4-3-3 World News


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


ይህ የእርሶ፣ የአንተ፣ የአንቺ፣ የእናንተ፣ የኛ የሁላችንም ድምጽ ነው! ለሃሳብ አስተያየት ለመስጠት @atsbaha12 ይጠቀሙ

Related channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


አዲሱ ፖስፖርት ዛሬ ይፋ ተደረገ

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አዲስ ዘርጋሁት ባለው የኢ-ፓስፖርት ሲስተም በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስና በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ የሚስጥራዊ ህትመትና ቴክኖሎጂ ልምድ አለው ከተባለው የጃፓኑ ቶፓን ሴኩሪቲ ኢትዮጵያ አ.ማ አማካይነት ዘመኑ በደረሰበት የሚስጥራዊ ህትመት የታተመ አዲስ ፖስፖርት ዛሬ የካቲ 14 ቀን 2017 ዓ.ም በሳይንስ ሙዚየም ይፋ እያደረገ ነው፡፡

@Ethionews433
@Ethionews433


በዋሽንግተን ዲሲ አንድ ኢትዮጵያዊ በጥይት ተመቶ ተገደለ፡፡ የ29 አመቱ ሱራፌል ዘላለም ሊገደል የቻለው ከፖሊስ ጋር በተፈጠረ ግብግብ መሆኑ ተገልጿል፡፡ ማክሰኞ እለት መኪናውን እያሽከረከረ እያለ ከተቃራኒ አቅጣጫ ከሚመጣ የፖሊስ መኪና ጋር መጋጨቱን ዘገባዎች ጠቁመዋል፡፡

ከዚያ በኋላ ፖሊስ እንደገለፀው ሱራፌል ወደፖሊሶቹ መኪና በመሄድ ቢላ በማውጣት ያስፈራራቸው ሲሆን ማስጠንቀቂያም ሰጥተውት ነበር፡፡ ይሁንና ማስጠንቀቂያውን ባለመስማቱ ተኩሰው አንደኛው ፖሊስ ሽጉጥ ተኩሶ እንደገደለው ተገልጿል፡፡ ይህ ድርጊት በሚፈፀምበት ወቅት ከሱራፌል አጠገብ አንዲት ሴት ተቀምጣ የነበረ ሲሆን ምንም ጉዳት እንዳልደረሰባት ፖሊስ አስታውቋል፡፡

ግድያውን የፈፀሙት ፖሊሶች በግዳጅ እረፍት እንዲወጡ መደረጉን የዲሲ ፖሊስ ገልጿል፡፡ በፖሊሶቹ ላይ የተገጠመውን ካሜራ በመመልከት የግድያው መንስኤ እንደሚጣራ ፖሊስ ገልፆ መረጃ ያለው ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርቧል፡፡(ዘ-ሐበሻ ዜና)

@Ethionews433 @Ethionews433


ህዝባዊ ቁጣ በእስራኤል!

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ህዝባዊ ቁጣ ተቀሰቀሰባቸው፡፡

አራት እስራኤላውያን ታጋቾ አስከሬናቸው ከጋዛ መመለሱን ተከትሎ ነው በኔታያንሁ እና መንግስታቸው ላይ ህዝባዊ ተቃውሞ የተቀሰቀሰው ፡፡

የፍልስጤሙ ሀማስ ሺሪ ቢባስ እና ሁለት ልጆቿን እንዲሁም ኤዴድ ሊፍሽዝ የተባለ ግለሰብ አስከሬን በደቡባዊ ጋዛ ኻን የኑስ ማስረከቡን አሳውቋል፡፡

ሀማስ ተጋቾቹ የሞቱት በእስራኤል የቦምብ ጥቃት ነው ሲል ለቀረበበት ወቀሳ ማስተባበያ እንደሰጠ ተዘግቧል ፡፡

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ከጋዛ ለተመለሱት አስከሬኖች በሚደረገው የቀብር ስነ ስርዓት ላይ ለመገኘት ቀጠሮ ይዘው የነበረ ቢሆንም በመጨረሻው ደቂቃ ሀሳባቸውን ቀይረዋል ሲል ከእስረኤሉ ቻናል 12 ያገኘውን መረጃ ጠቅሶ የዘገበው አናዶሉ ነው፡፡

