#Update
🚨የመሬት መንቀጥቀጡ በሬክተር ስኬል 5.1 ተለክቷል !!
ባለፉት ሳምንታት ትንሽ ጋብ ብሎ የነበረው የመሬት መንቀጥቀጥ ዛሬ ጠንክሮ ተሰምቷል።
የአዋሽ አካባቢ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ጠንካራ የመሬት መንቀጥቀጥ እንደነበር ገልጸዋል።
በአዲስ አበባ በርካታ አከባቢዎች እጅግ የጠነከረ ንዝረትም ለሰከንዶች ነበር።
" እኛ የተሰማን ከወትሮው የተለየ ነበር " ያለው አንድ የቤተሰባችን አባል " ያለሁበት ህንጻ ላይ ከፍተኛ መነቃነቅ ተሰምቶናል ፤ እጅግ ያስፈራም ያስደግጥም ነበር " ሲል ገልጿል።
በርካቶችም በተመሳሳይ ህንጻ ላይ የነበረው ስሜት ከፍተኛ እንደነበር ጠቁመዋል።
ከአዲስ አበባ ውጭም በርካታ ከተሞች ላይ ንዝረቱ በደምብ ተሰምቷል።
የመሬት መንቀጥቀጡ ከአዋሽ በ50 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ መከሰቱን የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ጠቁሟል።
በሬክተር ስኬልም 5.1 መለካቱን አመላክቷል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🚨የመሬት መንቀጥቀጡ በሬክተር ስኬል 5.1 ተለክቷል !!
ባለፉት ሳምንታት ትንሽ ጋብ ብሎ የነበረው የመሬት መንቀጥቀጥ ዛሬ ጠንክሮ ተሰምቷል።
የአዋሽ አካባቢ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ጠንካራ የመሬት መንቀጥቀጥ እንደነበር ገልጸዋል።
በአዲስ አበባ በርካታ አከባቢዎች እጅግ የጠነከረ ንዝረትም ለሰከንዶች ነበር።
" እኛ የተሰማን ከወትሮው የተለየ ነበር " ያለው አንድ የቤተሰባችን አባል " ያለሁበት ህንጻ ላይ ከፍተኛ መነቃነቅ ተሰምቶናል ፤ እጅግ ያስፈራም ያስደግጥም ነበር " ሲል ገልጿል።
በርካቶችም በተመሳሳይ ህንጻ ላይ የነበረው ስሜት ከፍተኛ እንደነበር ጠቁመዋል።
ከአዲስ አበባ ውጭም በርካታ ከተሞች ላይ ንዝረቱ በደምብ ተሰምቷል።
የመሬት መንቀጥቀጡ ከአዋሽ በ50 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ መከሰቱን የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ጠቁሟል።
በሬክተር ስኬልም 5.1 መለካቱን አመላክቷል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia