የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


ይህ በኡስታዝ ሱልጣን ኸድር እውቅና የተከፈተ ብቸኛው (official) ቻነል ሲሆን የእርሱ ትምህርቶችና አጫጭር መልእክቶች በየጊዜው የሚተላለፉበት ልዩ መድረክ ነው፡፡
አላህ መልካም ምንዳውን ይክፈለው፤ ከዕውቀቱም ተጠቃሚ ያድርገን!
ትምህርታዊ ቁም ነገሮች ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ እንዲሁም ሐሳብና አስተያየት ካልዎት በዋትስ ኣፕ ይላኩልን!
♻: https://api.whatsapp.com/send?phone=

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


ሸይኽ ኢብን ዑሠይሚን ረሂመሁ አሏህ እንዲህ ብለዋል፡-

"የቀልብ መድረቅ ለማስወገድ ከሚረዱ አንዳንድ ሰበቦች መካከል፡- ቁርአንን በ"ተደቡር" በአስተውሎት በብዛት መቅራት፣ በምታነብበት ጊዜ፤ ይህ የአሏህ የተቀደሰ ንግግር እንደሆነ ማሰብ፣ የሰማያትና የምድር ፈጣሪ ንግግር እንጂ የሰው ልጆች ንግግር አለመሆኑን ማሰብ። በዚህ መልኩ ቁርኣን ከቀራህ፣ የርሱ ቃል ልብህ ውስጥ ይገዝፋል፣ ከእሱም ተጠቃሚ ትሆናለህ"።

(ተፍሲሩ ሱራቲ አል-አንዓም ገጽ 224)


የሳዑዲ የፈትዋ ሊቃውንት ቋሚ ኮሚቴ  በዘመዳሞች መካከል የሚደረገው ጋብቻ፤ ልጆች ላይ አካል ጉዳት ሊያስከትል ይችላል ወይ? በሚል ጥያቄ በተጠየቁ ጊዜ እንዲህ ሲሉ መልሰዋል፡-

"በዘመዳሞች መካከል ጋብቻ ከማድረግ የሚከለክሉ ትክክለኛ የሆኑ ሐዲሶች የሉም። በህፃናት ላይ አካል ጉዳት የሚከሰተው በአላህ ፈቃድ እና መሻት እንጂ በሰፊው እንደሚሰራጨው፤ በዘመዳሞች መካከል በሚደረገው ጋብቻ የተነሳ አይደለም።"
📚ፈትዋ አል–ለጅነቱ አድ–ዳኢማህ (13/18)

وقد سئل علماء اللجنة الدائمة عن الزواج من الأقارب وهل ذلك سبب لحصول الإعاقة للأولاد ؟
فأجابوا : " ليس هناك أحاديث صحيحة تمنع من الزواج بين الأقارب , وحصول الإعاقة إنما يكون بقضاء الله وقدره , وليس من أسبابه الزواج بالقريبات كما يشاع " انتهى .
"فتاوى اللجنة الدائمة" (18/13) .


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
🪟ረመዳንን እንዴት እንቀበለው?

🎙ሸይኽ ዐብድሰላም አሽ'ወይዒር ሀፊዘሁሏህ

📌ማስታወሻ ትሆን ዘንድ ለቀቅ ባለ አማርኛ የተተረጎመ

@Abuhatim7


👆🏻👆🏻👆🏻
📚#ፈታዋ የሚጠይቅ ሰው ሲጠይቅ የሚከተላቸው ስርዓቶች

➡️ ፈተዋ የሚጠየቀው ሰው ውጥረት ውስጥ በሆነበት ፣ ባልተረጋጋበት፣ ሀዘን ውስጥ በሆነበት ወይም በመሳሰሉት ሁኔታ ባለበት ሰዓት አለመጠየቅ

🎙በሸይኽ ኢልያስ አሕመድ

🔗 ቴሌግራም ሊንክ
https://t.me/ustazilyas/1399

🔗 ቪዲዮውን ለመከታተል
https://www.facebook.com/ustathilyas/videos/1704645983797013/
____
🏳️ የኡስታዝ ኢልያስ አሕመድ የትምህርት መድረክ
https://www.facebook.com/ustathilyas




