4-3-3 World News


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


ይህ የእርሶ፣ የአንተ፣ የአንቺ፣ የእናንተ፣ የኛ የሁላችንም ድምጽ ነው! ለሃሳብ አስተያየት ለመስጠት @atsbaha12 ይጠቀሙ

Related channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


396 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 396 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡ ተመላሾቹ 315 ወንዶች፣ 71 ሴቶች እና 10 ጨቅላ ሕጻናት ሲሆኑ÷ ከእነዚህ መካከልም 15 ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡

ለተመላሽ ዜጎች ተገቢውን ድጋፍ የማድረግና ከቤተሰብ ጋር የማቀላቀል ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝም የሴቶችና ማህበራዊ አገልግሎት ገልጿል።FBC

@Ethionews433 @Ethionews433


1618424833639.xlsx
309.0Kb
በዲግሪ ፕሮግርም መማር የምትፈልጉት የትምህርት አየነት እና ትምህርቱ የት እንደሚሰጥ የሚጠቁም ፋይል ነው !

ተጠቀሙበት !

@Ethionews433 @Ethionews433


የሰንደቅ ዓላማ ቀን ዛሬ ይከበራል

17ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን ዛሬ በመላ ሀገሪቱ ተከብሮ ይውላል፡፡

የሰንደቅ ዓላማ ቀን የጥቅምት ወር በገባ በመጀመሪያው ሳምንት ሰኞ እንደሚከበር ይታወቃል፡፡

17ኛው ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን ሀገራዊ ይዘት ባላቸው የተለያዩ መልዕክቶች ይከበራል፡፡

ከመልዕክቶቹ መካከልም÷ ሰንደቅ ዓላማችን ለብሔራዊ አንድነታችንና ሉዓላዊነታችን፣ ሰንደቅ ዓላማችን የኅብረ-ብሔራዊነታችን ማሳያ፤ የአንድነታችን የጋራ ዓርማ፣ ሰንደቅ ዓላማችን የኅብረ-ብሔራዊ አብሮነታችን ዋስትና ነው እና ሰንደቅ ዓላማችን የሉዓላዊነታችን መገለጫ ነው የሚሉት ይገኙበታል፡፡

በተጨማሪም ኢትዮጵያ ምንም እንኳ ወቅታዊ ፈተና ቢያጋጥማትም አሸንፋ ትሻገራለች፣ በልጆቿ መስዋዕትነት የኢትዮጵያ አንድነት ፀንቶ ይቀጥላል፣ ጀግናው የሀገር መከላከያ ሰራዊታችን የሉዓላዊነታችን አርማ ነው እንዲሁም ሰንደቅ ዓላማችን ለጠንካራ ሀገረ መንግስት ግንባታ የሚሉት ከ17ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን መልዕክቶች መካከል ይገኙበታል፡፡

@Ethionews433 @Ethionews433


በትራምፕ የምርጫ ቅስቀሳ አቅራቢያ ሁለት ሽጉጥና ሐሰተኛ ፓስፖርት ይዞ የተገኘው ግለሰብ ታሰረ!

ዶናልድ ትራምፕ በካሊፎርኒያ የምርጫ ቅስቀሳ እያደረጉ ባሉበት መድረክ አቅራቢያ ሁለት ያልተመዘገቡ ሽጉጦች ይዞ ተገኝቷል የተባለው ግሰለብ በቁጥጥር ሥር መዋሉን ፖሊስ ገለፀ።የ49 ዓመቱ ተጠርጣሪ ቬም ሚለር ጥቁር መኪና እየነዳ ሳለ ነው በፖሊስ እንዲቆም ታዞ ፍተሻ የተደረገበት። ፖሊስ ከመኪናው ውስጥ ሁለት ሽጉጥ እና “ብዙ ጥይቶች ያሉት ካርታ” ማግኘቱን ይፋ አድርጓል።

