መከራዬ በበዛ መጠን የጣዕመ ፍቅርህ ብርሃን በእኔ ላይ ያጽደለድላል ያረጋጋኛልም ::ራሱን ስለ አንተ ፍቅር አሳልፎ ለመስጠት በቁርጥ ሕሊና ለተዘጋጀ ሰው መከራው ከመጠን እስክያልፍም ድርስ ምሕረትህን አታዘገይም ::
ከዚህች ከመራራይቱ መከራ ጥዑም ጸጋ ይፈልቃልና ስለ ፍቅርህ ብሎ መከራ መስቀልን ለሚሸከም ሰው በመከራው ሁሉ አንተ አብረህው ካለህ ስቃዮቹ ሁሉ የተድላ ደስታ ምንጮች እና ፏፏቴዎች ይሆኑለታል ::ሊጠግባቸው የሚመኛቸው የጣዕመ ጸጋ እና ተድላ ደስታ መፍለቂያ ይሆኑለታል :: ስለ ፍቅሩ ሰውነታቸውን በመከራ የሚያስጨንቁትን በልቡናቸው ተገልጦ ያዘኑትን ለሚያረጋጋ መሥተፍሥሂ ለሚሆን ለእርሱ ምስጋና ይሁን ለዘለዓለሙ አሜን በእውነት ያለ ሐሰት ይደረግ ::
(ቅዱስ ወቅሪስ )
ከዚህች ከመራራይቱ መከራ ጥዑም ጸጋ ይፈልቃልና ስለ ፍቅርህ ብሎ መከራ መስቀልን ለሚሸከም ሰው በመከራው ሁሉ አንተ አብረህው ካለህ ስቃዮቹ ሁሉ የተድላ ደስታ ምንጮች እና ፏፏቴዎች ይሆኑለታል ::ሊጠግባቸው የሚመኛቸው የጣዕመ ጸጋ እና ተድላ ደስታ መፍለቂያ ይሆኑለታል :: ስለ ፍቅሩ ሰውነታቸውን በመከራ የሚያስጨንቁትን በልቡናቸው ተገልጦ ያዘኑትን ለሚያረጋጋ መሥተፍሥሂ ለሚሆን ለእርሱ ምስጋና ይሁን ለዘለዓለሙ አሜን በእውነት ያለ ሐሰት ይደረግ ::
(ቅዱስ ወቅሪስ )