፍስየ ለእግዚአብሔር ፤ ወትትሐሠይ መንፈስየ ፤ በአምላኪየ ወመድኃኒየ ፤ እስመ ርእየ ሕማማ ለአመቱ ፤ ናሁ እምይእዜሰ ያስተበፅዑኒ ኵሉ ትውልድ ፤ እስመ ገብረ ሊተ : ኃይለ ዐቢያተ ፤ ወቅዱስ ስሙ ፤ ወሣህሉኒ : ለትውልደ ትውልድ ፤ ለእለ ይፈርህዎ ፤ ወገብረ ኃይለ በመዝራዕቱ ፤ ወዘረዎሙ ለእለ የዐብዩ ኅሊና ልቦሙ ፤ ወነሠቶሙ ለኃያላን እመናብርቲሆሙ ፤ አዕበዮሙ ለትሑታን ፤ ወአጽገቦሙ እምበረከቱ ለርኁባን ፤  ወፈነዎሙ ዕራቆሙ ለብዑላን ፤ ወተወክፎ ለእስራኤል ቊልዔሁ ፤ ወተዘከረ ሣህሎ ፤ ዘይቤሎሙ ፤ ለአበዊነ : ለአብርሃም ፤ ወለዘርዑ እስከ ለዓለም ፤ አሜን ።

አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ ትምጻእ መንግሥትከ። ወይኩን ፈቃድከ በከመ በሰማይ ከማሁ በምድር ሲሳየነ ዘለለ ዕለትነ ሀበነ ዮም። ኅድግ ለነ አበሳነ ወጌጋየነ ከመ ንህነኒ ንኅድግ ለዘአበሰ ለነ። ኢታብአነ እግዚኦ ውስተ መንሱት። አላ አድኅነነ ወባልሓነ እምኲሉ እኩይ እስመ ዚኣከ ይእቲ መንግሥት ኃይል ወስብሐት ለዓለመ ዓለም።

በሰላመ ቅዱስ ገብርኤል መልአክ ኦ እግዝእትየ ማርያም ሰላም ለኪ ድንግል በኅሊናኪ ወድንግል በሥጋኪ እመ እግዚአብሔር ጸባዖት ሰለም ለኪ ቡርክት አንቲ እም አንስት ወቡሩክ ፍሬ ከርሥኪ ተፈስሒ ፍስሕት ኦ ምልዕተ ጸጋ  እግዚአብሔር ምስሌኪ ሰአሊ ወጸልዪ  ምሕረተ ኀበ ፍቁር ወልድኪ ኢየሱስ ክርስቶስ ከመ ይሥረይ ለነ ኃጣውኢነ።
ምህረቱን ይላክሎት መምህር


🎤✨ድምፀ ተዋህዶ✨🎤 dan repost
የ ሀዋሳ ዩንቨርሲቲ 3ኛ አመት የAccounting ተማሪ
የሆነችው እህታችን ሀይማኖት ደግፌ ባደረባት ህመም ምክንያት ትምህርቷን መከታተል አልቻለችም ህመሟም የጡንቻካንሰር አይነት ሲሆን በህክምና አጠራሩ Rhabdomiosarcoma ሲሆን ለዚህም በሰርጅሪ ህክምና ተድርጎላት አሁን የ chemotherapy ህክምና እየወሰደች ትገኛለች ቀጥሎም የ Radiotherapy ህክምና ያስፈልግታል ለዚህም ደግሞ የሚያስፈልገው ገንዘብ ሲሰላ ከ 100,000 ብር በላይ ድረስ ያስፈልጋታል ለዚህም እሷም ሆነ ቤታሰቦቹዋ የማሳከም አቅም ስለሌላቸው እናንተ
ወገኖቻችን ወገናዊ እጃችሁን እንድትዘረጉልን ስንል በትህትና እንጠይቃለን።
እባካችሁ እህታችንን በአቅማችን በመርዳት ወደ ቀድሞ ጤንነቷ ተመልሳ ትምህርቷን እንድትከታተል እንድትተባበሩን እንጠይቃለን።


