#እመቤታችን_ቤዛዊተ_ኩሉ_ዓለም_ናት!!!
በማኅበራዊ ሚድያ ሲዘዋወር አንድ አባት የተናገሩት ቢድዮ አየሁት፡፡ጥቂት ነገር ልበል፡፡
ቤዛ ምንድን ነው???
#ቤዛ፣ቤዛነት ማለት ስለ አንድ ነገር ምትክ መሆን ነው፡፡እመቤታችን ቤዛ ናት ማለት እግዚአብሔር ቃል ሰው እንዲሆን ከሰው ልጅ የሚጠበቅ ነገር አለ ይህም መርገመ አዳም ወሄዋን ያልወደቀበት ንጹሕ ዘርእ ነው፡፡
እመቤታችን ቤዛ የሆነችው ደቂቀ አዳም ይጠብቁት የነበረውን ንጽሕና ይዞ መገኘት ነው፡፡ስለዚህ እመቤታችን ቤዛ ናት ማለት የደቂቀ አዳምን ግብር ወክላ የተገኘች ስለደቂቀ አዳም ፋንታ በንጽሕና በቅድስና ቤዛ ሆነች ማለት ነው፡፡
#ቤዜነቷም፦
የንጽህና የቅድስና ቤዛነት
የድንግልና ቤዛነት
የመጽነስ ቤዛነት
የመውለድ ቤዛነት
የማሳደግ ቤዛነት
የመሰደድ ቤዛነት
የርሀብ የጽምእ ቤዛነት
የሕማም የመከራ ቤዛነት
የአቂበ ህግ ቤዛነት ከፍላለች፡፡
ቤዛ አበው ነቢያት
ቤዛ ጻድቃን ነገሥት
ቤዛ ንጹሃን ደናግል
ቤዛ ፍንዋን ሐዋርያት
ቤዛ ግፉዓን ጽድቃን
ቤዛ ከዓውያነ ደም ሰማዕት
ቤዛ ስዱዳን ባሕታውያን
ቤዛ ተላውያን ፸ አርድእት ናት፡፡
እኒህ ሁሉ አበው በእመቤታችን ቤዛነት የዳኑ ናቸው እንጂ በእነርሱ ሥራ አይደለም የእነርሱ መከራ ሰውነታቸውን እንደ ወርቅ ቢያጸራውም አምላክን ለመወሰን አለበቁም የእመቤታችን የንጽሕና ቤዛ ግን በማሕፀኑዋ እንድትወስነው አድርጉዋታል፡፡
"እውነት እላችኋለሁ፥ብዙዎች ነቢያትና ጻድቃን የምታዩትን ሊያዩ ተመኝተው አላዩም፥ የምትሰሙትንም ሊሰሙ ተመኝተው አልሰሙም።
ማቴ13:17::
"ሁላችን እንደ ርኩስ ሰው ሆነናል፥ጽድቃችንም ሁሉ እንደ መርገም ጨርቅ ነው፤ሁላችንም እንደ ቅጠል ረግፈናል፥በደላችንም እንደ ነፋስ ወስዶናል።
ትን.ኢሳ.64:6
ነቢያት ሁሉ የአዳም መርገም ወድቆባቸው ሥራቸው ሁሉ ለጽድቅ አላበቃቸው ብሎ ኑረዋል፡፡ እመቤታችን ግን የአበውን ሁሉ ጩኸት የፈጸመች የጩኸታቸው ቤዛ ሆነችላቸው ማለት ነው፡፡
እመቤታችን ቤዛዊተ ዓለም ማለት ከዓለም የሚያስፈልገውን ሥራ ይዞ መገኘት ነው፡፡
ይህን ቤዛነት አለመረዳት እጅግ አደጋ ነው፡፡
"ንትፌሣሕ ኩልነ በዝክረ ስምኪ ጥዑም ወበደመ ዮሐንስ መአድም ቅድስት ማርያም ቤዛዊተኩሉ ዓለም" ቅዱስ ያሬድ
"ኢትኅፈር ልደቶ እም ብእሲት እስመ ይእቲ ኮነተነ ምክንያተ ሕይወት አስተጋበአተነ ቅድስት ማርያም ዘይእቲ ንዋየ ድንግልና ዘአልቦ ሙስና ወይእቲ ዘዳግም አዳም ገነት እንተ መንፈስ ወይእቲ ጽምርተ ህላዌ ወይእቲ በዓለ መድኃኒት እንተ ተቤዘወነ ጽርኅ ንጽሕት እንተ ባቲ ተመርዐወ ቃል"
ተረ ቄር 18፡5
"ዮም ፍሥሓ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም እምሐና ወኢያቄም ከመ ተቤዙ ነቢያተ ወጸድቃነ አማን ተወልደት እመ ብርሃን"
ቅዱስ ያሬድ
"መጽአ ዐቃቤ ሥራይ እም ኀበ አብ እምጽርሐ አርያም መድኃኒት ተረክበት በሀገረ ዳዊት እንተ ስማ ጽዮን ወተፈጸመ ዘተብህለ መኑ ይሁብ መድኃኒተ እም ጽዮን"
መጽ ምሥ 20፡11:
#ቅዱስ ያሬድ፣አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፤ቅዱስ ቄርሎስ ቤዛዊተ ዓለም ካሏት እነዚህ አባት ቤዛዊተ ዓለም የማይሎት ከማን ወገን ሆነው ነው??
