ታምሪን ሚዲያ(Tamrin Media)✍✍✍✍✍


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


Introducing daily news and information all over the world including our country ethiopia
ለፈጣን እና ተዓማኒ መረጃዎች ቻናላችንን ይቀላቀሉ። 🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
ቻናላችንን በመቀለቀል ወቅታዊ መረጃዎቸችን በፍጥነት ያግኙ👇👇👇
https://t.me/Tamrinmedia
✉️inbox 👉 @tamrin_bot

Связанные каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


ዶናልድ ትራምፕ የአፍሪካ መሪዎች ሰው መሆናቸውን እጠራጠራለሁ አሉ‼️

👉🏿 ከ50 ዓመታት የአህጉሪቷ የነጻነት ጉዞ በኋላ፣ ለህዝባችው አስፈላጊውን መሠረተ ልማት ካላሟላችው ሰው ነን ብላችው ታስባላችው?

👉🏿በወርቅ፣ በአልማዝ፣ በነዳጅ፣ በዩራኒየም፣ በብረት፣ በማዕድን፣ በብር፣ በማግኒዥየም፣ በነሐስ፣ በጋዝ የተፈጥሮ ሃብቶቻችው ላይ ተቀምጣችው፣ ህዝባችው በረሃብ፣ በትምህርት አለመዳረስ፣ በጤና አገልግሎት እጦት፣ ቢሞት፣ ሰው ነን ብላችው ታምናላችው?

👉🏿በስልጣን ላይ ቆይታችው፣የራሳችሁን ዜጎች ለመግደል ከውጭ የጦር መሣሪያዎችን ስታስገቡ፣ ሰው ነን ብላችው ታስባላችው?

👉🏿የገዛ ዜጎቻችሁን እንደውሻ ስታንገላቱና ስትገድሉ፣ ማን ዜጎቻችሁን እንዲያከብር ትጠብቃላችው?

👉🏿በራሳችው አገር ላይ ቀማኛና ሌባ በመሆናችው ፣ የሃገራችሁን ሀብቶች ሁሉ በመስረቅ፣ አብዛኞቹ ዜጋዎቻችው በስደትና በድህነት ውስጥ እንዲያልፉ ስታረጉ፣ የሰው ልጆ ነን ብላችው ታስባላችው?
ሲሉ ተናግረዋል😂😂😂


ስማቸውን ወደ “ትራምፕ” የቀየሩት ፖለቲከኛ

ቤን ዳውኪንስ የተባሉ የአውስትራሊያ ፖለቲከኛ ስማቸውን ወደ ኦሲ ትራምፕ ቀይረዋል።

ፖለቲካኛው ስማቸውን በአሜሪካው ፕሬዚዳንት ስም መሰየሙ ትኩረት ለማግኘት እና የትራምፕ የፖለቲካ አቋም ደጋፊ መሆናቸውን ለመግለጽ ነው ብለዋል።

በአዲሱ ስማቸው ኦሲ ትራምፕ የተባሉት ግለሰብ የምዕራብ አውስትራሊያ የላይኛው ምክር ቤት አባል ሲሆኑ የዶናልድ ትራምፕ ጸረ ግራ ዘመም ፖለቲካ አቋም አድናቂ እንደሆኑ ተናግረዋል።

ሰውዬው እንደ ዶናልድ ትራምፕ ሁሉ ነዳጅ እና ጋዝ በብዛት ማውጣትን የሚደግፉ ሲሆን “ዶናልድን ቢሮው ደውላችሁ አግኙት” ሲሉ “ክቡር ኦሲ ትራምፕ ኤምኤልሲ” በሚል በአዲሱ ስም በከፈቱት የኤክስ ገጻቸው አስፍረዋል።

ፖለቲከኛው ስማቸውን የቀየሩበት ምክንያት ለአገሪቱ ገዢ ፓርቲ ያለውን ተቃውሞ ለማሳየት ነውም ተብሏል።

ይህንንም ተከትሎ የምዕራብ አውስትራሊያ ገዢው ፓርቲ መሪ የሆኑት ሮጀር ኩክ የፖለቲከኛው ተግባር ትኩረት ፍለጋ የተደረገ አትርሱኝ ባይነት ነው ሲሉ ተችተውታል።