🔴« ብላቴናው እራሱን ከባእድ ሴቶች እስካራቀ ድረስ ኸይር ላይ ነው!! »
ሸይኽ ሱለይማን አሩሓይሊ




አነስ ረዲየሏሁ ዐንሁ እንዲህ ይላሉ፦
" ሙስሊሞች ሻዕባን በገባ ጊዜ በሙስሕፎች(ቁርኣን) ላይ ይደፉ ነበር፤ የሚያነቡ ሲሆን፣ ከገንዘቦቻቸው ዘካም ያወጡ ነበር። ይህንንም ያደረጉ የነበረው ደካማውን እና ድሃውን ለረመዳን ጾም ለማበረታታት ነው።

(ለጣኢፉ አልመዓሪፍ፣ ገጽ 135)


የማይሰለች ድምፅ!
ሸይኽ ሙሐመድ አዩብ ረሂመሁላህ
ሱረቱ ጣሀ
1414 አ/ሂ ከተራዊህ ሰላት የተወሰደ


https://t.me/sultan_54


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish


አላህ የተቀሩትን የሻዕባን ቀናቶች በረካ አድርጎልን ረመዳን ይዞት የሚመጣውን ኸይሮች ሁሉ ይምናገኝ ያድርገን!!




الشيخ محمد أيوب رحمه الله


ከአቡ መስዑድ አልአንሳሪይ ራዲየሏሁ ዓንሁ እንደተዘገበው።
ነቢዩ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም በሶላት ወቅት ሰሓቦች ትከሻ ይነካሉ፣ ቀጥ ብለው እንዲቆሙ እና እርስ በርስ እንዳይለያዩ ያዝዙ ነበር። ምክንያቱም በሰፍ ውስጥ ያለው ልዩነት በልቦች ውስጥ ልዩነት ያስከትላል። ከዚያም ነቢዩ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም፦
" ከእኔ ቀጥሎ ያለው ሰፍ አጠገብ ለመቆም ተገቢዎቹ ሰዎች የአእምሮና  የጥበብ ሰዎች ናቸው፣ ከዚያም ከነርሱ ቀጥሎ  ያለ ሰው ከዚያም ቀጥሎ ሰው ነው።" አሉ።

ከዚያም አቡ መስዑድ ራዲየሏሁ ዓንሁ በዘመናቸው ለነበሩ ሰዎች እንዲህ አሉ፦ "እናንተ ዛሬ የበለጠ ልዩነት ያለባችሁ ናችሁ"፣ ይህም በነቢዩ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም ዘመን ሲነፃፀር በአቡ መስዑድ ዘመን ሰዎች መካከል ያለው ልዩነት እንደተጨመረ ያሳያል።




ነቢያችን በሸዕባን ወር ለምን አብዝተው እንደሚጾሙ ሲጠየቁ፣ እንዲህ በማለት መለሱ።
«ያ በረጀብና በረመዳን መካከል ሰዎች የሚዘነጉበት ወር ሲሆን በውስጡም ለዓለማት ጌታ ሥራዎች ከፍ ብለው የሚወጡበት ወር ነው።»
አሕመድ እና ነሳኢይ ዘግበውታል/አልባኒ ሐሠን ብለውታል


🔴 የዛሬው የጁምዓ ኹጥባ

🎙 خطبة الجمعة
شهر شعبان يغفل عنه الناس

❗️
ወርሃ ሸዕባን
ብዙሃኑ የሚዘናጋበት ወር!

🕌 ቃሊቲ ሀምዛ መስጂድ

🗓 ሸዕባን 01/1446 አ/ሂ

http://t.me/sultan_54


ሰላማ ኢብን ኩሀይል (አላህ ይዘንላቸውና)**
እንዲህ ይላሉ፡
" የሻዕባን ወር የቁርአን አንባቢዎች ወር ነው። " ይባል ነበር።"


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
شهر شعبان

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.