አስ_ሱናህ


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


ይህ ቁርኣን እና ሐዲስ መሰረት በማድረግ የመልካም ቀደምቶቻችን ፋና በመከተል ስለ እስልምናችን የምንማማርበት እና የምንመካከርበት ቻናል ነው።
💎እዲሁም የኡለማዎች አጫጭር ፈትዋዎች ይለቀቁበታል إن شاء الله

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


በዚህ የረመዳን ወር ወደ ኋላ መቅረት ዋጋ ያስከፍላል።
ገብቶ ሲወጣ ፈጣን ነውና መዘናጋት አያስፈልግም።
ምጥቀት ያሻል…
ወሩን በመልካም ስራ ለማጠናቀቅ ወኔ ያስፈልጋል…
"(የረመዳን ቀናት) የሚቆጠሩ ቀናት ናቸው።"
"(በመልካም ስራ) ተሽቀዳዳሚዎች ይሽቀዳደሙ።"
👇👇👇
@tewihd


#رمضان_ረመዳን 🌙

"በአላህ ይሁንብኝ!! ለቀብር ባለቤቶች ተመኙ
ቢባሉ ኖሮ ከረመዷን አንዲትን ቀን ይመኙ ነበር"።

📚{ኢብኑልጀውዚ ረሒመሁሏሁ}
👇👇👇👇
👉@tewihd


ከረመዷን ሐዲሶች

ረሱል - ﷺ - እንዲህ ይላሉ ፦ የረመዷንን ወር በአላህ አምኖ እና ምንዳውን ከአላህ አገኛለው ብሎ የፆመ ሰው በፊት ያሳለፈው ወንጀሎች ይማሩለታል። (ቡኻሪ ፥ 37 / ሙስሊም ፥ 759)
👇👇👇
@tewihd


⭕ #የረመዷን_ትሩፋቶች

ጾም ከኢስላም ማዕዘናቶች መካከል አንዱ ሲሆን የሚያስገኛቸው ፋይዳዎችና በረከቶች በርካታ ናቸው፡፡ ከእነዚህ ፋይዳዎች መካከል የአላህ መልክተኛ ﷺ በሐዲሳቸው የተናገሩት አንዱ ነው፡፡

"من صام رمضان إيمانا واحتسابا غفر له ما تقدم من ذنبه" البخاري: ٣٨، مسلم: ٧٥٩

“ከአላህ ዘንድ የሚገኘውን አጅር ታሳቢ አድርጎ እና አምኖ የረመዷንን ጾም የጾመ ከዚህ በፊት ያለፈው ወንጀሉ ይሰረዝለታል፡፡” (ቡኻሪ: 38, ሙስሊም: 759)

ጾም በመጾም የሚገኘው ምንዳ ወይም አጅር እንደ ሰዎች ኒያ ወይም ኢኽላስ ሊለያይ ይችላል፡፡ በጾሙ መካከል ተፈጻሚ የሚሆኑ መልካም ተግባራቶች አንዱን ከፍ አንዱን ዝቅ ሊያደርጉት ይችላሉ፡፡ ለምሳሌ የጾምን አዳብና ስርዓት የሚጠብቅ እና የማይጠብቅ ከአላህ ዘንድ እኩል ደረጃ አይኖረውም፡፡

የረመዷንን ወር ከሌሎች ወሮች ለየት የሚያደርገው የሚሰሩ መልካም ተግባራት ሁሉ ምንዳቸው እጥፍ ድርብ መሆኑ ነው፡፡ በዚህም 。。。


