ኢብኑ ተይሚያህ የሱናው አንበሳ


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


"አላህ እንዳንተ አይነት መፍጠሩን ቀጥሏል ብዬ አላስብም ነበር፡፡" ኢብኑ ደቂቀል ዒድ
"ኢብኑ ተይሚያ ሸይኹል ኢስላም ካልሆነ እና ማን ሊሆን ነው?!" ኢብኑል ሐሪሪ

በኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር [ሀፊዘሁሏሂ] የተጻፈ መጽሐፍ፡፡

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


የባህሩ ድንበር አላፊነት ተመልከቱ

ኡስታዝ ሳዳትን ማንበብ አይችልም ብሎ ሲከስ ተመልከቱ በዚህ ልክ ድንበር አላፊ አካል ነው።
➜ ዛሬ ሲጣላ ሀረካት ተደርጎለት ያነብ ነበር አለ ይህ ውርደት መስሎት ነው ነገር ግን ወሏሂ ለኔ ጀግና ነው ሀረካት ተደርጎለት ይህንን ያህል ሰው ወደ ተውሂድ ወደ ሱና የመምጣት ምክንያት ከሆነ የአንተ ቃላት በመገለባበጥ ምን አዲስ ነገር አስገኘ?!

የትኛውም ቃል የሆነን አካል ለማሳነስ አግልግሎት ላይ ከዋለ እሱ ቃል ስድብ ነው።


➪ የወመል ቂያመህ ስለ ስድብህ ትትታሰባለህ!


https://t.me/Menhaje_Selef/




በስህተት ለተጨማሪ ረከዐ የቆመ ሰው
~
አንድ ሰው በስህተት ለተጨማሪ ረከዐ ከተነሳ ለምሳሌ በሱብሕ ሶላት ተሳስቶ ወደ ሶስተኛ ረከዐ ቢነሳ (ልክ እንደዚሁ በመግሪብ ወደ አራተኛ፣ በዙህር ... ወደ አምስተኛ ረከዐ ቢነሳ) ልክ እንዳስታወሰ ወዲያውኑ ተመልሶ መቀመጥ አለበት። እንጂ ባለበት መቀጠል የለበትም። ከዚያም መጨረሻ ላይ ለስህተቱ መጠገኛ ሁለት ሱጁድ ይወርዳል።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


Forward from: ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ🌹
ታላቅ የምስራች ለሀዋሳ ከተማ እና አካባቢዋ ሙስሊም ማህበረሰብ  በሙሉ‼️
=============
እነሆ ለሶስት ተከታታይ ቀናት ከፊታችን ጁሙዓ እስከ እሁድ  በቀን 10/08/2017—12 /08/2017 ዓ·ል  በአላህ ፍቃድ የሲዳማ መዲና  በሆነችው  ሀዋሳ   ከተማ  በተማሪዎች መስጂድና በሙሀጂር መስጂድ ከተለያዩ ቦታዎች በሚመጡ  የሀዋሳ የኒቨርሲቲ ፍሬዎች  በሆኑ ኡስታዞች  ጁሙዓ ከአስር ሶላት በኋላ ጀምሮ እስከ እሁድ  ዒሻእ ሶላት ድረስ  እጅግ በደመቀ እና ባማረ መልኩ  ታላቅ የደዕዋ እና  የኮርስ  ድግስ ተዘጋጅቶ የሚጠብቃችሁ መሆኑን በታላቅ ደስታ ነው  ለመግለፅ እንወዳለን።
 
የእለቱ ተጋባዥ  ኡስታዞች እና የሚሰጡት የኮርስና የደዕዋ ፕሮግራም ዝርዝር እንደሚከተለው ይሆናል::

①  ኡስታዝ ሑሴን ዓሊ(አቡ አመቲ ረሕማን)፡  ኮርስ፦
منهج أهل السنة  في توحيد الأمة للشيخ عبد الرزاق البدر

② ኡስታዝ ዓብዱ ረሕማን ሰዒድ(አቡ ሒዛም)ኮርስ
أصول الدعوة السلفية للشيخ عبد السلام بن برجس 
③ ኡስታዝ ኸዲር አሕመድ፡ ሙሐዶራ፦

إلقاء المحاضرات في المساجد


④ ኡስታዝ ዓብዱሰላም ሸይኽ ሐሰን ዓሊ (አቡ ዓብዲላህ) ኮርስ

الطريق إلى السلفية  للشيخ سلطان العيد

👉በዚህ ፕሮግራም ላይ በምንም አይነት ምክንያት  መቅረት የሌለባችሁ
🚥 የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎችና ሌሎችም ከሀዋሳ በቅርብ ርቀት ላይ የምትገኙ የዩኒቨርስቲ  ተማሪዎች
🚥በሀዋሳ ከተማና በዙሪያዋ  የምትኖሩ የመስጂድ ኢማሞች ፣አቅሪዎች እና ሙአዚኖች
🚥በሀዋሳ ከተማና በዙሪያዋ ያላቸሁ ነጋዴዎች
🚥በሀዋሳ ከተማና በዙሪያዋ የምትኖሩ የመንግስት ሰራተኞች
🚥ሀዋሳ  ከተማ ና በዙሪያዋ የምትኖሩ   ተማሪዎች
🚥በሀዋሳ  ከተማና በዙሪያዋ የምትኖሩ የግል ሰራተኞች
🚥በሀዋሳ  ከተማና በዙሪያዋ የምትኖሩ  ሹፌሮች ና ሌሎችም ከዚህ ውጭ ያላችሁ በሙሉ ተጋብዛችኋል።

ማሳሰቢያ

① ለሴቶችም በቂና ምቹ ቦታ አለን
② ኮርስ የሚሰጡትን ኪታቦችን በተማሪዎች መስጂድ ሱቅ እና በሙሀጂር መስጂድ ማግኘት ይችላሉ::
③ በአካል መገኘት እና መሳተፍ ለማይችሉ ሙሉ ፕሮግራሙን በሚከተሉት ሊንኮች እናስተላልፋለን።


t.me/HawassaUniversityAlumniSunaJamaa


t.me/HawassaUniversityMuslimStudents


Forward from: abdu_rheman_aman
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته.