በቁጥጥር ሥር የዋለው ግለሰብ ምርመራ እየተደረገበት እንደሆነ የአካባቢው ፖሊስ ኃላፊ አሳውቀዋል።የአሜሪካ የደኅንነት መሥሪያ ቤት ሲክሬት ሰርቪስ ግለሰቡ ለትራምፕ “አደጋ የሚሆን አይደለም” ብሎ ምንም ዓይነት ግርግር እንዳልተፈጠረ አስረድቷል።

የአካባቢው ፖሊስ በቁጥጥር ሥር የዋለውን ግለሰብ “ወፈፌ” ሲሉ የገለፁት ሲሆን የትራምፕ ምርጫ ቅስቀሳ ታዳሚዎች ላይ ምንም ዓይነት ጉዳት አልደገነም ብለዋል።

ነገር ግን አሁንም በርካታ ጥያቄዎች ምላሽ አላገኙም።የሪቨርሳይድ ክፍለ ግዛት ፖሊስ ኃላፊ ተጠርጣሪው ምን ዕቅድ እንደነበረው ማወቅ ከባድ ቢሆንም ግለሰቡ ግን ፖሊስ ፕሬዘደንቱን ከሶስተኛ የግድያ ሙከራ እንደታደጋቸው ነው “የሚያምነው” ይላሉ።

ግለሰቡ በቁጥጥር ሥር የዋለው በአካባቢው ሰዓት አቆጣጠር ከሰዓት 11፡00 ሲሆን ትራምፕ የምርጫ ቅስቀሳ ለማድረግ አንድ ሰዓት ቀርቷቸው ነበር።የአሜሪካ ምርጫ ድምፅ መስጫ ቀን ሶስት ሳምንታት ይቀሩታል። በየቦታው እየዞሩ የምረጡኝ ቅስቀሳ እያደረጉ የሚገኙት ዶናልድ ትራምፕ ከባድ የሚባል ጥበቃ እየተደረገላቸው ነው።

[BBC]

@Ethionews433 @Ethionews433


ቤተክርስቲያን ልጆቿን ሸለመች !

በ2016 ዓ.ም 12ተኛ ክፍል ላጠናቀቁ ተማሪዎች የአደራ እና የሽኝት መረሃግብር ተካሄደ !

ካደጉበት ማህበረሰብ ለቀው አዲስ የህይወት ምዕራፍ ለመጀመር ወደ ተለያዩ የሀገራችን ክፍል ለትምህርት ለሚሰማሩ ተማሪዎች የግቢ ህይወት ምን ይመስላል ፣ ምንስ ማድረግ ይገባል የሚሉት ነገሮች ለተጓዥ ተማሪዎች ተሞክሮ የተሰጠ ሲሆን

ከፍተኛ ውጤት ላመጡ ተማሪዎችም ዘመኑን የዋጀ ላፕቶፕ ሽልማት የተበረከታለቸው ሲሆን በቦታው ለተገኙ ሁሉም ተማሪዎች የፀሎት መፀሃፍ በአደራ መልክ ተሰጥቷል።

በመንበረ ፀባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል በተደረገው የአደራ እና የሽኝት መረሃ ግብር ላይ ብፁዕ አቡነ ፍሊጶስ የተገኙ ሲሆን

ተማሪዎች በሁለት ቦታ የተሳለ ሰይፍ ሊሆኑ እንደሚገባቸው በማሳሰብ ቃለምዕዳን እና ቡራኬን በመስጠት መረሃ ግብሩ ተጠናቋል።

433 world newsም ሁነቱን ቦታው ድረስ በመሄድ የተከታተለ ሲሆን ዝርዝሩን ማታ 2 ሰዓት በሰፊው ይዘን እንቀርባለን!

@Ethionews433 @Ethionews433


ውሽት አየደለም !