🔶 በረመዷን ወር ሙስሊሙ ሊሰራቸው የሚገቡ መልካም #ተግባራት
.
.
👇👇👇👇👇👇👇
http://telegram.me/tewihd


አስ_ሱናህ dan repost
በእድሜ የገፉ ሰዎች፣ የነፍሰ‐ጡር እና አጥቢ ሴቶች ጾም ሸሪዓዊ ብይን

ጥያቄ፡- ጾም መጾም ያቃታቸው ሽማግሌዎችና አሮጊቶች መዳን ያልቻሉ በሽተኞች እርጉዝ ሴቶች እና ጾም ከጾምን ጡታችን ይደርቃል ብለው የሰጉ አጥቢ ሴቶች የረመዷንን ጾም አፍጥረው ለእያንዳንዱ ቀን ምስኪን ማብላት ይችላሉ?
መልስ፡-
1ኛ፡- በእድሜ መግፋት የተነሳ የረመዷንን ጾም መጾም ያልቻሉ ወይም በጣም ተጨናንቀውና ከብዷቸው የሚጾሙ ሽማግሌዎች እና አሮጊቶች እንደዚሁ ጾሙን መጾም ያልቻለ ወይም በግድ የሚጾም መዳኑ ተስፋ የሌለው በሽተኛ የረመዷንን ጾም እንዲያፈጥሩ ተፈቅዶላቸዋል፡፡ ነገር ግን ቤተሰቡን ከሚመግበው እህል ከስንዴ፣ ከተምር፣ ከሩዝ እና ከመሳሰሉት የአንድ ቁና ግማሽ (አንድ ኪሎ ተኩል) ለእያንዳንዱ ያፈጠሩበት ቀን አንዳንድ ሚስኪን ማብላት ይኖርባቸዋል፡፡

አላህ እንዲህ ብሏል፡-
{لاَ يُكَلِّفُ اللّهُ نَفْساً إِلاَّ وُسْعَهَا..  } (البقرة: ٢٨٦)
“አላህ ነፍስን ከችሎታዋ በላይ አያስገድዳትም፡፡” (በቀራህ፡ 286)

{..وَمَا جَعَلَ عَلَيْكُمْ فِي الدِّينِ مِنْ حَرَجٍ.. } (الحج:٧٨)
“በእናንተ ላይ በሃይማኖቱ ውስጥ ምንም ችግር አላደረገባችሁም፡፡” (ሀጅ፡ 78)

{...وَعَلَى الَّذِينَ يُطِيقُونَهُ فِدْيَةٌ طَعَامُ مِسْكِينٍ... } (البقرة :١٨٤)
“በእነዚያም ጾምን በማይችሉት ላይ ቤዛ ድሃን ማብላት አለባቸው፡፡” (በቀራህ፡ 184)

قال ابن عباس : "نزلت رخصة في الكبير والمرأة الكبير وهما لا يطيقان الصيام : أن يفطرا ويطعما عن كل يوم مسكينا" رواه البخاري : ٤٥٠٥)
አብደሏ ብን አባስ እንዲህ ይላሉ፡-
“ይህ የቁርዓን አንቀጽ ጾምን መጾም ለማይችሉ ሽማግሌዎችና አሮጊቶች እንዲያፈጥሩና ለእያንዳንዱ ቀን ምስኪን እንዲያበሉ የወረደ ነው፡፡” ቡኻሪ: 4505)

በሽተኛ ሆኖ ጾም መጾም ያልቻለ ወይም በጣም ከብዶት የሚጾም ሊድን ያልቻለ በሽታ ያለበት ሰው ሸሪኣዊ ብይናቸው ልክ ጾም ያቃታቸው ሽማግሌዎች እና አሮጊቶች አይነት ነው፡፡
2ኛ፡- በነፍሷ ወይም በተጸነሰው ልጅ ላይ ጉዳት ይመጣል ብላ የፈራች ነፍሰ‐ጡር፤ ወይም በነፍሷ ወይም በምታጠባው ህጻን ላይ ችግር ይመጣል ብላ የሰጋች አጥቢ ሴት ልክ ከበሽታው መዳን እንዳልቻለው ሰው ያፈጠሩበትን ቀን ቆጥረው ቀዷእ የማውጣት ግዴታ አለባቸው፡፡

وبالله التوفيق ، وصلى الله على نبينا محمد وآله وصحبه وسلم.
فتاوى اللجنة الدائمة للبحوث العلمية والإفتاء (10/160


@tewihd


⭕ #የረመዷን_ትሩፋቶች

ጾም ከኢስላም ማዕዘናቶች መካከል አንዱ ሲሆን የሚያስገኛቸው ፋይዳዎችና በረከቶች በርካታ ናቸው፡፡ ከእነዚህ ፋይዳዎች መካከል የአላህ መልክተኛ ﷺ በሐዲሳቸው የተናገሩት አንዱ ነው፡፡

"من صام رمضان إيمانا واحتسابا غفر له ما تقدم من ذنبه" البخاري: ٣٨، مسلم: ٧٥٩

“ከአላህ ዘንድ የሚገኘውን አጅር ታሳቢ አድርጎ እና አምኖ የረመዷንን ጾም የጾመ ከዚህ በፊት ያለፈው ወንጀሉ ይሰረዝለታል፡፡” (ቡኻሪ: 38, ሙስሊም: 759)