የምዕራብ አውስታራሊያ ግዛት በቀጣዩ ወር ምርጫ እንደምታካሂድም ስካይ ኒውስ ዘግቧል።
https://t.me/Tamrinmedia


አስገራሚ ዜና

የመቀሌ ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ መድህን በ75 ዓመታቸው ወለዱ።

ከዚህ ቀድም በ73 ዓመቷ ሕንዳዊ ተይዞ የነበረው ክብረ ወሰንም በእጃቸው ማስገባት ችለዋል።

"በዚህ ዕድሜየ ልጅ አገኛለው ብየ አስቤው አላውቅም፤ ከአርግዘሻል ስባልም ማመን አልቻልኩም ነበር፤ ስምንት ወር እስኪሞላኝ ድረስ በምስጢር ይዤ ነው የጤና ክትትል ያደረግኩ" ብለዋል ወይዘሮ መድህን ባርካ።

መረጃው የድምፂ ወያነ ቴሌቪዥን ነው


በጋምቤላ ክልል የመንግስት የሥራ ሰዓት ለውጥ ይደረጋል።

ከነገ ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆነው የሥራ ሰዓት ለውጥ በሙቀት መጨመር ሳቢያ ነው ተብሏል።

በክልሉ የሙቀቱ መጨመር ለሥራ ምቹ ባለመሆኑ ነገ የሚጀምረው የሥራ ሰዓት ለውጥ ለ3 ወራት ይቆያል።

በዚህ መሰረትም ቀደም ሲል የመደበኛው የሥራ ሰዓት ከጠዋቱ 1፡00 እስከ 6 ፡30 የነበረው ከ1፡00 እስከ 5፡30 ይሆናል።

እንዲሁም ከሰዓት በኋላ ከቀኑ 9፡00 እስከ 11፡30 የነበረው ከ10፡00 እስከ 12፡30 እንዲሆን የክልሉ አስተዳደር ወስኗል።

የሥራ ሰዓት ለውጡ በማጃንግ ዞን የመንገሺና ጎደሬ ወረዳዎችን እንደማይጨምር ተጠቁሟል።
https://t.me/Tamrinmedia


አርቲስት ቴዎድሮስ ተሾመ ፤ የግሮቭ ጋርደን ባለቤት እንደፃፈው!...
***

ግሮቭ ጋርደን ወደ ትዝታነት ተቀይሯል።
ለወንዝ ዳርቻ ልማት ቦታውን ለቋል።

ላለፉት አምስት አመታት አብራችሁን ለነበራችሁ የዕለት ተዕለት ደንበኞቻችን፣ ሠርጋችሁን በግሮቭ ጋርደን ለደገሳችሁ ሙሽሮቻችን፣ የፍቅር ጥያቄያችሁን በግሮቭ ጋርደን ያደረጋችሁ እጮኛሞቻችን፣ልደታችሁን እኛ ጋ ላደረጋችሁ ልጆቻችን፣
የጋብቻ በዓላችሁን በግሮቭ ላከበራችሁ አንጋፋዎቻችን፣ በኦፕን ኤር ሲኒማችን ተቃቅፋችሁ ለደመቃችሁ ፍቅረኞቻችን፣
በሰርከስ ዝግጅቶቻችን እርካታን ለሸመታችሁ ቤተሰቦቻችን፣ እግር ኳስ በሜዳችን ለተጫወታችሁም በስክሪናችን ለኮመኮማችሁም የስፖርት ወዳጆቻችን፣
መጽሐፎቻችሁን ላስመረቃችሁ ደራሲዎቻችን፣
ፊልሞቻችሁን ለቀረፃችሁ አርቲስቶቻችን፣
ክሊፖቻችሁን ላስከሸናችሁ ድምፃውያኖቻችን፤
ለሁላችሁም ከልብ የመነጨ ምስጋናችን ይድረሳችሁ።

