በኢትዮጵያ ብሔራዊ ዲጂታል የጤና የመረጃ ቋት ለመዘርጋት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ!
በኢትዮጵያ ብሔራዊ የሆነ ዲጂታል የጤና የመረጃ ቋት ለመዘርጋት እየተሰራ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።ሚኒስቴሩ በኢትዮጵያ እየተስተዋለ ያለውን የተበታተነ የጤና መረጃ አያያዝ ማሻሻል አስፈላጊ መሆኑ እንደታመነበት ገልጿል።
ይዘጋጃል የተባለው የመረጃ ቋት የመድኃኒት አያያዝንና ቁጥጥርን ጨምሮ የበሽታ አይነቶች የሚመዘገቡበት እንዲሆን ውጥን መያዙን የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ገልጸዋል።
አክለውም፤ ዲጂታል የጤና መረጃ ለማደራጀት፣ ለመጠቀም እንዲሁም ወደ ዲጂታል አገልግሎቶች መግባት የሚችሉ የጤናው ዘርፍ ሥራዎችን በዲጂታል ለመተካት bጤና ሚኒስቴር በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ለአሐዱ ተናግረዋል።
ዲጂታል የጤና የመረጃ ቋት በተለያዩ ጊዜያቶች የሚፈጠሩ በሽታዎችን ለመለየት የሚያስችል መሆኑን የገለጹት ሚንስተሯ፤ የተያዘው ውጥን እንዲሳካ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በትብብር መስራት አስፈላጊ መሆኑን አሳስበዋል።
"የዲጂታል የጤና መረጃ ስርአት መዘርጋቱ የጤና አገልግሎት አሰጣጡን ለማቀላጠፍ ይረዳል፡፡" የተባለ ሲሆን፤ ስርዓቱ መረጃን በፍጥነት ተደራሽ ለማድረግ፣ እንግልትን ለመቀነስ እንዲሁም፤ ቶሎ ውሳኔ በመስጠት ወረርሽኝን ለመግታት እና ለመሳሰሉት አስፈላጊ መሆኑን ተነግሯል።በኢትዮጵያ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚከሰቱ በሽታዎች ዙርያ በሰነድ ደረጃ የሚያዝ መረጃ እንዳልነበረ ሲገለፅ ቆይቷል።
[Ahadu]
@YeneTube @FikerAssefa
በኢትዮጵያ ብሔራዊ የሆነ ዲጂታል የጤና የመረጃ ቋት ለመዘርጋት እየተሰራ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።ሚኒስቴሩ በኢትዮጵያ እየተስተዋለ ያለውን የተበታተነ የጤና መረጃ አያያዝ ማሻሻል አስፈላጊ መሆኑ እንደታመነበት ገልጿል።
ይዘጋጃል የተባለው የመረጃ ቋት የመድኃኒት አያያዝንና ቁጥጥርን ጨምሮ የበሽታ አይነቶች የሚመዘገቡበት እንዲሆን ውጥን መያዙን የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ገልጸዋል።
አክለውም፤ ዲጂታል የጤና መረጃ ለማደራጀት፣ ለመጠቀም እንዲሁም ወደ ዲጂታል አገልግሎቶች መግባት የሚችሉ የጤናው ዘርፍ ሥራዎችን በዲጂታል ለመተካት bጤና ሚኒስቴር በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ለአሐዱ ተናግረዋል።
ዲጂታል የጤና የመረጃ ቋት በተለያዩ ጊዜያቶች የሚፈጠሩ በሽታዎችን ለመለየት የሚያስችል መሆኑን የገለጹት ሚንስተሯ፤ የተያዘው ውጥን እንዲሳካ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በትብብር መስራት አስፈላጊ መሆኑን አሳስበዋል።
"የዲጂታል የጤና መረጃ ስርአት መዘርጋቱ የጤና አገልግሎት አሰጣጡን ለማቀላጠፍ ይረዳል፡፡" የተባለ ሲሆን፤ ስርዓቱ መረጃን በፍጥነት ተደራሽ ለማድረግ፣ እንግልትን ለመቀነስ እንዲሁም፤ ቶሎ ውሳኔ በመስጠት ወረርሽኝን ለመግታት እና ለመሳሰሉት አስፈላጊ መሆኑን ተነግሯል።በኢትዮጵያ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚከሰቱ በሽታዎች ዙርያ በሰነድ ደረጃ የሚያዝ መረጃ እንዳልነበረ ሲገለፅ ቆይቷል።
[Ahadu]
@YeneTube @FikerAssefa