ጾም በመጾም የሚገኘው ምንዳ ወይም አጅር እንደ ሰዎች ኒያ ወይም ኢኽላስ ሊለያይ ይችላል፡፡ በጾሙ መካከል ተፈጻሚ የሚሆኑ መልካም ተግባራቶች አንዱን ከፍ አንዱን ዝቅ ሊያደርጉት ይችላሉ፡፡ ለምሳሌ የጾምን አዳብና ስርዓት የሚጠብቅ እና የማይጠብቅ ከአላህ ዘንድ እኩል ደረጃ አይኖረውም፡፡

የረመዷንን ወር ከሌሎች ወሮች ለየት የሚያደርገው የሚሰሩ መልካም ተግባራት ሁሉ ምንዳቸው እጥፍ ድርብ መሆኑ ነው፡፡ በዚህም 。。。


🔶 በረመዷን ወር ሙስሊሙ ሊሰራቸው የሚገቡ መልካም #ተግባራት
.
.
👇👇👇👇👇👇👇
http://telegram.me/tewihd


እድለኞች ነን አላህን ልናመሰግን ይገባል!!

ጠለሓ ኢብን ዑበይደላህ ረድየላሁ ዐንሁ እንዳስተላለፉት:-
« ሁለት ሰዎች ወደ መልክተኛው ﷺ ይመጡና በተመሳሳይ ሰዓት ኢስላምን ይቀበላሉ ።
አንደኛው ዒባዳ ላይ በጣም ብርቱ ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ጅሃድን አብዝቶ ይሳተፍ ነበር ፤ እናም አንድ ቀን ጅሃድ ላይ ይገደልና ይሞታል ፤ አንደኛው እርሱ ሌላኛው ከሞተ ከአንድ ዓመት በኋላ ያርፋል ።
ጠላሃ ረዲየላሁ ዐንሁ እንዲህ ይላል፦
" አንድ ቀን በህልሜ ከነዚህ ሁለት ሰዎች ጋር በር ጀነት በር ላይ ቆሜ ነበር ፤ አንድ ነገር ከበሩ ይወጣና ከመጀመሪያው ሟች ቀጥሎ የሞተውን ሰው ግባ ይለዋል ፤ ከዚያም ድጋሚ ይመጣና መጀመሪያ የሞተውን ግባ ይለዋል ፤ ከዚያም ወደኔ ዞር ብሎ 'አንተ ሂድ ተመለስ ያንተ ጊዜ ገና ነው' ይለኛል" ::
ጠለሃ ከዕንቅልፉ እንደተነሳ ስላየው ህልም ለሰዎች ይነግራቸውና ሰዎቹም ይገረማሉ ፤ እናም ይህ ወሬ መልክተኛው ﷺ ጋር ይደርሳል ፤
እሳቸውም ፦ ሰዎቹን "ምንድ ነው ያስደነቃቹ?" ብለው ይጠይቃሉ። ሰዎቹም "የአላህ መልዕክተኛ ሆይ ከነዚህ ሁለቱ ሰዎች አንደኛው ጅሃድን አብዝቶ ይሳተፍ ነበር ሸሂድ ሆኗልም ነገር ግን ቅድሚያ ጀነትን እንዲገባ የተደረገው ቀጥሎ የሞተው ነው።" አሏቸው
የአላህ መልክተኛም ﷺ " ቀድሞ ጀነትን የገባው ሰው ከመጀመሪያው አንድን ዓመት በሕይወት አልቆየምን?"
ሰዎቹም አዎን ሲሉ መለሱ። የአላህ መልክተኛም ﷺ "#‎ረመዳንን
አላገኘምን ?
#‎አልፆመምን? ፤ ይሄንና ይሄን ያክል ሰላት
አልሰገደምን ?"
ሰዎቹም "አዎን" አሉ ።
የአላህ መልክተኛም ﷺ :- " ታዲያ በርሱና በዛኛው ሰውዬ መካከል የሰማይና የምድር ያክል በላይ ልዩነት አለ" አሏቸው:: »