ያጀመዓ! ለአሏህ ብለን እህታችንን እንርዳት፣ እህታችን "ሐይከል ኢዲሪስ" ትባላለች፣ አንድ ጠንቋይ እሱን እንድታገባ መስተፋቅርት አድርጎባት እንደምታያት...መላ ሰውነቷን እንዳትራመድ አሳስሯታል። ትንሽ ተራምዳ ብዙ ትቆማለች፣ ሰው ደግፎ ካላራመዳት መራመድ አትችልም!። ጠንቋዩ ባገሩ ስለሚፈራ... ቤተሰቦቿም ከሱ (ከጠንቋዩ) ጎን ሁነው ፥ በሽታው እንዲለቅሽ ከፈለግሽ እሱን አግቢ!....አልያ ግን..እኛ ምንም ነገር አንረዳሽም፣ የራስሽ ጉዳይ ብለዋታል። እሷ ደግሞ የአሏህን ጥላት ከማገባ...መጠጋዬ፣ መሸሻይ አሏህ ነውና ወደ ጀባሩ እጠጋለሁ ብላ ይሄው ብዙ ግዜያትን አስቆጥራለች። ምግብና ቤት ክራይኳን የኢስላም ወንድም እህቶቿ  እየከፈሉላት ብዙ ቆይታለች፣ አሁን ልይ ግን ህመሙና ስቃዩ ስለበዛባት የአኼራ ወንድም እህቶች ጤናይን እንዳገኝ እርዱኝ ብላለች፣ አከባቢው ላይ ባሉ ሩቃ ቤቶች ከዓመት በላይ ብትመላለስም ጤናዋ ግን ያው ነው፣ አሁን ላይ የተሻሉ የሚባሉ ሩቃ ቤቶችና የተለያዩ መድኃኒቶችን ለመጠቀም፣ እንደዚሁም የቤት ክራይና  የቀለብ ስለሚያስፈልጋት ለአሏህ ብለን እንርዳት!።

ንግድ ባንክ ፦
1000107541164
Lubaba Ebrahim

ዘምዘም ባንክ ፦
0038054520201
Lubaba Ebrahim

እሷን ማገኘት የፈለጋቹህ..ጎረቤቷ "ሉባባ ኢብራሂም" ቁ. +251928318674

የነየታቹሁትን :
@Nehnu_abnau_aselefiyin_bot
በዚህ ላኩልኝ "ባረከሏሁ ፊኩም!"


Forward from: قناة دروس فضيلة الشيخ محمد زين بن آدم الحبشي - Sheikh Muhammed Zain Adam - ሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ኣደም
ሳምንታዊ የሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ኣደም የደርስ ፕሮግራም!
=
ትምህርቶቹን በቴሌግራም ለመከታተል ይህን ቻናል ይቀላቀሉ:-
https://t.me/SheikhMuhammedZainAdam


Forward from: Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ሐዘን እና ትካዜ በቃ.pdf
577.9Kb
የሸይኽ ዐብዱሰላም አሹወይዒር
وداعا للهموم والأحزان
አጠር ያለ መልእክት "ሐዘን እና ትካዜ በቃ" በሚል ርዕስ በወንድማችን ዐብዱ ሰዒድ ተተረጉሞ ቀርቦላችኋል። አንብቡት። አሰራጩት። ባረከላሁ ፊኩም።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor


Forward from: قناة أبي ريس لنشر السنة
የተጠናቀቁ ዱሩሶች ስብስብ!
------------------------------------

በሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ተቀርተው ተጠናቀው የተለቀቁ ዱሩሶችን እነዚህን ሊንኮች በመጫን በቀላሉ ማግኘት ትችላላችሁ።

1, "አድ'ዱሩሱል ሙሂማህ | الدروس المهمة"
https://t.me/SheikhMuhammedZain/762

2, "ኡሱሉ'ሱንናህ | أصول السنة"
https://t.me/SheikhMuhammedZain/755

3, "ሸርሑ ከሽፊ' ሹቡሀት | شرح كشف الشبهات"
https://t.me/SheikhMuhammedZain/970

4, "ሸርሑ መሳኢሊል ጃሂሊያህ | شرح مسائل الجاهلية"
https://t.me/SheikhMuhammedZain/994

5, "ሸርሑ ዐቂደቲ 'ጠሐዊያህ | شرح عقيدة الطحاوية"
https://t.me/SheikhMuhammedZain/775

6, "ኡሱሉን'ፊ ተፋሲር | أصول في التفسير"
https://t.me/SheikhMuhammedZain/912

7, "አር'ረሒቁል መኽቱም | الرحيق المختوم"
https://t.me/SheikhMuhammedZain/548

8, "ሙልሐቱል' ኢዕራብ | ملحة اﻹعراب"
https://t.me/SheikhMuhammedZain/150

9, "ከሽፉ'ኒቃብ | كشف النقاب"
https://t.me/SheikhMuhammedZain/662

10, "አል'ፈዎኪሁል ጀንያህ | الفواكه الجنية"
https://t.me/SheikhMuhammedZain/224

11، "አል'ፈዎኪሁል ጀንያህ | الفواكه الجنية"
https://t.me/SheikhMuhammedZain/1084

12, "ሙዘኪራ ፊ አሕካሚ አስ-ሲያም | " مذكرة في أحكام الصيام
https://t.me/SheikhMuhammedZain/1255