በ- ቶማይ መኮንን

@Ethionews433 @Ethionews433


ሩሲያ የአውሮፓ ሀገራት በዩክሬን የሰላም አስከባሪ ጦር ለማሰማራት ማቀዳቸውን አጥብቃ ተቃወመች

ክሪምሊን ባወጣው መግለጫ በሩስያ ድንበር ላይ የሚደረግ የማንኛውም የኔቶ አባል ሀገር ወታደራዊ እንቅስቃሴ አልቀበልም ብሏል።

የክሪምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ በዛሬው ዕለት በሰጡት መግለጫ ሀገራቸው ጉዳዩ እንደሚያሳስባት እና በቅርበት እየተከታተለችው እንደምትገኝ ገልጸዋል፡፡

የብሪታኒያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኪር ስታርመር በሞስኮ እና በኪየቭ መካከል የተኩስ አቁም ስምምነት ሲደረግ እንደ የደህንነት ዋስትና የብሪታንያ ወታደሮችን በዩክሬን መሬት ላይ ለማስፈር ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል ።

@Ethionews433 @Ethionews433


የትራምፕ ህገወጥ ስደተኞችን የማፈናቀል ፖሊሲ በአሜሪካ ኢኮኖሚ ላይ ችግር መፍጠሩ ተነገረ

ዶናልድ ትራምፕ የፕሬዝዳንትነት ስልጣን በያዙ ከአንድ ወር ባነሰ ጊዜ ውስጥ ፕሬዝዳንቱ የድንበር ደህንነትን ለመቆጣጠር ባደረጉት ሙከራ ከ8,700 በላይ ህጋዊ ሰነድ የሌላቸው ስደተኞች ከአሜሪካ ተባርረዋል። የትራምፕን እርምጃ በመቃወም በመላው የአሜሪካ ከተሞች ሰፊ ተቃውሞ ቢደረግም ስደተኞችን ወንጀለኞች በማለት ይፈርጃሉ። አስደንጋጭ በሆነው እርምጃ የትራምፕ አስተዳደር በስደተኞች ጉዳይ ላይ ውሳኔ የመስጠት ኃላፊነት የነበራቸው 20 የኢሚግሬሽን ዳኞችን ኃላፊነታቸውን አልተወጡም በማለት በቅርቡ ከስራ አሰናብተዋል።

ይህው እርምጃ ቤተሰቦች እንዲለያዩ እና ህጻናት ያለ ምንም የድጋፍ ስርዓት በማስቀረት ከ3 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ሰነድ አልባ ስደተኞች እጣ ፈንታ በእርግጠኝነት አይታወቅም።የጥገኝነት ጉዳዮች ለመታየት እና ለመጨረስ አመታትን ሊወስድ ይችላል፣ እናም ብዙ ሰነድ የሌላቸው ስደተኞች የኢሚግሬሽን እና የጉምሩክ ማስፈጸሚያ ህጋዊ ሂደታቸውን እንዲቆም እና ቤተሰቦቻቸው ሊለያይ ይችላል በሚል ፍራቻ ስራ እና ትምህርት ቤት ለመቅረት እየተገደዱ ይገኛል።

የስደተኞች ጠቀሜታ እና አስተዋፅዖ በአጠቃላይ በአሜሪካ የሰው ኃይል ውስጥ የማፈናቀል ዘመቻው በኢኮኖሚው ላይ የሚኖረውን አሉታዊ ተፅእኖ የከፋ እንደሚሆን የኢኮኖሚ ተንታኞች ስጋታቸውን ያስቀምጣሉ። ዩናይትድ ስቴትስ በስደተኛ እና በተለይም ሰነድ አልባ በሆኑ ዜጎች ጉልበት ላይ የተደገፈች ነች።ስደተኞች የኢኮኖሚው ምሰሶ በመሆናቸው  ወደ ስራ መግባት ትተው መደባበቅ መጀመራቸው ችግሩ አፍጥጦ እንደሚታይ ያሳያል ብለዋል።

በስምኦን ደረጄ

@Ethionews433 @Ethionews433


ኤርትራ በአዲስ አበባ ያለውን ኤምባሲዋን እየዘጋች መሆኑ ታወቀ

ካለፉት ሁለት አመታት ወዲህ ግንኙነታቸው እየሻከረ የመጣው የኢትዮጵያ እና ኤርትራ መንግስታት የቃላት ጦርነት መጀመራቸውን ተከትሎ ኤርትራ በአዲስ አበባ የሚገኘውን ኤምባሲዋን እየዘጋች መሆኑ ታውቋል።