_
ኢብ
ን ማጃህ (2/345, 346) ፤ ሸኽ አልባኒ በሲልሲላ አ'ሰሂሃ ሰሂህ ብለውታል ዘግበውታል

አድራሻችን ቴሌግራም
channel👉🏿@tewihd
Group👉🏿@tewihddd


ረመዷን _1
  🔃ቁርአን ጁዝእ ➊

ቃሪእ:- አቡ በክር አሽ-ሻጢሪይ
القارئ= ابو بكر الشاطري

ቻናል
👉🏿@tewihd


#ረመዷን

ታላቁ እና የተቀደሰው የረመዷን ጾም ነገ ቅዳሜ ይጀምራል።

በሳኡዲ አረቢያ የረመዷን ጨረቃ ታይታለች።

ዛሬ የተራዊህ ሶላት የሚጀመር ሲሆን ነገ ቅዳሜ  የረመዷን ጾም ይጀምራል።

👉@tewihd


✴️🌙 ሰበር ዜና ... ሰበር ዜና ⤵️

✴️ 🌙 ...*عاجل ... عاجل*...

*تم رصد هلال رمضان في تمير*

*غداً السبت أول أيام شهر رمضان المبارك*

*{تقبل الله منا ومنكم صالح الاعمال}*

*✍ "الراصد نيوز"

📮 ሱዑዲ ላይ ጨረቃ ስለታየች አላህ
ካለ ነገ ቅዳሜ የረመዷን ፆም ጅማሬ  ይሆናል።


@tewihd👉@eross_eross


🌙
    አህለን ቢከ ያ…ረመዷን
      أهلاً بك يا رمضان


  ነቢያችንﷺ ሶሐቦቻቸውን የረመዷንን መቃረብ አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ ብስራትን ሲገልጹላቸው እንዲህ ይሏቸው ነበር……

عن أبي هريرة رضي الله عنه قال، قال رسول اللهﷺ
  «أتاكم رمضان شهر مبارك فرض الله عز وجل عليكم صيامه تفتح فيه أبواب السماء وتغلق فيه أبواب الجحيم وتغل فيه مردة الشياطين لله فيه ليلة خير من ألف شهر من حرم خيرها فقد حرم»
(صحيح رواه أحمد 9/225 ( الفتح الرباني ) والنسائي 4/129 وصححه الألباني في الترغيب 1/490)

«የተባረከው የረመዷን ወር መጣላችሁ! አላህ ጾሙን በእናንተ ላይ ግዳጅ አድርጓል፡፡ በዚህ ወር የሰማይ ደጃፎች ይከፈታሉ፡፡ የጀሀነም ደጃፎች ይዘጋሉ፡፡ አመፀኛ ሰይጣናት ይታሰራሉ፡፡ አላህ ከአንድ ሺህ ወር (ስራ) የምትበልጥ የሆነች አንድ ለሊት አለችው፡፡ የዚህን ወር መልካም ነገር የተነፈገ ሰው በእርግጥም ከብዙ መልካም ነገራት የተነፈገ ነው፡፡»

             🌙የኸይር እና
          🌙የበረካ ወር!!


https://t.me/tewihd


🚨 አምስቱ የጂብሪል መልዕክቶች

➥ የፈለከውን ያክል ኑር ሟች ነህ።
➥ የፈለከውን ውደድ ትለየዋለህ።
➥ የፈለከውን ስራ ትመነዳበታለህ።
➥ ሌሊትን መቆም የአማኝ ክብር ነው።
➥ ከሰዎችም መብቃቃቱ ክብር ነው።

🎤 በኡስታዝ አቡ ዐማር ዐብድልዐዚዝ ፈረጅ አላህ ይጠብቀው።
👉🏻https://t.me/tewihd


#የእለቱ_ሐዲስ ፡
🔻ረሱል - ﷺ - እንዲህ ይላሉ ፦ [ ጀነት ውስጥ 8 በሮች አሉ ፤ በሷ ውስጥ ረያን ተብሎ የሚጠራ በር አለ ፤ ፆመኞች እንጂ አይገቡትም። ] (ቡኻሪ ዘግቦታል).

ጆይን ፦ @tewihd


✍……
ሰለፎች ስለረመዷን
قال عمرو بن قيس المُلائي :

ኡመር ኢብን ቀይስ እንዲህ አሉ

طُوبَى لِمَن أصلَحَ نفسَهُ قبل رمضان.
እድለኛ ሆነ ረመዶን ከመድረሱ በፊት እራሱን ያስተካከለ

لطائف المعارف لابن رجب.
  