13, "ሸርሑ ኡሱሊ አስ-ሱና | شرح أصول السنة"
https://t.me/SheikhMuhammedZain/1281

14, "ደዓኢሙ ሚኒሃጂ ኑቡዋህ | دعائم منهاج النبوة"
https://t.me/SheikhMuhammedZain/1310

15, "ሸርሑ ሱንና ሊልበርበሃሪ | شرح السنة للإمام البربهاري"
https://t.me/SheikhMuhammedZain/1462

16, "ሱነኑ አቢ ዳውድ / سنن أبي داود"
https://t.me/SheikhMuhammedZain/1537

17, አልዑቡዲያህ / العبودية
https://t.me/SheikhMuhammedZain/2127

18,ቡሉጉል መራም / بلوغ المرام
https://t.me/SheikhMuhammedZain/2181

19,ሙዘኪራ ዐለል ዐቂደቲል ዋሲጢየህ / مذكرة على العقيدة الواسطية
https://t.me/SheikhMuhammedZain/2479

20,ሸርሑ ኢብኒ ዐቂል ዐላ አልፊየቲ ኢብኒ ማሊክ/شرح ابن عقيل على ألفية ابن مالك
https://t.me/SheikhMuhammedZain/2523

21,አል ቀዋዒዱል ሒሳን አል ሙተዐሊቀቲ ቢተፍሲሪል ቁርኣን/القواعد الحِسان المتعلقة بتفسير القرآن
https://t.me/SheikhMuhammedZain/2772

22,ሙስጠለሑል ሐዲሥ/مصطلح الحديث
https://t.me/SheikhMuhammedZain/2830

23,ሸርሑ ሙቀዲመቲ ተፍሲር/شرح مقدمة التفسير
https://t.me/SheikhMuhammedZain/2849

24,መትኑል አጅሩሚየህ/متن الأجرومية
https://t.me/SheikhMuhammedZain/2898

25,ደላሉ ጀማዐቲል አሕባሽ/ضلال جماعة الأحباش
https://t.me/SheikhMuhammedZain/3112


📍የሸይኹን የተጠናቀቁ ዱሩሶችን ለማግኘት ይህን ቻናል ይቀላቀሉ ↓↓↓
https://t.me/SheikhMuhammedZain


ኡስታዝ ቃል አሚን በቴሌ ግራም ብቅ ብለዋል ተቀላቀሉ በተለይ ንጽጽር የምትሰሩ https://t.me/KASTREGR


ለይሰል ገሪቡ 3

🎙አብዱ ሸኩር አቡ ፈዉዛን

የግጥሟን ፒዲኤፍ ለማግኘት👇
https://t.me/abu_fewzan_abdu_shikur/5837


Forward from: ስለ ቀልባችን
መልካም ዜና!
~
• ለተወሰኑ ቀናት ብቻ የሚቆይ በቴሌግራም የቀጥታ ስርጭት የሚካሄድ ልዩ የኮርስ ፕሮግራም አዘጋጁተናል። በዚህ ፕሮግራም ላይ አራት መሰረታዊ ኪታቦችን በሶስት ኡስታዞች ይቀርባሉ።

①- (منظومة السير إلى الله)
- በኡስታዝ አብዱ ረዛቅ ሙሐመድ አል-ባጂ
②-لفتة الكبد إلى نصيحة الولد)
- በወንድም አቡ ሱፍያን
③-(سلسلة تسهيل العلوم الشرعية)
- በኡስታዝ ሙሐመድ ባቲ
④-(مفتاح طريق الأولياء)
- በኡስታዝ አብዱ ረዛቅ ሙሐመድ አል-ባጂ
|•|
🗓የሚጀመርበት ቀን፦መጋቢት 30(ማክሰኞ)
⏰ ሰዓት፦ከ ምሽቱ 3:00 ጀምሮ

🖇ፕሮግራሙ ቀጥታ ስርጭት የሚተላለፍበት ሊንክ፦👇
https://t.me/Sle_qelbachn1
https://t.me/Sle_qelbachn1




Forward from: Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
April the fool - ክፉ ልማድ!
~
ዛሬ April 1 ነው። በዚህ ቀን April Fools' Day or All Fools' Day የሚባል ልማድ የሚከተሉ ሰዎችን ተጠንቀቁ። ሙስሊም የሆነ ሰው ራሱን የማንም ቆሻሻ ባህል ማራገፊያ አያደርግም። በዚህ ዘመን ከነጮች ከተቀዱ ነውረኛ ባህሎች ውስጥ አንዱ ይሄ April the Fool የተሰኘው የጅላጅሎች ልማድ ነው። ያልተከሰቱ ሃሰተኛ ነገሮችን በመንገር ሰዎችን በማስደንገጥ ይዝናናሉ። ሰዎች ላይ ከሚፈጠረው ከባድ ድንጋጤ ይልቅ የራሳቸውን ቅፅበታዊ ደስታ ያስቀድማሉ። ይሄ ልማድ በጣም ጎጂ ነው። ከያዛቸው ጥፋቶች ውስጥ ለመጥቀስ ያክል፦