ፋይሉ የ 2021 ነው ይሄ ማለት ከሶስት ዓመት በፊት የተሰራ ነው ይሁን እንጂ በአከባቢው የምናገኛቸው ነገሮች በዘርዝር ተቀምጠዋል ልዩነቱ ዋጋው ነው ከ ከ3መት በፊት 20 ወይም 30 ከነበረ አሁን ባለው የገብያ ምህዋር ቢያንስ 80-90 ይሆናል በዛ ትምኑት።

እና አንዳንድ ግቢዎች ላይ እማይሰጡ የነበሩ ኮርሶች አሀን ላይ አንዳንዱ ላይ የተጨመሩ አሉ እሱን ቡኋላ ላይ update እናደርጋቸዋለን።

ከዛ በተረፈ አሪፍ info የሚሰጥ ፋይል ነውነውተ ዋጋው ላይ እናንተ ብቻ ይዘቱን ከሁን ካለው ጋር ለማቀራረብ ሞክሩ።

@Ethionews433 @Ethionews433


የግል_ከፍተኛ_ትምህርት_ተቋማትና_እውቅና_ፈቃድ_የተሰጣቸው_የትምህርት_መስኮች.pdf
6.0Mb
ዕውቅና ያገኙ የግል ኮሌጆች እና የመንግስት ተቋማት !

የእውቅና ፈቃድ ባልታደሰባቸው የትምህርት መስኮች #አዲስ_ተማሪ_መቀበል_እንዳይችሉ ተደርጎ የተዘጋጀ ነው፡፡

በሂደት ላይ ያሉ የእውቅና ፈቃድ እና የእውቅና ፈቃድ እድሳት ጥያቄዎች ውሳኔ ሲያገኙ እንዲሁም በተለያዩ ምክንያቶች የእውቅና ፈቃድ ሲሰረዝና በሌሎች ምክንያቶች የውሳኔ ለውጦች በሚኖሩበት ወቅት የመረጃ ለውጥ ሊኖር ይችላል።

በመሆኑም ፦
- ተማሪዎች፣
- ወላጆች፣
- ቀጣሪና የሙያ ፈቃድ የሚሰጡ ድርጅቶች ፣
- የሚዲያና ማስታወቂያ ተቋማት ፣ እንዲሁም መላው ህብረተሰብ የተቋማቱን ወቅታዊ መረጃ በመከታተል ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ጥብቅ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

ተቋማት ይፋ ከተደረገው የእውቅና ፈቃድ መረጃ ውጪ ተማሪ ተቀብለው ቢያስተምሩ ህጋዊ እና አስተዳደራዊ እርምጃ ይወሰድባቸዋል።

[ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና እውቅና ፈቃድ የተሰጣቸው የትምህርት መስኮች ከላይ በ #PDF ተያይዟል ]

@Ethionews433 @Ethionews433

9k 0 91 8 15

መረጃ_ስለ_ሁሉም_ዪኒቨርሲቲዎች_@QesemAcademy.pdf
1.0Mb
በቀጥታ እና በሬሜዲያል ፕሮግራም ትምህርታቹን በግልም ሆነ በመንግስት ዩንቨርሲቲ ለምተከታተሉ በሙሉ !

የ ዩንቨርስቲ መሙያ ቀን ዛሬ መሆኑ ይታወቃል ይህንን ተከትሎ የት የት ልሙሉ ብላቱ ሀሳብ ለገባቹ ሰለ ሁሉም ዩንቨርስቲ በቂ መረጃ የያዛ ፋይል ለቀንላቹዋል ከፍታቹ መመልከት ትችላላቹ።

@Ethionews433 @Ethionews433

10.3k 0 314 35 46

የሚኖርበት ቤት ለልማት በሚል የፈረሰበት እና ስራ እንዳይሰራ የተከለከለ ወጣት ራሱን አጠፋ 💔

ነዋሪነቱ አዲስ አበባ ኡራኤል አካባቢ የሆነ አዲሱ ካሳሁን የተባለ ወጣት ከኡራኤል ቤተክርስቲያን ወደ አትላስ ሆቴል በሚወስደው መንገድ አካባቢ በሚገኘው 'በፀጋህ ሆስፒታል' ፊት ለፊት ነዋሪ ሲሆን ከትናንት በስቲያ ራሱን አጥፍቷል።

አዲሱ ነጠላ ከሚሸጥበት ኡራኤል ቤተከርስቲያን አካባቢ ስራ እንዳይሰራ ሁለት ግዜ በደንብ አስከባሪዎች ተባሮ እና ንብረቱም ተወስዶበት እንደነበር የአካባቢው ነዋሪዎች እና የቅርብ ሰው ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።

