ጥርትና ኩልል እያለ ይመጣል!
ስለ ብሄርተኝነት ያነበበና የገባው ሰው ቀስቃሽ አያስፈልገውም፡፡ ሁልጊዜም ስለ ህዝቡ ሰላምና ደህንነት፣ ሁልጊዜም ስለ ህዝቡ ነጻነት፣ ህልውናና ክብር ይጨነቃል፡፡ መፍትሄ ይፈልጋል፡፡ ከመሰሎቹ ጋር ይወያያል፡፡ ይደራጃል፡፡ ያደራጃል፡፡ ህዝቡን በሚጠቅሙ ተግባራዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ይሰማራል፡፡ አንዱ መንገድ ባይሳካ ሌላ መንገድ ይቀይሳል እንጅ ፈፅሞ ተስፋ አይቆርጥም፡፡ አይቷቸው ለማያውቀው ግን ደግሞ ወገኔ ለሚላቸው የብሄሩ አባላት ሁሉ ያስባል፡፡ ለዚያ ህዝብ ህልውናና ክብር ይጨነቃል፡፡ የወገኖቹ በደል እንቅልፍ ይነሳዋል፡፡ ስኬታቸውና ደስታቸው ያስፈነድቀዋል፡፡ በተቋማት መስረታና ግንባታ ውስጥ ንቁ ተዋናይ ይሆናል፡፡ የግድ እኔ ካልመራሁት ብሎ የሚመሰረተውን ተቋም በሚያውክ ተግባር ላይ አይሰማራም፡፡ ይልቁንም ስልጣንና ማእረግ ሳይኖረው በምግባሩ መሪ ሆኖ የትግሉ ተዋናይ ይሆናል፡፡
የእንዲህ አይነት ብሄርተኞች ቁጥር እየበረከተ ሲሄድ ነው ያ ህዝብ ነፃነቱ የተረጋገጠ የሚሆነው፡፡ በሁሉም የተሳካላቸው ብሄርተኝነቶች ውስጥ እንዲህ አይነት ሁለመናቸውን ለህዝባቸው የሰጡ (selfless) ሰዎች አሉ፡፡ እነዚያ ጀግኖች ናቸው የዚያ ብሄርተኝነት መስራች አባቶች የሚባሉት፤ አብሪ ከዋክብት የሚባሉት፡፡
አንድ ጊዜ በፖለቲካ የተነደፈ ሰው ከፖለቲካ ለመውጣት ይከብደዋል፡፡ አንድ ጊዜ ብሄርተኛ የሆነ ሰው ደግሞ ከዚያ በላይ ነው፡፡ ሳይፈልግ ራሱን የሆነ ቦታ ውስጥ ያገኘዋል፡፡ ካልተሳተፈ እረፍት አያገኝም፡፡ ልሸሸው ቢልም የወገኖቹ መጠቃት ያቃጭልበታል፡፡ ስለዚህም ያለ ቀስቃሽ በሚችለው መንገድ ሁሉ አስተዋፅኦ ለማድረግ ይታትራል፡፡
በአማራ ትግል ውስጥ አሁን የምናየው ተነፋራ ነገር የብሄርተኛው ቁጥር ከማነሱ የመነጨ ነው፡፡ ብሄርተኝነቱን በየእለቱ እየከተኮትን ስናሳድገው ትግላችን ጥርትና ኩልል እያለ ይመጣል፡፡ ድላችን ይቀርባል፡፡ የተቋማት ባለሀብቶች እንሆናለን፡፡ በሁሉም መስክ አማራ ጀግና ተሟጋቾችን ያገኛል፡፡ ስለሆነም ሀልጊዜም የአማራ ብሄርተኝነትን ማጠናከር ይገባናል፡፡
የአማራ ብሄርተኝነት ይለምልም!!!
ስለ ብሄርተኝነት ያነበበና የገባው ሰው ቀስቃሽ አያስፈልገውም፡፡ ሁልጊዜም ስለ ህዝቡ ሰላምና ደህንነት፣ ሁልጊዜም ስለ ህዝቡ ነጻነት፣ ህልውናና ክብር ይጨነቃል፡፡ መፍትሄ ይፈልጋል፡፡ ከመሰሎቹ ጋር ይወያያል፡፡ ይደራጃል፡፡ ያደራጃል፡፡ ህዝቡን በሚጠቅሙ ተግባራዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ይሰማራል፡፡ አንዱ መንገድ ባይሳካ ሌላ መንገድ ይቀይሳል እንጅ ፈፅሞ ተስፋ አይቆርጥም፡፡ አይቷቸው ለማያውቀው ግን ደግሞ ወገኔ ለሚላቸው የብሄሩ አባላት ሁሉ ያስባል፡፡ ለዚያ ህዝብ ህልውናና ክብር ይጨነቃል፡፡ የወገኖቹ በደል እንቅልፍ ይነሳዋል፡፡ ስኬታቸውና ደስታቸው ያስፈነድቀዋል፡፡ በተቋማት መስረታና ግንባታ ውስጥ ንቁ ተዋናይ ይሆናል፡፡ የግድ እኔ ካልመራሁት ብሎ የሚመሰረተውን ተቋም በሚያውክ ተግባር ላይ አይሰማራም፡፡ ይልቁንም ስልጣንና ማእረግ ሳይኖረው በምግባሩ መሪ ሆኖ የትግሉ ተዋናይ ይሆናል፡፡
የእንዲህ አይነት ብሄርተኞች ቁጥር እየበረከተ ሲሄድ ነው ያ ህዝብ ነፃነቱ የተረጋገጠ የሚሆነው፡፡ በሁሉም የተሳካላቸው ብሄርተኝነቶች ውስጥ እንዲህ አይነት ሁለመናቸውን ለህዝባቸው የሰጡ (selfless) ሰዎች አሉ፡፡ እነዚያ ጀግኖች ናቸው የዚያ ብሄርተኝነት መስራች አባቶች የሚባሉት፤ አብሪ ከዋክብት የሚባሉት፡፡
አንድ ጊዜ በፖለቲካ የተነደፈ ሰው ከፖለቲካ ለመውጣት ይከብደዋል፡፡ አንድ ጊዜ ብሄርተኛ የሆነ ሰው ደግሞ ከዚያ በላይ ነው፡፡ ሳይፈልግ ራሱን የሆነ ቦታ ውስጥ ያገኘዋል፡፡ ካልተሳተፈ እረፍት አያገኝም፡፡ ልሸሸው ቢልም የወገኖቹ መጠቃት ያቃጭልበታል፡፡ ስለዚህም ያለ ቀስቃሽ በሚችለው መንገድ ሁሉ አስተዋፅኦ ለማድረግ ይታትራል፡፡
በአማራ ትግል ውስጥ አሁን የምናየው ተነፋራ ነገር የብሄርተኛው ቁጥር ከማነሱ የመነጨ ነው፡፡ ብሄርተኝነቱን በየእለቱ እየከተኮትን ስናሳድገው ትግላችን ጥርትና ኩልል እያለ ይመጣል፡፡ ድላችን ይቀርባል፡፡ የተቋማት ባለሀብቶች እንሆናለን፡፡ በሁሉም መስክ አማራ ጀግና ተሟጋቾችን ያገኛል፡፡ ስለሆነም ሀልጊዜም የአማራ ብሄርተኝነትን ማጠናከር ይገባናል፡፡
የአማራ ብሄርተኝነት ይለምልም!!!