መልሱ ከንስጥሮስ ወገን መሆናቸው ነው፡፡
#እመቤታችን ለዓለም ሁሉ ብቸኛ ንጽሕት ዘርዕ ሆና ከጥፋት በመታደግ ለሁሉም ቤዛ ሆናለች፡፡
ጠቅለል ሲል እመቤታችን ንጹሕ አካሏን ለዓለም ቤዛ አድርጋ ለእግዚአብሔር አቅርባለች ነው፡፡
"የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ እንደ ሰዶም በሆንነ እንደ ገሞራም በመሰልነ ነበር::
ትን. ኢሳ. 1:9::
#እሰግድ ለንጽሕናኪ ወአስተበርክ ለድንግልናኪ ማርያም ድንግል ቤዛዊተ ነፍስየ ዘኮንኪ!!!
❖እናመልከው ዘንድ ለፈጠረን እግዚአብሔር ምስጋና ይግባው እንላለን!!!
❖አ.ዘ.ያዕቆብ፡፡
©ጌዴዎን ዘለዓለም::
በማኅበራዊ ሚድያ ሲዘዋወር አንድ አባት የተናገሩት ቢድዮ አየሁት፡፡ጥቂት ነገር ልበል፡፡
ቤዛ ምንድን ነው???
#ቤዛ፣ቤዛነት ማለት ስለ አንድ ነገር ምትክ መሆን ነው፡፡እመቤታችን ቤዛ ናት ማለት እግዚአብሔር ቃል ሰው እንዲሆን ከሰው ልጅ የሚጠበቅ ነገር አለ ይህም መርገመ አዳም ወሄዋን ያልወደቀበት ንጹሕ ዘርእ ነው፡፡
እመቤታችን ቤዛ የሆነችው ደቂቀ አዳም ይጠብቁት የነበረውን ንጽሕና ይዞ መገኘት ነው፡፡ስለዚህ እመቤታችን ቤዛ ናት ማለት የደቂቀ አዳምን ግብር ወክላ የተገኘች ስለደቂቀ አዳም ፋንታ በንጽሕና በቅድስና ቤዛ ሆነች ማለት ነው፡፡
#ቤዜነቷም፦
የንጽህና የቅድስና ቤዛነት
የድንግልና ቤዛነት
የመጽነስ ቤዛነት
የመውለድ ቤዛነት
የማሳደግ ቤዛነት
የመሰደድ ቤዛነት
የርሀብ የጽምእ ቤዛነት
የሕማም የመከራ ቤዛነት
የአቂበ ህግ ቤዛነት ከፍላለች፡፡
ቤዛ አበው ነቢያት
ቤዛ ጻድቃን ነገሥት
ቤዛ ንጹሃን ደናግል
ቤዛ ፍንዋን ሐዋርያት
ቤዛ ግፉዓን ጽድቃን
ቤዛ ከዓውያነ ደም ሰማዕት
ቤዛ ስዱዳን ባሕታውያን
ቤዛ ተላውያን ፸ አርድእት ናት፡፡
እኒህ ሁሉ አበው በእመቤታችን ቤዛነት የዳኑ ናቸው እንጂ በእነርሱ ሥራ አይደለም የእነርሱ መከራ ሰውነታቸውን እንደ ወርቅ ቢያጸራውም አምላክን ለመወሰን አለበቁም የእመቤታችን የንጽሕና ቤዛ ግን በማሕፀኑዋ እንድትወስነው አድርጉዋታል፡፡
"እውነት እላችኋለሁ፥ብዙዎች ነቢያትና ጻድቃን የምታዩትን ሊያዩ ተመኝተው አላዩም፥ የምትሰሙትንም ሊሰሙ ተመኝተው አልሰሙም።
ማቴ13:17::