ከዚህም በተጨማሪ ከትናንት በስቲያ ምሽት ማታ ወደ ቤቱ ሲገባ የሚኖርበት ቤት በነጋታው ጠዋት እንደሚፈርስ ሲነገረው ተስፋ በመቁረጥ ስሜት እዛው ቤቱ ውስጥ ራሱን እንዳጠፋ ለመሠረት ሚድያ ከአካባቢው ነዋሪዎች የደረሰው ጥቆማ ያሳያል።

የልጅ አባት የሆነው እና በቅርቡ የወለደች ባለቤት ያለው ወጣቱ ይህን ድርጊት ከፈፀመ በኋላ ትናንት ስድስት ሰአት ላይ በኡራኤል ቤተክርስቲያን ቀብሩ እንደተፈፀመ ሰምተናል።

4-3-3 WORLD NEWS ለወዳጅ ዘመዶቹ እንዲሁም ለቤተሰቦቹ መጽናናትን ይመኛል።

[መሠረት ሚድያ]

@Ethionews433 @Ethionews433

8.6k 0 21 65 358

ፕሬዝዳንት ኤርዶሃን እስራኤል የዓለማችን ዋነኛ ስጋት ነች አሉ

ሩሲያ እና ኢራን በእስራኤል ላይ እርምጃ እንዲወስዱ ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል
ፕሬዝዳንት ኤርዶሃን እስራኤል የዓለማችን ዋነኛ ስጋት ነች አሉ፡፡

በመካከለኛው ምስራቅ የተጀመረው ጦርነት አንድ ዓመት ያለፈው ሲሆን ጦርነቱ በድርድር ይፈታል ቢባልም አድማሱን እያሰፋ ቀጥሏል፡፡

የቱርክ ፕሬዝዳንት ረሲብ ጣይብ ኤርዶሃን እንዳሉት እስራኤል የመካከለኛው ምስራቅ እና የዓለማችን ሰላም ዋነኛ ጠላት ናት ብለዋል፡፡

ፕሬዝዳንቱ አክለውም እስራኤል በሶሪያ በተደጋጋሚ ጥቃት እየፈጸመች መሆኗን ተናግረው በቅንጅት ሊያስቆሟት ይገባል ሲሉም ተናግረዋል፡፡
በሶሪያ ዘላቂ ሰላም እንዲመጣ ኢራን፣ ሶሪያ እና ሩሲያ የተቀናጀ ጥቃት በመክፈት ሊያስቆሟት ይገባልም ብለዋል፡፡

ሩሲያ እና ኢራን እስካሁን በፕሬዝዳንት ኤርዶሃን ንግግር ዙሪያ ምላሽ አልሰጡም፡፡

የባህረ ሰላጤው ሀገራት እስራኤል ኢራንን ለማጥቃት የአየር ክልላቸውን እንዳትጠቀም ከለከሉ እስራኤል በተደጋጋሚ በሶሪያ ዋና ከተማ ደማስቆን ጨምሮ በሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች ጥቃቶችን ማድረሷ ይታወሳል፡፡

ፕሬዝዳንት ኤርዶሃን እስራኤል በጋዛ በሚኖሩ ፍልስጤማዊያን ላይ የዘር ማጥፋት ወንጀል እየፈጸመች ነው በሚል በተደጋጋሚ ተናግረዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም እስራኤል ከሊባኖስ በኋላ ቱርክ የማጥቃት እቅድ እንዳላት መናገራቸውን ዶቸ ቪሌ ከሰሞኑ አስነብቧል፡፡

የሐማስ እና ሂዝቦላህ ዋነኛ ደጋፊ ናት የምትባለው ኢራን ከሰሞኑ እስራኤል በቴህራን ላይ ጥቃት ከሰነዘረች የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት የአየር ክልላቸውን እንዳይፈቅዱ አስጠንቅቃለች፡፡

@Ethionews433 @Ethionews433

9.5k 0 3 20 142

የተሰማቹ ቦታ አለ ?