የዛሬ ሰባት አመት ገደማ ግንኙነታቸውን ያደሱት ሁለቱ ሀገራት በትግራይ የተካሄደው ደም አፋሳሽ ጦርነት ላይ በጋራ ቆመው ቢዋጉም የፕሪቶሪያው ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ ግንኙነቱ መሻከር መጀመሩ ይታወሳል።

"ኤምባሲው ከዚህ በኋላ የአፍሪካ ህብረት ተወካዩን ይዞ ይቀጥላል፣ በኢትዮጵያ ያለውን የኤምባሲ ስታፍ ግን እያሰናበተ ነው" ያሉን አንድ የኤምባሲው ምንጫችን ሂደቱ በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን ለመሠረት ሚዲያ መናገራቸውን ዳጉ ጆርናል ከዜና ምንጩ ዘገባ ተመልክቷል።

ከቀናት በፊት የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ የኤርትራ መንግስት የአፍሪካ ቀንድን የማተራመስ አላማ ይዞ እየተንቀሳቀሰ ነው፣ በአስቸኳይ እንዲቆም መደረግ አለበት በማለት አልጀዚራ ላይ በቀረበ ፅሁፋቸው አስነብበው ነበር።

የኤርትራው የኢንፎርሜሽን ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረመስቀል ለዚህ ምላሽ የሰጡ ሲሆን የፕሬዝደንቱን አስተያየት አጣጥለው የኢትዮጵያን መንግስት የቀጠናውን ሀገራት በመተንኮስ ከሰዋል።

የኤርትራ ኤምባሲ መዘጋት መጀመርን ተከትሎ በአስመራ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ እጣ ፈንታ እስካሁን አልታወቀም። ላለፉት ጥቂት አመታት ኤምባሲው ክፍት ቢሆንም አምባሳደር ሳይመደብበት መቆየቱም ይታወሳል።

Via መሠረት ሚዲያ

@Ethionews433 @Ethionews433


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


ዛሬ በካራቆሬ አጃንባ ኮንደሚኒየም ከፍሎ በሚገኘው ተራራ ላይ ከባድ የተባለ ሰደደ እሳት ተነስቷል።


አዲሱ የአፕል አይ ኦ ኤስ (iOS) 18.3 ሶፍትዌር

አይፎን ተጠቃሚዎቹ ያለ ኢንተርኔት ዳታ ወይም ያለ ዋይፋይ የጹሁፍ መልዕክት ለመላላክ የሚችሉበትን አይ ኦ ኤስ (iOS) 18 ነጥብ 3 የተባለ ሶፍትዌር አስተዋውቋል።

ይህ አዲሱ ሶፍትዌር በአይፎን 14 እና ከሰሱ በኋላ በተሰሩ በሁሉም የአይፎን ሞዴሎች ይሰራል ተብሏልለ።

ተጠቃሚዎች የኢንተርኔት ዳታ እና ዋይፋይ በማይሰራባቸው ቦታዎች ሆነው ሳተላይት ብቻ በመጠቀም የጽሑፍ መልእክት፣ ኢሞጂዎችን ለመቀበል እና ለመላክ ያስችላቸዋል ተብሏል።

አፕል በቅርብ የአይ ኦ ኤስ (iOS) 18 ነጥብ 3 ማሻሻያን የስታርሊንክ ሳተላይት ቴክኖሎጂን ወደ አይፎን በማካተት የሞባይል ግንኙነቱን ቀይሯል።

ይህ ስራ በስፔስ ኤክስ እና ቲ-ሞባይል መካከል በተደረገው ትብብር አማካኝነት የተሰራ ሲሆን ወደ ፊትም ፎቶዎችን፣ ሙዚቃዎችን እና ቪዲዮዎችን መላላክ የሚችሉበትን መንገድ ለማካተት ታቅዷል።

አዲሱ ስምምነት አፕል በግሎባልስታር ላይ ካለው የረዥም ጊዜ ጥገኝነት ሲወጣ የመጀመሪያው ሲሆን ወደፊት ለሚደረጉ የሞባይል ግንኙነት የበለጠ እንዲሚያጠናከር ፍንጭ የሚሰጥ መሆኑ ተመላክቷል።

የመልዕክት ሳተላይቱ በአሜሪካ እና ካናዳ አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን የአይፎን 14 እና ከሱ በኋላ ባሉ በሁሉም ሞዴሎች ላይ ይሰራል ተብሏል። ሶፍትዌሩ ስልክ ላይ ከተጫነ በኋላ ደንበኞች ለሁለት ዓመት ያህል በነፃ መጠቀም እንደሚችሉም ከአፕል ድረገፅ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