Haymanot Degife Bosen 1000191370922

በስልክም ማነጋገር ለምትፈልጉ 0986252118


"እንዲሁ እየደከማችሁ ድውዮችን ልትረዱና እርሱ ራሱ፡ ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው እንዳለ የጌታን የኢየሱስን ቃል ልታስቡ ይገባችሁ ዘንድ በሁሉ አሳየኋችሁ።" ሐዋ 20:35




🎤✨ድምፀ ተዋህዶ✨🎤 dan repost
እንኳን ለጻድቁ አባታችን ለአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደርሳቹ❗️

ጥቅምት 5-ኑሮአቸው እንደሰው ያይደለ በምድረ በዳ እንደመላእክት የኖሩትና በዝቋላ ተራራ ባለው ባሕር ውስጥ 100 ዓመት ተዘቅዝቀው ለኢትዮጵያ ሰዎች ምሕረትን የለመኑት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ታላቅ ቃልኪዳን የተቀበሉበት ዕለት ነው፡፡ 

አባታችን አራት ሺህ እልፍ እየሰገዱ፣ 300 ጊዜ የቀኝ 300 ጊዜ ደግሞ የግራ ፊታቸውን በድንጋይ እየመቱ፣ መዝሙረ ዳዊትን እየደገሙ፣ 15ቱን መኅልየ ነቢያት፣ መኅልየ ሰለምንንና ውዳሴ ማርያም እየጸለዩ ለኃጥአን ምሕረትን ሲለምኑ ዕንባቸው እንደ ውኃ ይፈስ ነበር፡፡ ጌታችንም ‹‹በተወለድሁባት፣ በተጠመቅሁባትና ከሞት በተነሣሁባት ዕለት እልፍ እልፍ ነፍሳትን እምርልሃለሁ›› የሚል ቃል ኪዳን ሰጣቸዉ

አምላካችን በቃል ኪዳናቸው ይማረን


✝️#ድምፀ_ተዋህዶ ✝️


🎤✨ድምፀ ተዋህዶ✨🎤 dan repost
“አሁን ባለን የአስተዳደር ክፍተቶችና በውስጣችን ያሉ ግልጽነት የጎደላቸው አሠራሮች ለአገልግሎታችን እንቅፋት እየሆኑብን ነው”ሲሉ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ገለጹ፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት 43ኛው ዓለም አቀፍ መደበኛ ጉባኤ መክፈቻ ላይ ለተገኙ ተሳታፊዎች መልእክት አስተላልፈዋል።

ቅዱስነታቸው በመልእክታቸው አሁን ባለን የአስተዳደር ክፍተቶችና በውስጣችን ያሉ ግልጽነት የጎደላቸው አሠራሮች ለአገልግሎታችን እንቅፋት እየሆኑብን ነው። በዚህ ጉባኤ በቤተ ክርስቲያናችን የሚታየውን  ችግር ለመፍታት በጥናት ላይ የተመሠረተ መፍትሔ ማምጣት ይገባል ሲሉ አፅዕኖት ሰጥተዋል፡፡

ቅዱስነታቸው ጨምረው እንደገለጹት ቅዱስ ሲኖዶስ ተግባራዊ እንዲሆን የወሰነውን የቤተ ክርስቲያን የ10 ዓመት መሪ ዕቅድ ውጤታማ ለማድረግ ሁላችንም በትብብር መሥራት ይገባናል ብለዋል።

በዛሬው ዕለት የተጀመረው 43ኛው አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባኤ ከሀገር ውስጥ እና ውጪ ከሚገኙ አህጉረ ስብከቶች፣ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አድባራት እና ገዳማት እንዲሁም ከተለያዩ መንፈሳዊ ማኅበራት የተወከሉ ተሳታፊዎች በተገኙበት እየተከናወነ ይገኛል።

#ድምፀ_ተዋህዶ

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.