በአገልግሎታችን ቅር ለተሰኛችሁ ምህረታችሁን እንሻለን።
ለተደሰታችሁ ደግሞ የትዝታችሁ አካል ስለነበርን ደስታችን ወደር የለውም።

የግዮን ሆቴል ሰራተኞችና አመራሮች ለነበረን ቆይታ እናመሠግናለን።
ባስከፋናችሁ ይቅርታችሁን እንሻለን።
ላስከፋችሁን ደግሞ ይቅር ብለናል።

ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን አብዝቶ ይባርክ!!
አሽቃባጭም አልተረፈም ዘንድሮማ😂😂😂
https://t.me/Tamrinmedia


🐪 ትራምፕ ኢራን እንድትደመሰስ ትዕዛዝ ሰጡ!

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፥ ኢራን እርሳቸውን የምትገድላቸው ከሆነ፥ አሜሪካ ኢራንን እንድታወድም የሚያደርግ ትዕዛዝ ለአማካሪዎቻቸው ማስተላለፋቸውን ተናገሩ።

ትራምፕ ይህን የተናገሩት፥ እርሳቸው የሚመሩት የአሜሪካ መንግስት ኢራን ላይ ከፍተኛ ጫና ለማሳደር የሚያግዙ ፖሊሲዎችን ማስፈጸሚያ ትዕዛዝ ላይ ፊርማቸውን ባኖሩበት ወቅት መሆኑን አሶሼትድ ፕረስ ዘግቧል።

ከኢራን መሪዎች ጋር በቴህራን ፊት ለፊት ተገናኝቶ የመምከር ፍላጎት እንዳላቸው የተናገሩት ትራምፕ፥ "እነርሱ እኔን የሚገድሉኝ ከሆነ፥ ኢራን እንድትወድም ለአማካሪዎቼ ትዕዛዝ ሰጥቻለሁ። ይህም አንዳች ነገር እንዳይቀራቸው ያደርጋል" ማለታቸውን ዘገባው አክሏል።

ሆኖም ፕሬዝዳንቱ እንዳሉት ቢገደሉ ምክትላቸው ጄዲ ቫንስ መንበረ ስልጣኑን የሚረከቡ ይሆናል የሚለው የአሶሼትድ ፕረስ ዘገባ፥ ይህ ደግሞ ቀዳሚው ፕሬዝዳንት ያስቀመጠውን ትዕዛዝ እንዲያስፈጽም የሚያስገድደው አለመሆኑን ጠቅሷል።

የ78 ዓመቱ ፕሬዝዳንት ታዲያ "ኢራን እኔን ከገደለችኝ፣ እንድትወድም ትዕዛዝ ሰጥቻለሁ" ማለታቸው፥ በምን አግባብ ይፈጸማል የሚለው ጥያቄ ምላሽ አላገኘም።

ትራምፕ በመጀመሪያው የስልጣን ዘመናቸው ማገባደጃ ማለትም እ.ኤ.አ 2020 ላይ የኢራን እስላማዊ አብዮት ዘብ መሪ የነበሩትን ቃሲም ሶሌይማኒን ካስገደሉ በኋላ፥ የትራምፕና ኢራን ፍጥጫ ከፍ ወደአለ ምዕራፍ መሸጋገሩ ይነገራል።

ከኢራን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ፕሮግራም ጋር በተያያዘ ዶናልድ ትራምፕ የሚያንጸባርቁት አቋምና እርሱን በተመለከተ የሚከተሉት ፖሊሲ ደግሞ ጡዘቱን አንሮታል።

ፕሬዝዳንቱ ኢራን በዚህ ሰዓት "እጅግ ጠንካራ" በሚባል ቁመና ላይ ስለመሆኗ ግን ከመናገር አልተቆጠቡም።


በጉጂ ዞን በመሬት መደርመስ የ8 ሰዎች ሕይወት አለፈ

በጎጂ ዞን ሳባ ቦሩ ወረዳ በባሕዊ መንገድ ማዕድን እያወጡ በነበረው ሰዎች ላይ በደረሰው የመሬት መደርመስ የስምንት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የዞኑ ኮሚኒኬሽን ገልጸዋል፡፡ የዞኑ ኮሙኒኬሽን ኃላፊ አቶ አሸናፊ ዳንቆ ለዲዳቢሊው እንደገለጹት በትናትናው ዕለት 9፡00 ገደማ አደጋው መድረሱን ገልጸው በቦታው በባሕላዊ መንገድ ሲያወጡ የነበሩ ሕይወታቸው ያለፈው 8ቱ ሰዎች አስከረን ዛሬ መውጣቱን አመልክተዋል፡፡