1ኛ:- ውሸት አለበት።
ውሸት በኢስላም ሐራም ነው። ለቀልድ እያሉ ማቅረቡ እውነታውን አይቀይረውም። ነብያችን ﷺ እንዲህ ይላሉ፡-
وَيْلٌ لِلَّذِي يُحَدِّثُ بِالْحَدِيثِ لِيُضْحِكَ بِهِ الْقَوْمَ فَيَكْذِبُ وَيْلٌ لَهُ وَيْلٌ لَهُ
"ሰዎችን ለማሳቅ ብሎ እየዋሸ ወሬን የሚያወራ ሰው ወዮለት! ወዮለት! ወዮለት!" [አቡ ዳውድ፣ ነሳኢይ፣ ቲርሚዚይ እና አሕመድ የዘገቡት ሲሆን ሸይኹል አልባኒይ “ሐሰን” ብለውታል፡፡]

2ኛ፦ ሰዎችን ማስደንገጥ አለበት።
ይሄ ከዚህ ልማድ ጋር በሰፊው የተቆራኘ ጥፋት ነው። ሰዎችን ማስደንገጥ መዝናኛ ሊሆን አይገባም። ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል:–
لا يحل لمسلم أن يروع مسلماً
"ለሙስሊም ሙስሊምን ሊያስደነግጥ አይፈቀድለትም።" አልባኒይ ሶሒሕ ብለውታል። [ሶሒሕ አቢ ዳውድ፡ 5004]

3ኛ፦ በአጥፊዎች መመሳሰልና የሌሎችን ብልሹ ባህል ማስፋፋት አለበት። ነብያችን ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
مَنْ تَشَبَّهَ بِقَوْمٍ فَهُوَ مِنْهُمْ
"በሰዎች የተመሳሰለ ከነሱው ነው።" [ሶሒሕ አቢ ዳውድ፡ 3401]
ስለዚህ ይህን ክፉ ልማድ በመፈፀም ራሳችንን ወንጀል ላይ፣ ሌሎችን ድንጋጤና አደጋ ላይ ከመጣል ልንቆጠብ ይገባል።
=
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor


Forward from: MuhammedSirage M.Nur.
"የውሸት ቀን "

ሀቅ ነው እምነትህ ከስር መሰረቱ
ውሸት ላይ አልቆመም እውነት ነው ከጥንቱ
ትናንትም ያማረ ዛሬም ነው የፀዳ
እውነት ብቻ ‘ሚሰብክ የለበት ቀዳዳ

እናም ወንድሜ ሆይ ፣
የእብለት ሌሊት ነው ወይም የውሸት ቀን
ሲልህ ያውሮፓ ሰው የነሱም በቀቀን
ውሸት ለናንተ ነው በለው አላውቀውም
ያንተን የቅጥፈት ቀን ከቶ አላከብረውም!
ሰኞም የ’ውነት ቀን ነው ማክሰኞም የሀቁ
ሰኔም ላይ አይዋሽም ሙስሊም እውነት ስንቁ
ዳሩ ለነሱማ ለዛ ለምእራቡ
ሀምሌና ነሀሴው ማክሰኞና ሮቡ
ያው የውሸት ወር ነው የእብለት ቀናቸው
የቅጥፈት ቀን እንጂ የ’ ውነት መች አላቸው።

https://t.me/Muhammedsirage


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


Forward from: Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ከዒደል ፊጥር ቀጥሎ ያሉት ቀናት የዒዱ ድባብ ይከተላቸዋል። በዚህ የተነሳ ሰፊና የሚጠያየቁ ቤተሰቦች የሸዋልን ፆም ቀጥታ ከዒዱ ማግስት ከሚጀምሩ ትንሽ ቢያቆዩት የተሻለ ነው። በተለይ በዚያራ መገናኘት ሲኖር ለጠያቂ ቤተሰብ እና ጓደኛ ትኩረት መስጠቱ መልካም ነው። ነብያችን ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
إن لِزَوْرِك عليك حقا
"ለዘያሪህ ባንተ ላይ ሐቅ አለው።" [አልቡኻሪይ እና ሙስሊም]

መዕመር ብኑ ራሺድ ረሒመሁላህ ከዒደል ፊጥር በኋላ ቀጥታ የሸዋልን ስድስት ስለ መፆም ሲጠየቁ "በአላህ እንጠበቃለን! እነዚህ'ኮ የዒድ፣ የመብላት የመጠጣት ቀናት ናቸው!" ብለዋል። ከዐብዱረዛቅ አሶንዓኒይም ተመሳሳይ መልእክት ተገኝቷል። [ሙሶነፍ ዐብዲረዛቅ አሶንዓኒይ]

* በዚህ መልኩ መፈፀሙ ሌላም ፋይዳ አለው። አንዳንድ አላዋቂዎች ዘንድ ሸዋል ስምንትን ሌላ ዒድ አድርገው እንዳያስቡ ያግዛል። [ሙኽተሶሩል ፈታወል ሚስሪያህ፣ ኢብኑ ተይሚያህ]

ይሄ ማለት ግን ቀጥታ ከሸዋል ሁለት ጀምሮ መፆም ከነጭራሹ አይፈቀድም ለማለት አይደለም። ሰውዬው እንደ ሁኔታው በኸይር ስራ ላይ መቻኮልን ቢያስቀድም የሚነቀፍበት አይደለም። አዋቂው አላህ ነው።
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor


Forward from: Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
1፦ ከዐረብ ሃገራት ውስጥ ፍልስጤም፣ ኢማራት፣ የመን፣ ኩወይት፣ በሕረይን፣ ቀጠር፣ ሊባኖስ፣ ሱዳን፣ የዒራቅ ሱኒዮች የወቅፍ ተቋም እና ሞሪታኒያ ዛሬ እሁድ ዒድ እንደሆነ ያወጁ ሃገራት ናቸው። የኛዎቹ "ምሁራን" ይህን ሁሉ ሃገር ጥለው ጉዳዩን የሳዑዲ ሴራ አድርገውታል።
2ኛ፦ አዘርቤጃን፣ አፍጋኒስታን፣ ካዛኽታን፣ ኡዝቤኪስታን፣ ቱርክ፣ ... ዒድ ዛሬ እሁድ እንደሆነ ያወጁ ሃገራት ናቸው።
3ኛ፦ እንዲሁም ዘጠኝ የምዕራብ አፍሪካ ሃገራት (ናይጄሪያ፣ ኒጀር፣ ማሊ፣ ጊኒ፣ ኮትዲቯር፣ ቤኒን፣ ሴኔጋል፣ ጋምቢያ እና ቶጎ) ዛሬ እሁድ ዒድ እንደሆነ አውጀዋል።
4ኛ፦ ከነዚህም ውጭ አናሳ ሙስሊሞች ባሉባቸው አሜሪካ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሩሲያ፣ ብሪታኒያ፣ ፈረንሳይ፣ ካናዳ፣ ወዘተ. በየሃገራቱ የሚገኙ ኢስላማዊ ተቋማት ዒድ ዛሬ እሁድ እንደሆነ ገልፀዋል።
ከተዘረዘሩት ውስጥ ከፊሎቹ የስነ ፈለክ ካሌንደር የሚጠቀሙ ናቸው።

ከነዚህ ሁሉ ሃገራት ነጥለው የሳዑዲው እወጃ ላይ ግርግር ማስነሳት ጅህልና እና ለሳዑዲ ያረገዙት ጭፍን ጥላቻ ተጣምረው የወለዱት ብልግና ነው። ስለ ሳዑዲ የራሳቸው ጉዳይ! ግን የሙስሊሞችን የደስታ ቀን እዚህ ግባ በማይባል ተልካሻ ሰበብ ወደ ግርግር መቀየር የለየለት ነውረኛ ተግባር ነው። በዚህ ነውረኛ ተግባር ላይ ከተሰለፉት ውስጥ በአካደሚ ትምህርት ገፋ አድርገናል ብለው የሚያስቡ አንዳንድ አካላት ከፊት ረድፍ ተሰልፈው አይተናል። ለነዚህ አካላት የምለው አለኝ። ድንበራችሁን ጠብቁ! አቅማችሁንም እወቁ። ሰው እንዴት አካውንቲንግ፣ ቢዝነስ አስተዳደር፣ ሳይኮሎጂ፣ ፍልስፍና ወይም የሳይንስ ዘርፎችን ተምሮ ይሄ ነው የሚባል ትኩረት ባልሰጠው የሸሪዐ ጉዳይ ውስጥ ጥልልቅ እያለ ግልፅ መረጃ በመጣባቸው የፊቅህ ጉዳዮች ውስጥ ያላቅሙ እየገባ ደፋር ግላዊ አስተያየት ይሰጣል?!

ወንድሞቼ! የተማራችሁት የቀለም ትምህርት አረቄ ሆኖ አጉል ድፍረት እየሰጣችሁ ጊዜ ባልሰጣችሁት የሸሪዐ እውቀት ላይ ፍርድ እንድትሰጡ ሲያደርጋችሁ ትንሽ ሐያእ አይሰማችሁም እንዴ? የምትከበሩትኮ የሚከበረውን ስታከብሩ ነው። ሃይማኖቱ የናንተም ነውና ስለ ኢስላም አታውሩ አይባልም። ግን ከቁርኣንና ከሐዲሥም፣ ከዑለማእ ንግግርም ርቆ ሌጣ ግላዊ እይታዎችን በድፍረት ማንፀባረቅ ነውር አይደለም ወይ? አንዳንዶቹ የፈለክ ምሁራንን ውሳኔ መከተል እንደሚገባ ያሳስቡናል። ያላስተዋሉት ግን የፈለክ ምሁራኑ ራሳቸው ወጥ ውሳኔ የላቸውምኮ። በተለያዩ አመታት በርካታ ታዋቂ የፈለክ ምሁራንን እርስ በርሱ የሚጋጭ ትንበያ ሲያወጡ ማየት የተለመደ ነው። ለምሳሌ ያህል የፈለክ ሂሳብን ከሚጠቀሙ ሃገራት ውስጥ የአሁኑን ዒድ ከፊሎቹ ዛሬ እሁድን፣ ከፊሎቹ ነገ ሰኞን መርጠዋል። ይሄ ምንድነው የሚያሳየው?
ለማንኛውም ተምረናል የምትሉ አካላት እረፉ። በየዘርፉ ጥልቅ እያላችሁ የእርጎ ዝንብ አትሁኑ። ሁሉም ዘርፉን ሊጠብቅ ይገባል። ኢንጂኔር በህክምና ጉዳይ ላይ ጣልቃ እንደማይገባው አካደሚ የተማረውም ትኩረት ባልሰጠው የሸሪዐ እውቀት ላይ እጁንም ምላሱንም ሊሰበስብ ይገባል። ብዙም ይሰማሉ ብዬ አይደለም ይህን የማነሳው። ብዙዎቹ እነዚህ አካላት ትኩረት ፈላጊ (attention seekers) ናቸው። ችግራቸው እራሳቸውን ከመሀይማን መሀል የተገኙ ልዩ አድርጎ የመመልከት በሽታ ነው። ስለዚህ የሚሸወድባቸው አካል ይነቃ ዘንድ በሚግገባቸው መልኩ ማናገር ይገባል። ቆማጣን ቆማጣ ካላሉት ገብቶ ይፈተፍታል ይሉት አባባል በነሱ ጎልቶ እየታየ ነው።