👉@tewihd


ረሱል - ﷺ - እንዲህ ይላሉ ፦ [ ከአሏሁ ተዓላ ውጭ አንድም አካል በሱ ላይ ከሚሰማው ችግር የሚታገስ የለም። እነርሱ ለሱ ቢጤን ያደርጉለታል ፤ ለሱ ልጅ ያደርጉለታል ፤ ይህም ከመሆኑ ጋር እሱ ሲሳይ ይለግሳቸዋል , ጤነኛ ያደርጋቸዋል , ይሰጣቸዋል። ] (ቡኻሪ እና ሙስሊም ዘግበውታል)

📣ጆይን ፦ @tewihd


#ፆማችንን_ያበላሻሉን?#ብልትን_በመነካካት #የዘር_ፈሳሽን_ማስወጣት
"ፆመኛ ሆኖ በረመዷን የቀኑ ክፍለ-ጊዜ አውቆ ብልትን በመነካካት የዘር ፈሳሽን ማስወጣት ፆምን ያበላሻል። የግዴታ ፆም ከሆነ ቀዷእ ማውጣት አለበት። ይህም ተግባር በፆም ጊዜም ይሁን ከፆም ውጭ የተከለከለ ነው። ይህም ሰዎች "ዓደቱ-ሲሪያ" በማለት የሚጠሩት ነው።"
ሼይኽ ዓብዱልዓዚዝ ቢን ዓብዲሏህ ኢብን ባዝ
ምንጭ ፦ ["መጅሙዓል ፈታዋ" (15/267)]
ጆይን ፦ @tewihd


🔍ተዓምር🔎

📶ተኝተህ ማደርህ እኮ ተዓምር ነው ምክንያቱም  ዛሬን ማየት ያልቻሉ ብዙ ናቸው

🛜መተንፈስ እኮ ተዓምር ነው ምክንያቱም ከማሽን ውጪ የማይተነፍሱ ሞልተዋል።

*⃣የሚያስጨንቅህ ነገሮች በሞት ፊት ተራ ናቸው!

☑️ከጎደለህ ይልቅ የተሰጠህን ተመልከት፤ ከስንቱ ችግር አልፈሀል፤

🔹አበቃልኝ ብለህ ተስፋ የቆረጥክባቸው ጊዜያት እንደ ቀልድ አልፈዋል እኮ፤

🔸ወዳጄ አላስተዋልከውም እንጂ ህይወትህ አላህ በሰጠህ ተዓምር የተሞላው ነው።


🔗👉@tewihd


☞…ከቢድዓዎች_ዉስጥ…በየመስጅዶች ላይ የጨረቃንና የኮከብን ቅርጽ ማስቀመጥ አንዱ ነው። ይህ እምነት ከነሷራዎችና ከመጁሳዎች የተወረሰ መማሊኮች፣ ፋጢሚዮችና ዑስማኒዮች በሙስሊም ሀገራት ላይ እንድለመድ እንድሁም እንድሰራጭ ያደረጉት መጤ ተግባር (ቢድዓ) እንድሁም በሌሎች መመሳሰልም ጭምር ነው።

👤ሸይኽ አልባኒ


👉🏿@tewihd


ከቁርኣን ቀጥሎ የ2ኛው ትክክለኛ ኪታብ ፀሐፊ የሆኑት የቡኻሪ ሙሉ ስም ፡ ሙሐመድ ኢብኑ ኢስማዒል ኢብኑ ኢብራሂም ኢብኑልሙጊራህ ኢብኒ በርዲዘበህ አልጁዕፊ አልቡኻሪ ይባላል። እናት ከቡኻሪ በኋላ የቡኻሪን ዓይነት ሰው መውለድ አልቻለችም የተባለላቸው ... ሸይኹል ሙሐዲሲን ናቸው። አላህ ይዘንላቸው.
___
©@tewihd


🔻ሴት ብቻ ያሳደገችውን ሰው አትናቅ! ቡኻሪን , ኢማሙ ሻፍዒይን , ኢማሙ አሕመድን ማን እንዳሳደጋቸው ተመልከት!! ሁሉም የቲሞች ነበሩ
የአላህ እዝነት በነሱ ላይ ይሁን.
_
@tewihd

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.