አዲሱ አሰራር ተግባራዊ መሆኑን ተከትሎ የግሎባልስታር አክሲዮኖች በ11 በመቶ እንዲቀንስ ማድረጉን ተዘግቧል።

@Ethionews433 @Ethionews433


ቴል አቪቭ-ሐማስ ከሚለቃቸዉ ታጋቾች አንዱ ኢትዮጵያዊ-እስራኤላዊ ነዉ

እስራኤልና ምዕራባዉያን መንግሥታት በአሸባሪነት የሚወነጅሉት የፍልስጤም ደፈጣ ተዋጊ ቡድን ሐማስ በቅርቡ ከሚለቃቸዉ ታጋቾች አንዱ ኢትዮጵያዊ-እስራኤላዊ ነዉ። እስራኤልና ሐማስ ባለፈዉ ጥር ባደረጉት ሥምምነት መሠረት በመጀመሪያዉ ዙር ከተለቀቁና ከሚለቀቁ ታጋቾች 6ቱ በመጪዉ ቅዳሜ ይለቀቃሉ ተብሎ ይጠበቃል። ከሥድስቱ ታጋቾች አንዱ ኢትዮጵያዊ-እስራኤላዊ አቬራ መንግሥቱ ነዉ።አቬራ መንሥቱ እንደ ሌሎቹ ታጋቾች ሐማስ መስከረም 29፣ 2016 ደቡባዊ እስራኤልን በወረረበት ወቅት የታገተ አይደለም።ጀሩሳሌም ፖስት የተባለዉ የእስራኤል ጋዜጣ ምንጮችን ጠቅሶ ባለፈዉ ጥር በኢንተርኔት እንደዘገበዉ የ38ት ዓመቱ ጎልማሳ እንደ ግሪጎሪያኑ አቆጣጠር መስከረም 7፣2014 በራሱ ፈቃድ ጋዛ ገብቶ እጁን ለሐማስ ሰጥቷል።በዘገባዉ መሠረት ያኔዉ የ28 ዓመት ወጣት የእስራኤል ወታደር እንደነበር ሐማስ አስታዉቋል።ይሁንና ሑዩማን ራይትስ ወች የተባለዉ የመብት ተሟጋች ድርጅትና ቤተሰቦቹ የሐማስን አባባል አልተቀበሉትም።ወጣቱ የአዕምሮ ሕመምተኛ ነዉ ይባላል።ጋዛ ከመግባቱ በፊት ከእናቱ ጋር ተጣልቶ እንደነበረም ጋዜጣዉ የመብት ተሟጋቹን ድርጅት ጠቅሶ ዘግቧል።(DW)

@Ethionews433 @Ethionews433


ናይሮቢ-ጎማ ከተማ ዉስጥ በተደረገ ዉጊያ ከ5000 በላይ ሰላማዊ ሰዉ ተገድሏል-መንግስት

የምሥራቃዊ ኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ትልቅ ከተማ ጎማ ዉስጥ በተደረገ ዉጊያ በትንሹ 5000 ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸዉን የሐገሪቱ መንግሥት አስታወቀ።የጎማ ከተማን ላለማስያዝና ለመያዝ የኮንጎ መንግስት ጦር፣የአፍሪቃ መንግስታት፣የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ወታደሮችና በሩዋንዳ የሚደገፈዉ የM23 አማፂያን ባለፉት ሳምንታት ከፍተኛ ዉጊያ ሲያደርጉ ነበር።የኪንሻ መንግሥት የሩዋንዳ ወታደሮች ከአማፂዉ ቡድን ጋር አብረዉ ተካፍለዉበታል ባለዉ ዉጊያ በትንሹ 5000 ሰዎች መገደላቸዉን ትናንት ማታ አስታዉቋል።የኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ መንግሥት ቃል አቀባይ ፓትሪክ ሙያያ እንዳሉት እስከ ትናንት ድረስ 5000 ሰዎች መቀበራቸዉን መንግስታቸዉ ከተለያዩ ምንጮች አረጋግጧል።ይሁንና የሐገሪቱ የጤና ሚንስቴር የሆስፒታል ምንጮችን ጠቅሶ እንደዘገበዉ የሟቾቹ ቁጥር 8000 ሊደርስ ይችላል።የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በቅርቡ ባወጣዉ መግለጫ ግን የ2900 ሰዎች አስከሬን ማግኘቱን አስታዉቋል።አማፂዉ ቡድን ጎማን ከተቆጣጠረ በኋላ በመቶ ሺሕ የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ተፈናቅለዋል፤ እስረኞች ተለቅቀዋል፣ የመንግስት፣ የድርጅቶችና የግል ንብረቶች ተመዝብረዋል።ጦርነቱ ዛሬም በተለይ ኖርድ ኪቩ በተባለዉ ግዛት መቀጠሉ ተዘግቧል።(DW)

@Ethionews433 @Ethionews433


እሳቱ በቁጥጥር ስር ውሏል ....!