"ሁላችን እንደ ርኩስ ሰው ሆነናል፥ጽድቃችንም ሁሉ እንደ መርገም ጨርቅ ነው፤ሁላችንም እንደ ቅጠል ረግፈናል፥በደላችንም እንደ ነፋስ ወስዶናል።
ትን.ኢሳ.64:6
ነቢያት ሁሉ የአዳም መርገም ወድቆባቸው ሥራቸው ሁሉ ለጽድቅ አላበቃቸው ብሎ ኑረዋል፡፡ እመቤታችን ግን የአበውን ሁሉ ጩኸት የፈጸመች የጩኸታቸው ቤዛ ሆነችላቸው ማለት ነው፡፡
እመቤታችን ቤዛዊተ ዓለም ማለት ከዓለም የሚያስፈልገውን ሥራ ይዞ መገኘት ነው፡፡
ይህን ቤዛነት አለመረዳት እጅግ አደጋ ነው፡፡
"ንትፌሣሕ ኩልነ በዝክረ ስምኪ ጥዑም ወበደመ ዮሐንስ መአድም ቅድስት ማርያም ቤዛዊተኩሉ ዓለም" ቅዱስ ያሬድ
"ኢትኅፈር ልደቶ እም ብእሲት እስመ ይእቲ ኮነተነ ምክንያተ ሕይወት አስተጋበአተነ ቅድስት ማርያም ዘይእቲ ንዋየ ድንግልና ዘአልቦ ሙስና ወይእቲ ዘዳግም አዳም ገነት እንተ መንፈስ ወይእቲ ጽምርተ ህላዌ ወይእቲ በዓለ መድኃኒት እንተ ተቤዘወነ ጽርኅ ንጽሕት እንተ ባቲ ተመርዐወ ቃል"
ተረ ቄር 18፡5
"ዮም ፍሥሓ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም እምሐና ወኢያቄም ከመ ተቤዙ ነቢያተ ወጸድቃነ አማን ተወልደት እመ ብርሃን"
ቅዱስ ያሬድ
"መጽአ ዐቃቤ ሥራይ እም ኀበ አብ እምጽርሐ አርያም መድኃኒት ተረክበት በሀገረ ዳዊት እንተ ስማ ጽዮን ወተፈጸመ ዘተብህለ መኑ ይሁብ መድኃኒተ እም ጽዮን"
መጽ ምሥ 20፡11:
#ቅዱስ ያሬድ፣አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፤ቅዱስ ቄርሎስ ቤዛዊተ ዓለም ካሏት እነዚህ አባት ቤዛዊተ ዓለም የማይሎት ከማን ወገን ሆነው ነው??
መልሱ ከንስጥሮስ ወገን መሆናቸው ነው፡፡
#እመቤታችን ለዓለም ሁሉ ብቸኛ ንጽሕት ዘርዕ ሆና ከጥፋት በመታደግ ለሁሉም ቤዛ ሆናለች፡፡
ጠቅለል ሲል እመቤታችን ንጹሕ አካሏን ለዓለም ቤዛ አድርጋ ለእግዚአብሔር አቅርባለች ነው፡፡
"የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ እንደ ሰዶም በሆንነ እንደ ገሞራም በመሰልነ ነበር::
ትን. ኢሳ. 1:9::
#እሰግድ ለንጽሕናኪ ወአስተበርክ ለድንግልናኪ ማርያም ድንግል ቤዛዊተ ነፍስየ ዘኮንኪ!!!
❖እናመልከው ዘንድ ለፈጠረን እግዚአብሔር ምስጋና ይግባው እንላለን!!!
❖አ.ዘ.ያዕቆብ፡፡
©ጌዴዎን ዘለዓለም::