‹«ቦታው ጉጂ ዞን ሳባ ቦሩ ወረዳ ቃቲቻ የሚባል ቀበሌ ውስጥ ነው፡፡ በትናንትናው ዕለት ከ9፡00 በኋላ ነው ድርጊቱ የተፈጠረው፡፡ በባሕላዊ መንገድ ማዕድን በማውጣት እየሠሩ የነበሩ ሰዎች ላይ አፈር ተንሸራርቶ የስምንት ሰዎች ሕይወት አልፏል፡፡ ሕይወታቸውን ለማሻሻል በባሕላዊ መንገድ የሚሠሩ ሰዎች ናቸው መሬት ተንሸራርቶ ነው ሕይወታቸው ያለፈው አስከረናቸው ወጥቷል›› ብለዋል ።

ሳባ ቦሩ ወረዳ ከጉጂ ዞን አስተዳደር መቀመጫ ከሆነችሁ አዶላ ከተማ 70 ኪ.ሜ ገደማ ላይ የሚትገኝ ወረዳ ናት፡፡


🇮🇳 😎

ከአዲስ ፍቅረኛዋ ጋር ለመኖር የባሏን ኩላሊት ያሸጠችው ህንዳዊት

ኩላሊቱ በጥቁር ገበያ ቢሸጥ ለሴት ልጃቸው የትምህርት ወጪና ጥሎሽ እንደሚሆን አሳምና ነው የተሸጠው

ከኩላሊት ሽያጭ የተገኘውን ከ11 ሺህ በላይ ዶላር በፌስቡክ ከተዋወቀችው አዲሱ ፍቅረኛዋ ጋር እየተዝናናችበት ነው ተብሏል

በምዕራብ ቤንጋላ ሳንካሬል በተባለች ከተማ ነዋሪ የሆነችው እንስት ባሏ የአካል ክፍሉን እንዲሸጥ ያሳመነችው የሴት ልጃችን የትምህርት ወጪ ለመሸፈንና ለትዳር እድሜዋ ሲደርስ ለጥሎሽ የሚሆን ገንዘብ እንዳንቸገር በሚል ነው።

ባል መጀመሪያ ላይ የሚስቱን አንድ ኩላሊትህን ሸጠን ችግራችን እንለፍ በሚለው ሀሳብ በፍፁም እንደማይቀበለው ቢገልፅም የወራት ውትወታዋ አቋሙን እንዲለውጥ አድርጎታል።

ባል የቤተሰቡን ወቅታዊ የገንዘብ ችግር እና የልጁን የወደፊት ህይወት ለማቃናት መስዋዕትነት መክፈሉ ጥቅሙ እንደሚያመዝን አምኖበት የሚስቱን ጥያቄ መቀበሉን ያወሳል።

በህንድ የሰው የአካል ክፍልን መሸጥ ወንጀል በመሆኑ የኩላሊት ሽያጩ ሚስት በፈለገችበት ጊዜ አልተካሄደም፤ በጥቁር ገበያ ኩላሊት ገዥ ፍለጋው አንድ አመት ወስዷል ይላል የሂንዱስታን ታይምስ ዘገባ።

ከሶስት ወራት በፊት ስሙ ያልተጠቀሰውን ህንዳዊ ኩላሊት የሚገዛ አንድ ሰው ተገኝቶ 1 ሚሊየን የህንድ ሩፒ (11 ሺህ 500 ዶላር) ለሚስቱ መሰጠቱንም ዘገባው ጠቅሷል።

ድብቅ አቅዷን ለማሳካት ረጅም ጊዜን የጠበቀችው ሚስት ከባሏ አንድ ኩላሊት ሽያጭ የተገኘው ገንዘብ በእጇ እንደገባ በቤቷ ማደርን በመተው አድርሻዋን ታጠፋለች።