@Ethionews433 @Ethionews433


ለቻይና ድርጅቶች መረጃ አሳልፎ በመስጠት የተጠረጠረው ዲፕሲክ

የደቡብ ኮርያው የግል መረጃ ጠባቂ ኮሚሽን የቻይናውን የሰው ሰራሽ አስተውሎት ድርጅት ዲፕሲክን የተጠቃሚዎችን የግል መረጃ አሳልፎ እየሰጠ ነው ሲል ወንጅሎታል።

መረጃውንም ለቻይናው ለቲክቶክ እናት ኩባንያ ባይትዳንስ አሳልፎ እንደሰጠ ገልጿል።

ዲፕሲክ ከባይትዳንስ ጋር ግንኙነት መፍጠሩን ደርሼበታለሁ ያለው የደቡብ ኮርያው የግል መረጃ ጠባቂ ኮሚሽን በትክክል ምን ዓይነት እና ምን ያህል መረጃዎች እንደተጋሩ ግን አልገለጸም።

ደቡብ ኮርያ ዲፕሲክን ያገደች ሲሆን ምክንያቷም ከግል መረጃ ደህንነት ጋር በተያያዘ መሆኑን አስታውቃለች።

አውስትራሊያ እና ታይዋንም ዲፕሲክን በመንግስት ተቋማት የኤሌክትሮኒክስ መገልገያዎች ላይ መጠቀም የከለከሉ ሀገራት ሆነዋል።

አንድ የአሜሪካ የሳይበር ደህንነት ድርጅትም ዲፕሲክ ከባይትዳንስ ጋር ቀጥተኛ የሲስተም ግንኙነት እንዳለው ማስረጃ ማግኘቱን አስታውቋል። በዚህም ዲፕሲክ ለባይትዳንስ ብቻ ሳይሆን ለሌሎች የቻይና ድርጅቶች ጭምር መረጃ አሳልፎ ሳይሰጥ እንደማይቀር ጠቁሟል።

ዲፕሲክ ይፋ በተደረገበት የጥር ወር ላይ በርካታ ተጠቃሚዎች ያገኘ እና በአጭር ጊዜ ውስጥ ገበያውን ያነቃነቀ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ነው።

በደቡብ ኮርያ ከመታገዱ በፊት ከአንድ ሚሊየን ጊዜ በላይ ሰዎች ያወረዱት የሰው ሰራሽ አስተውሎት ነበር።


5ተኛ ተጨምሯል የአሳት አጥፊ መኪና




4ተኛ ተጨምሯል .....


3 የእሳት አደጋ ደርሷል .....

@Bisrat_Sport_433et @Bisrat_Sport_433et


ከአየር ጤና አከባቢ ጭሱ 📸

@Bisrat_Sport_433et @Bisrat_Sport_433et


ግራር ልዩ ቦታው ናትራን ፕላስቲክ ማከፋፈያ(ቤተሰብ አካዳሚ) አከባቢ የአሳት አደጋ ተነስቷል !📸

@Bisrat_Sport_433et @Bisrat_Sport_433et


Forward from: 4-3-3 ስፖርት በኢትዮጵያ™
💐💐💐💐የካቲት 12💐💐💐💐

ልክ በዛሬዋ ቀን ከ88 ዓመታት በፊት፥ የካቲት 12 የጣሊያን የቀድሞ ጀነራል ሩዶልፎ ግራዚያኒ ለይ በተደረገ የግድያ ሙከራ በቀል በማለት

በ3 ቀን ውስጥ 30,000 የሚሆኑ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎችን በተለይም ምሁሮችን እያስለቀመ ያስፈጀው።

እንኳን ለ88ኛው የየካቲት 12 ሰማዕታት መታሰቢያ ቀን አደረሳችሁ!

@Bisrat_Sport_433et @Bisrat_Sport_433et

20 last posts shown.