9.2k 0 3 100 92

በተለምዶ korbe ኦሮምያ ክልል ውስጥ የሚገኝ ቦታ ላይ በድጋሜ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል።

በዚ የመሬት መንቀጥቀጥ 4.6 rector scale አስመዝግቧል

@Ethionews433 @Ethionews433


የመሬት መንቀጥቀጥ በድጋሚ ተከስቷል

ዛሬ ጠዋት ከሰዓታት በፊት 1:38 በአዋሽ ከተማ ባለፈው ሳምንት ከተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ጨመር ያለ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የተነገረ ሲሆን

ከዚህ በተጨማሪ በአደስ አበባ በአዳማ ከተማም ተመሳሳይ ንዝረት መሰማቱን በርካታ ሰዎች እየገለፁ ይገኛል።

#ዳጉ_ጆርናል

@Ethionews433 @Ethionews433

9.3k 1 31 12 73

ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ለፕሬዚዳንት ታየ የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላለፉ

የቻይና ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ አዲስ ለተሰየሙት የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

@Ethionews433 @Ethionews433

8.8k 0 1 14 174

🇪🇹የጨዋታ ቀን ! 🇪🇹

በ2025 የሞሮኮ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ ሦስተኛ የምድብ ጨዋታ 🇪🇹ኢትዮጵያ 🇬🇳 ጊኒን ትገጥማለች።

ጨዋታው ከምሽቱ 1:00 በአይቮሪኮስት አቢጃን ስታድ ደ'ኢቢምፔ ይደረጋል።

ድል ለኢትዮጵያ 🇪🇹!

@Ethionews433 @Ethionews433


ኢትዮቴሌኮም 10 በመቶ ድርሻውን ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ መሸጥ እንደሚጀምር አስታወቀ

ኢትዮጵያን 130 ዓመታትን እንደ ዘመኑ ቴክኖሎጅ ያገለገለው መንግስታዊዉ የቴሌኮም አቅራቢያ ድርጅት ኢትዮቴሌኮም 10 በመቶ ድርሻዉን ለህዝብ መሸጥ እንደሚጀምር ተሰምቷል።

በኢትዮጵያ 130 ዓመታት ገደማ በመንግሥት በብቸኝነት ተይዞ የነበረዉን የቴሌኮም ዘርፍ ከረቡዕ ጥቅምት 6 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለግል ባለሃብቱ በይፋ መሸጥ እንደሚጀምር ከተቋሙ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

@Ethionews433 @Ethionews433


በትራፊክ አደጋ የሁለት ሰዎች ሕይወት አለፈ

አደጋው ከዮራ ሻሾ ቀበሌ በቆሎ ጭኖ ወደ አመያ ሲጓዝ የነበረ ተሽከርካሪ ጨበራ ሻሾ ቀበሌ ላይ በመገልበጡ ነው የደረሰው፡፡

በዚህም የ2 ሰዎች ሕይወት ያለፈ ሲሆን÷በ5 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት መድረሱን የአመያ ዙሪያ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር በቀለ በለጠ ተናግረዋል፡፡

የአደጋው መንስኤ እየተጣራ እንደሚገኝ መጠቆማቸውንም የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ፖሊስ መረጃ ያመላክታል።

@Ethionews433 @Ethionews433


እስራኤል ከ1100 በላይ የአየር ድብደባ እንዳደረገች ተገለፀ

ኢራን እስራኤል ላይ ጥቃት ከፈፀመች በኋላ የእስራኤል አየር ሀይል በተለያዩ አከባቢዎች ከ1100 በላይ የአየር ድብደባዎች እንዳደረገ ተገለፀ።

በተጨማሪም ትናንት የእስራኤል መከላከያ ሚኒስተር
ኢራን በታሪኳ አይታው የማታውቀው እሳት ይወርድባታል።

ሲል ተናግሯል።

በሌላ በኩል ኢራን ለሁሉም አረብ ሀገራት እስራኤል በኢራን እንዲሁም በሊባኖስ ለምታደርገው የአየር ደብዳብ የአየር ክልላቸው እንዳይፈቅዱ አስንቅቋል። ማንኛውም ሀገር ለእስራኤል የአየር ክልላቸው የፈቀዱ እንደሆነ ግን ኢራን ከባድ ምላሽ እንደምትሰጥ አስንጠንቅቃለች።