ጉዳዩ ግራ ያጋባው ባል የሚስቱን መጥፋት ለፓሊስ ሲያሳውቅ ልቡን በሀዘን የሚሰብር መረጃ ደርሶታል።

የባሏን ኩላሊት በልጃቸው አመካኝታ ያሸጠችው እንስት ባራክፖር በተባለ ከተማ በፌስቡክ ከተዋወቀችው አዲስ "ፍቅረኛዋ" ጋር እንደምትኖር ለማወቅ ተችሏል፡፡

ክህደት የተፈጸመበት ባል ከፖሊስ በተሰጠው ጥቆማ ሚሰቱና አዲሱ ፍቅረኛዋ ወደሚኖሩበት ቤት ከ10 አመት ልጃቸውና ቤተሰቦቻቸው ጋር ቢያቀናም የልጁ እናት ሚስቱ ከቤት አልወጣም ብላለች።

በር ለመክፈት ፈቃደኛ ካለመሆኗ ባሻገር ለልጇ አባት "የፈለከውን ነገር ማድረግ ትችላለህ፤ የፍቺ ማመልከቻ እልክልሀለው" ማለቷም ልቡን እንደሰበረው ተናግሯል።

ግለሰቡ በተደራረበ ሀዘን ውስጥ ልጁን በብቸኝነት ማሳደግ ጀምሯል።


በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ተከስቶ የነበረውን የእሳት አደጋ መቆጣጠር ተቻለ
በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ቡልቡላ 40/60 እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ የተከሰተውን የእሳት አደጋ ወደ ሌላ ቦታ ሳይዛመት መቆጣጠር መቻሉ ተገለጸ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ ንጋቱ ማሞ ለፋና ዲጂታል እንዳሉት ፥ የእሳት አደጋው ዛሬ ከቀኑ 11 ሰዓት ከ 10 ደቂቃ አካባቢ ተከስቷል።

በአካባቢው በሚገኘው በአንድ ጅምር ሕንጻ ግራውንድ ላይ የተከማቸ የሕንጻ መሳሪያ ልዩ ልዩ ቁሳቁስ ላይ የእሳት አደጋ አጋጥሞ እንደነበረም ነው የገለጹት።

እሳቱን ለማጥፋት የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች ባደረጉት ርብርብ እሳቱ ወደ ሌላ ቦታ እንዳይዛመት በማድረግ መቆጣጠር መቻሉንም ተናግረዋል ባለሙያው፡፡

የእሳት አደጋውን ለማጥፋት ስድስት የአደጋ መቆጣጠር ተሽከርካሪና 2 የውሃ ቦቴ ከ40 የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች መሰማራቱን አንስተው ፥ በአደጋው በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት አለመኖሩንና በንብረት ላይ የደረሰው ጉዳት እየተጣራ መሆኑን አመልክተዋል።


የኢህአዴግ ከፍተኛ አመራር የነበሩት አቶ ብርሃኑ አዴሎ፤ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽንን እንዲመሩ ተሾሙ

በቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የስልጣን ዘመን ለስድስት ዓመት ገደማ የካቤኔ ጉዳዮች ኃላፊ ሆነው የሰሩት አቶ ብርሃኑ አዴሎ፤ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽንን (ኢሰመኮ) እንዲመሩ በፓርላማ ተሾሙ።

አቶ ብርሃኑ የብሔራዊው የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር የሆኑት፤ ተቋሙን ለአምስት ዓመታት የመሩትን ዶ/ር ዳንኤል በቀለን በመተካት ነው። ዶ/ር ዳንኤል ከኃላፊነታቸው የተሰናበቱት፤ የስራ ዘመናቸው ባበቃበት ባለፈው ዓመት ሐምሌ ወር ነበር።

ላለፉት አምስት ወራት ኢሰመኮን የመምራት ኃላፊነት በተጠባባቂነት ተረክበው የቆዩት የእርሳቸው ምክትል የነበሩት ራኬብ መሰለ ናቸው።