ሃገራችን እስከ መቼ ሳዑዲን ትከተላለች?
~
ጥያቄው ንፁህ ጥያቄ ሆኖ ሚዛን የሚደፋውን ለመለየት ከሆነ ጥሩ ነው። አንድ ሃገር ካወጀ ተመሳሳይ የሰዓት አቆጣጠር ያላቸውና ሰዓታቸው ከኋላ የሆኑ ሌሎች ሃገራት መከተል አለባቸው ወይ የሚለው በዑለማእ መካከል የተለያየ ሃሳብ የተሰነዘረበት ጉዳይ ነው።

1- ኢማሙ ማሊክ፣ ሻፊዒይ፣ አሕመድ፣ ለይሥ እና ሌሎችም በርካታ ዓሊሞች አንድ ሃገር ጨረቃን ካየ ሌሎችም ሊከተሉ ይገባል ይላሉ። ይሄ አቋም የኢብኑ ተይሚያ፣ የሸውካኒይ፣ የሲዲቅ ሐሰን ኻን፣ የአልባኒይ እና የኢብኑ ባዝ ምርጫ ነው። ይህንን የማነሳው በዚህ ጉዳይ ላይ አንድ ሰው እንዲሁ የሳዑዲን ወይም የሌላ ቀድሞ ያወጀን ሃገር ምርጫ እንከተላለን ቢል እንደዋዛ የምናጣጥለው ሃሳብ እንዳልሆነ ለማስታወስ ያክል ነው።
2- ሌላ ተመሳሳይ የሰዓት አቆጣጠር መስመር ላይ ያሉ ሃገራት አንዱ ባየው ሌላው ሊከተል ይገባል የሚል አቋም አለ። ይሄ የኢብኑ ዑሠይሚን፣ የሙቅቢልና የሌሎችም አቋም ነው። በዚህም ሂሳብ ቢኬድ ከሳዑዲ ጋር የቀረበ ሁኔታ አለን።
3- እያንዳንዱ ሃገር ራሱን የቻለ ስለሆነ የአንዱ ሃገር ማየት በሌላው ላይ አስገዳጅ አይሆንም የሚል አቋም የመረጡም አሉ።
እነዚህ በጉዳዩ ላይ ከተሰነዘሩ ሃሳቦች ውስጥ ጠንካራዎቹ ናቸው። የሃሳቡ መለያየት ምክንያት "ጨረቃውን ስታዩት ፁሙ ። ስታዩትም አፍጥሩ" በሚለው ሐዲሥ ያለ የግንዛቤ ልዩነት ነው።

ሚዛን የሚደፋው የትኛውም ቢሆን ዛሬ እኛ ላለንበት ተጨባጭ ሳዑዲን መከተል ትክክለኛ ምርጫ ነው። ሃገራዊ ቅቡልነት ያለው ሁሉን የሚያግባባ ተቋም ሲኖር መስአላውን መፈተሸ ወግ ነው። እንዲሁ በመዝሀብ ጎጠኝነት ስለታሰሩ ብቻ በራሳቸው ጨረቃ እያዩ ሳይሆን "ወሃB ያየውን አንቀበልም" በሚል አጉል ድርቅና ብቻ በፆምም በዒድም ካልተለየን የሚሉት ግን እልህ ወለድ ሙግት እንጂ ውሃ የሚያነሳ ሃሳብ አይደለም።
በድጋሚ ተቀበላለሁ ሚና ወሚንኩም!
(ኢብኑ ሙነወር፣ ሸዋል 1/1446)
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor


Forward from: Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ረመዳን 29 ወይስ ሰላሳ? ስለ ወቅታዊው የዒድ ውዝግብ
~
ከፊል ሃገራት ዒዳቸው ዛሬ እሁድ እንደሆነ ከፊሎቹ ደግሞ ነገ ሰኞ እንደሚሆን አውጀዋል። ይህንን ተከትሎ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ጉዳዩ መነጋገሪያ ሆኗል። እውነት ጉዳዩ ይህን ያህል የሚደርስ ነበር? በጭራሽ! ጌታችን አላህ እንዲህ ይላል:-
{یَـٰۤأَیُّهَا ٱلَّذِینَ ءَامَنُوۤا۟ أَطِیعُوا۟ ٱللَّهَ وَأَطِیعُوا۟ ٱلرَّسُولَ وَأُو۟لِی ٱلۡأَمۡرِ مِنكُمۡۖ فَإِن تَنَـٰزَعۡتُمۡ فِی شَیۡءࣲ فَرُدُّوهُ إِلَى ٱللَّهِ وَٱلرَّسُولِ إِن كُنتُمۡ تُؤۡمِنُونَ بِٱللَّهِ وَٱلۡیَوۡمِ ٱلۡـَٔاخِرِۚ ذَ ٰ⁠لِكَ خَیۡرࣱ وَأَحۡسَنُ تَأۡوِیلًا}
"እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ታዘዙ። መልክተኛውንና ከእናንተም የስልጣን ባለቤቶችን ታዘዙ። በማንኛውም ነገር ብትከራከሩ በአላህና በመጨረሻው ቀን የምታምኑ ከሆናችሁ (የተከራከራችሁበትን ነገር) ወደ አላህና ወደ መልክተኛው መልሱት። ይህ የተሻለ መጨረሻውም ያማረ ነው።" [አኒሳእ፡ 59]