@Ethionews433 @Ethionews433

9k 0 3 23 155

ወደ ኤርትራ ሲደረግ የቆየው መደበኛ የስልክ አገልግሎት ተቋረጠ

ሐሙስ መስከረም 30 ቀን 2017(አዲስ ማለዳ) ከኢትዮጵያ ወደ ኤርትራ የሚደረግ የመደበኛ ስልክ አገልግሎት መቋረጡን በርካታ ኤርትራውያን እየገለጹ ነው ተባለ፡፡

ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ግንኙነታቸውን ካደሱ በኋላ ያስጀመሩት የመደበኛ ስልክ አገልግሎት በተጀመረ በሰባት አመቱ መቋረጡ ተጠቁሟል፡፡[አዲስ ማለዳ]

@Ethionews433 @Ethionews433


አውሮፕላን አብራሪው የመንገደኞች አውሮፕላን በማብረር ላይ እያለ ህይወቱ አለፈ፡፡

የ59 ዓመቱ ካፒቴን ኢሴሂነ ፔህሊቫን ንብረትነቱ የቱርክ አየር መንገድ የሆነ አውሮፕላን አብራሪ ነበር፡፡

ይህ አብራሪ ከአሜሪካዋ ሲያትል ወደ ኢስታንቡል በመብረር ላይ እያለ ህመም ከተሰማው ከጥቂት ጊዜ በኋላ ህይወቱ እንዳለፈ ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

እንደ ዘገባው ከሆነ በበረራ ላይ የነበረው አውሮፕላን ረዳት አብራሪው ሃላፊነት በመውሰድ በመንገደኞች ላይ ጉዳት እንዳይደርስ ማድረጉን የአየር መንገዱ ቃል አቀባይ ተናግረዋል፡፡

ቃል አቀባዩ ያህያ ኡስተን እንዳሉት "ለካፒቴኑ የመጀመሪያ ህክምና እርዳታ ለማድረግ የተደረገው ጥረት አለመሳካቱን ተከትሎ ረዳት አብራሪው ወዲውኑ በድንገት በረራውን በማቋረጥ አውሮፕላኑን ወደ መሬት ለማሳረፍ እየተሞከረ እያለ ህይወቱ አልፏል" ብለዋ፡፡

ኤርባስ ኤ350 አውሮፕላኑ በኒዮርክ በድንገት ካረፈ በኋላ መንገደኞችን በመጫን ወደ ኢታንቡል የተጀመረው በረራ እንደቀጠለም በዘገባው ላይ ተጠቅሷል፡፡

አውሮፕላን አብራሪው ከፈረንጆቹ 2007 ጀምሮ የቱርክ አየር መንገድ አውሮፕላኖችን ሲበር ነበር የተባለ ሲሆን በየጊዜው የጤና ምርመራም ሲያደርግ ነበር ተብሏል፡፡

እስካሁን ለአብራሪው ህይወት ማለፍ ምክንያት ምን እንደሆነ ይፋ አልተደረገም፡፡ አየር መንገዱ እድሜያቸው ከ40 ዓመት በላይ ለሆኑ አብራሪዎች በየ 6 ወሩ የጤና ምርመራ ማስረጃ እንዲያቀርቡ የሚያስገድድ ህግ አለው፡፡

ከዚህ በፊት በፈረንጆቹ 2015 ላይ የአሜሪካ አየር መንገድ አብራሪ ከአሜሪካ ፎኒክስ ወደ ቦስተን በመብረር ላይ እያለ የ57 ዓመቱ አብራሪ በድንገት ህይወቱ አልፎ አውሮፕላኑም እንዲያርፍ ተደርጎ ነበር፡፡

አልዓይን

@Ethionews433 @Ethionews433

20 last posts shown.