ተጠሪነቱ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሆነው ኢሰመኮ፤ ለሰብዓዊ መብቶች መስፋፋት፣ መከበር እና ጥበቃ የመስራት ስልጣን በአዋጅ የተሰጠው ነው።

በ2012 ዓ.ም. የተሻሻለው የኢሰመኮ ማቋቋሚያ አዋጅ፤ ተቋሙን በዋና ኮሚሽነርነት፣ በምክትል ዋና ኮሚሽነርነት እና በዘርፍ ኮሚሽነርነት የሚያገለግሉ ኃላፊዎች በተወካዮች ምክር ቤት እንደሚሾሙ ይደነግጋል። 

ዛሬ ሐሙስ ጥር 22፤ 2017 በተካሄደው የተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ፤ ኮሚቴው የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር እንዲሆኑ አቶ ብርሃኑ አዴሎን በዕጩነት አቅርቧል። ላለፉት አስር አመታት በግል አማካሪነት እና ጠበቃነት እየሰሩ የቆዩት አቶ ብርሃኑ፤ በኢህአዴግ የስልጣን ዘመን በከፍተኛ የኃላፊነት ቦታ የሰሩ ናቸው። 
https://t.me/Tamrinmedia


ቀሲስ በላይ መኮንን በ5 ዓመት ጽኑ እስራትና በ10 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ተቀጡ።
https://t.me/Tamrinmedia


ሰበር ዜና

1,713 ኢትዮጵያዊያን ተጠርንፈው ሊባረሩ ነው

በዶናልድ ትራንፕ አስተዳደር ዉሳኔ ምክንያት ወደ ሀገራቸዉ ከሚመለሱ ሰነድ አልባ ዜጎች መካከል 1,713 ኢትዮጵያዊያን ተለይተዋል ተብሏል።

የትራምፕ አስተዳደር ላሁኑ ዙር ለማባረር ካዘጋጃቸው 1.4 ሚሊዮን ዶክመንት የሌላቸው ስደተኞች ውስጥ 1,713 ኢትዮጵያውያን ይገኙበታል

የሚያሳዝነው አብዛኞቹ ኢትዮጵያውያን እርስ በርሳቸው የአሜሪካ መንግስት ላስቀመጠው የብር ሽልማት ብለው እየተጠቋቀሙ መሆኑ ተሰምቷል
አይ ሀበሻ😂😂


መነኸሪያ ሬዲዮ ይቅርታ ጠየቀ፣ ፕሮግራሙ ታግዷል።

ቲክቶከር ሮማን በመናኸሪያ ሬዲዮ 99.1 በተባባሪ አዘጋጆች ከሚቀርቡ ዝግጅቶች መካከል አንዱ በሆነው  የብርሐን መንገድ በተሰኘ ፕሮግራም ላይ መቅረቧ ይታውቃል፡፡

የቀረበችው “ማኅበራዊ ሚዲያን ለበጎ አላማ ማዋል” በሚል ከዚህ በፊት በማህበራዊ ሚዲያ ያስተላለፈችውን የተዛቡ አመለካከቶችን በተመለከተ ይቅርታ ለመጠየቅ እና ከስህተቷ ሌሎች ትምህርት እንዲወስዱ ነው፡፡

በመሆኑም በርካታ አድማጮቻችን በግለሰቧ መቅረብ መከፋታቸውን ነግረውናል፡፡ ለተፈጠረው ጉዳይ ጣቢያችን ይቅርታ እየጠየቀ ላልተወሰነ ጊዜ በተባበሪ አዘጋጆች የሚቀረበው የብርሐን መንገድ የተሰኘ ፕሮግራም የታገደ መሆኑን እናሳወቃለን፡፡ 

በተጨማሪም በቀጥታ ስርጭት ወቅት የፕሮግራሙ አዘጋጆች  በቀጥታ ስልክ መስመር የገባ አድማጭን ያቋረጡበት መንገድ  ከሙያ ስነምግባር ያፈነገጠ በመሆኑ አጣርተን እርምጃ የምንወስድ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
እውነትም መናኸሪያ😀
https://t.me/Tamrinmedia



14 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.