በዚህም መሰረት ይህንን ውዝግብ የተከሰተበትን ጉዳይ ወደ ነብዩ ﷺ ሱና ስንመልሰው የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ እንዳሉ እናገኛለን፦
"إِذَا رَأَيْتُمُ الْهِلَالَ، فَصُومُوا، وَإِذَا رَأَيْتُمُوهُ، فَأَفْطِرُوا، فَإِنْ غُمَّ عَلَيْكُمْ ؛ فَصُومُوا ثَلَاثِينَ يَوْمًا"
"ጨረቃውን ስታዩት ፁሙ ። ስታዩትም አፍጥሩ። ከተጋረደባችሁ ሰላሳ ቀን ፁሙ።"[አልቡኻሪይ፡ 1906] [ሙስሊም፡ 1080]

ይህንን ነብያዊ አስተምህሮት መነሻ በማድረግ ሃገራት የፆማቸው መጀመሪያ እና የዒዳቸው ቀን ሊለያይ ይችላል። ወደ አሁኑ ክስተት ስናመጣው የሸዋልን ጨረቃ ያዩ ሃገራት ዛሬ እሁድ ዒድ እንደሆነ አወጁ። ያላዩት ደግሞ ረመዳን 30 መሙላትን ወሰኑ። የሁለቱም ውሳኔ በሐዲሡ መሰረት ትክክለኛ ነው። ጨረቃውን ያየ ሃገር በጨረቃው መሰረት ይወስናል። ያላየ ደግሞ የወሩን ቁጥር ሰላሳ ይሞላል። ይሄ ነገር ዘንድሮ የመጣ ሳይሆን ጥንትም የነበረ ነው። እንኳን ዛሬ ሙስሊሙ ዓለም ለብዙ የተለያዩ ሃገራት በተበተነበት ጊዜ በአንድ ኺላፋ ስር በነበረበት በሙዓዊያህ ጊዜ ተከስቷል። [ሶሒሕ አቢ ዳውድ፡ 2332] ጉዳዩ በዚህ ልክ ከሆነ አሁን ለምን የውዝግብ አጀንዳ ሆነ? ሁለት ምክንያት ሊነሳ ይችላል።

* 1ኛው የውዥንብሩ ምክንያት፦ የሸሪዐውን አስተምህሮት በቅጡ አለማወቅ ነው። አለማወቁ ሁለት መልክ አለው።

1.1. አንዱ ችግር ጉዳዩ በጨረቃ እንጂ በስነ ፈለክ ሂሳብ እንደማይወሰን አለማወቅ ነው። ብዙ የሸሪዐ መሰረታዊ እውቀት የሌላቸው ግን አካደሚ የተማሩ ወገኖች እዚህ ውስጥ አሉ። ፆምም ሆነ ዒድ በስነ ፈለክ ሂሳብ አይወሰንም። ምክንያቱም ነብያችን ﷺ እንዲህ ብለዋልና፦
"لَا تَصُومُوا حَتَّى تَرَوُا الْهِلَالَ، وَلَا تُفْطِرُوا حَتَّى تَرَوْهُ، فَإِنْ غُمَّ عَلَيْكُمْ فَاقْدُرُوا لَهُ"
"ጨረቃዋን ሳታዩ እንዳትፆሙ፡፡ ሳታዩትም እንዳታፈጥሩ። ከተጋረደባችሁ ሰላሳ ሙሉት።" [አልቡኻሪይ፡ 1906] [ሙስሊም፡ 1080]

1.2. ሌላው ችግር ደግሞ በኢስላማዊው አቆጣጠር ወሩ 29 ቀን የሚሆንበት ብዙ ጊዜ እንዳለ አለማወቅ ነው። ይህንን የማያውቁ መሀይማን "ሳዑዲ አንድ ቀን ቀነሰችብን" እያሉ ነው። ይሄ ድንቁርና የወለደው ባዶ ድፍረት ነው። የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
"الشَّهْرُ تِسْعٌ وَعِشْرُونَ"
"ወር 29 ቀን ነው።" [አልቡኻሪይ እና ሙስሊም] ይሄ ብዙ ጊዜ እንደሚከሰት የታወቀ ነው። አንዳንዶች ግን የረመዳን ፆም ገና ዘንድሮ የጀመሩ ይመስል እንደ አዲስ መነጋገሪያ እያደረጉት ነው። በጣም የሚገርመው በዚህ ጉዳይ አንዳንድ የ'ርጎ ዝንብ የሆኑ ካfi ሮች ጭምር የፃፉ ሲሆን በርካታ ቂላቂል ሙስሊሞች ጭምር ላይክና ሼር ያደረጉላቸው መሆኑ ነው። እንዲህ አይነት ሞኞችን በማሰብ ነው አል ኢማም ኢብኑ ኹዘይማ በሶሒሕ ከታባቸው እንዲህ የሚል ርእስ ያሰፈሩት:-
(38) باب الدليل على أن صيام تسع وعشرين لرمضان كان على عهد النبي - صلى الله عليه وسلم - أكثر من صيام ثلاثين خلاف ما يتوهم بعض الجهال والرعاع ، أن الواجب أن يصام لكل رمضان ثلاثون يوما كوامل
"አንዳንድ መሀይማንና እና ሞኞች ሁሌም ረመዳን ሰላሳ ቀን ሙሉ ሙሉ እየተደረገ ሊፅፆም ግዴታ እንደሆነ ከሚገምቱት በተለየ ረመዳንን 29 ቀን መፆም ሰላሳ ቀን ከመፆም በበዛ መልኩ በነብያችን ﷺ ዘመን እንደነበረ የሚያሳይ መረጃን የሚመለከት ርእስ" በማለት በርእስ ደረጃ አስፍረው ጉዳዩን ዳሰዋል።" [ሶሒሕ ኢብኒ ኹዘይፋህ፡ 3/369]

ሶሐቢዩ ዐብዱላህ ብኑ መስዑድ ረዲየላሁ ዐንሁ እንዲህ ይላሉ፦
مَا صُمْتُ مَعَ النَّبِيِّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ تِسْعًا وَعِشْرِينَ أَكْثَرُ مِمَّا صُمْنَا ثَلَاثِينَ
"ከነብያችን ﷺ ጋር ሃያ ዘጠኝ የፆምኩት ሰላሳ ከፆምኩት የበዛ ነው።" [አቡ ዳውድ፡ 2322] [ቲርሚዚይ፡ 689] [ኢብኑ ማጀህ፡ 1658] አልባኒይ እና አሕመድ ሻኪር ሶሒሕ ብለውታል።

* ሁለተኛው የውዥንብሩ ምክንያት ብዙዎች የተለከፉበት ጥግ የደረሰ የሳዑዲ ጥላቻ ነው። በየትኛውም ጉዳይ ላይ ሳዑዲ ካለችበት የተለየ የሆነውን ይመርጣሉ። ሳዑዲ ከሌሎች ሃገራት ጋር የጋራ ምርጫ ቢኖራት ራሱ ነጥለው ከማብጠልጠል አይመለሱም። ክፋትና ምቀኝነት በዚህ መጠን ልብን ሲበላ ማየት የሚደንቅ ነው።

መታወቅ ያለበት የሳዑዲ የጨረቃ እይታ ከሌሎች ሃገራት የተሻለ እንጂ ያነሰ አይደለም። ሳዑዲ የሂጅራውን አቆጣጠር መሰረት በማድረግ የየወሩን መግባት ለመለየት ባለሙያዎች የሚሰማሩባቸው:-

1- ከ10 በላይ ቋሚና ተንቀሳቃሽ ጣቢያዎች አሏቸው።
2- ለመመልከት የሚሰማሩት በጉዳዩ ላይ የረጅም ጊዜ ልምድ እና የእይታቸው ጤናና አቅም ተመርምሮ ብቁ መሆናቸው የተረጋገጡ አካላት ናቸው።
3- እነዚህን ጣቢያዎች የሚቆጣጠረውና የሚከታተለው የንጉስ ዐብዱልዐዚዝ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ከተማ ሲሆን
4- የእይታዎቹን ውሳኔ የሚያፀድቀው የሃገሪቱ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነው።

ለዚህ አላማ የሚመደቡት አካላት በየወሩ 29ኛ ምሽት ላይ ጨረቃን ለመመልከት በሃገሪቱ የተለያዩ ግዛቶች በሚገኙት በየጣቢያዎቹ ይሰማራሉ። ለእይታው እንዲያግዛቸው ቴሌስኮፕ ይጠቀማሉ። ቴሌስኮፕ መጠቀም ግዴታም ባይሆን የተፈቀደ ነው ይላሉ ሸይኽ ኢብኑ ዑሠይሚን። [መጅሙዑ ፈታወል ዑሠይሚን፡ 19/37]
በዚህ መልኩ የተደራጀውን የሳዑዲያ እይታ አናምንም የሚሉ አካላት እነ ገብሬና እርገጤ የሚቆጣጠሩትን አቅሙም እዚህ ግባ የማይባለውን አዲስ አበባ ዳርቻ ላይ የሚገኘውን የእንጦጦ ጣቢያ ብንጠቀም ይሻላል እያሉ ነው። እነዚህ አካላት ለሳዑዲ ያላቸው ጥላቻ ጋርዷቸው እንጂ የእንጦጦው ጣቢያ በየትኛውም መመዘኛ ጥንቅቅ ብለው ከተዋቀሩት በርካታ የሳዑዲ ጣቢያዎች የሚሻልበት አንድ ሰበዝ መምዘዝ አይችሉም። እንዲሁ ጥላቻ ብቻ! ጥላቻ ደሊል ይሆናል እንዴ?

ደግሞም መነጋገሪያ የሆነውን የዘንድሮውን ዒድ ብንወስድ ዒዱ እሁድ እንደሆነ በመግለፅ ላይ ሳዑዲ ብቸኛ አይደለችም።


Forward from: Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ነገ እሁድ ዒደል ፊጥር ነው።
ተቀበለላሁ ሚና ወሚንኩም ሷሊሐል አዕማል!
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor


Forward from: Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ወንድማችን ኢብራሒም ከክርስቲያን ቤተሰብ የተገኘ በቅርብ የምናውቀው ጠንካራ የሱና ወጣት ነው። ይህ ወንድማችን የአላማጣ እና የቆቦ የሱና እንቅስቃሴዎች ላይ የቻለውን ሲያደርግ ነበር፤ በማድረግ ላይ ይገኛል። ያጋጠሙትን የዱንያ ችግሮች ዋጥ አድርጎ ረዘም ያለ ጊዜ እያሳለፈ ቢሆንም ገና በወጣትነቱ የስኳር ህመምተኛ በመሆኑ ነገሮች ከብደውታል። የሞያ ትምህርት ተምሮ የነበረ ቢሆንም ወደ ስራ ለመግባት ግን የተወሰነ ቢሆን ገንዘብ የሚያስፈልግ በመሆኑ ስራ ሊጀምር አልቻለምና እሱ ሳያውቅ እና ሳይጠይቅ እሱን ለመርዳት ከአንዳንድ ወንድሞች ጋር በመመካከር ተነስተናልና የምትችሉ ከጎናችን ብትቆሙ ደስ ይለናል ባረከላሁ ፊኩም።

የአላህን ምንዳ ፈልገን የተወሰነ ገንዘብ ሰብስበን ሃሳቡን በመቀነስ ላይ ሰበብ እንሁነው እንላለን።


አካውንት ቁጥሩ:-
1000593765238 Ebrahm argane

20 last posts shown.