ኑ እናንብብ


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


እንባየን የት ላርገው
(በእወቀቱ ስዩም)

ቀና በል ይሉኛል፥ ወዴት ልበል ቀና
ከላይ ተደፍቶብኝ፥ አገር እንደቁና
ጣራው ባጡ ቀርቦኝ
በር አልባ ግድግዳ፥ እንደ ዝናር ከቦኝ
በጫጩት ጉልበቴ፥ እየተወራጨሁ
እንባየን ዘግኘ፥ ሽቅብ እየረጨሁ
ወደ አማልክት ብጮህ፥ ጸሎቴን አይሰሙት
በየት በኩል ኖሬ፥ በየት በኩል ልሙት፤

በምን ይገለጻል፥ የትውልዴ አበሳ ከመንበርከክ ብዛት፥ መራመድ የረሳ
ያልፋል ተለጉሞ
ያልፋል ተከርችሞ
የጉልበቱን ኮቴ፥ ምድር ላይ አትሞ፤

ወፈፌ ቀን አልፎ፥ እብድ ቀን ሲመጣ
ማልቀስ አመጽ ሲሆን፥ በሸንጎ ሚያስቀጣ
እንባየን የት ላርገው
ወዴት ልሸሽገው?


Video is unavailable for watching
Show in Telegram




"ጥፊያችሁ ተመልሶ ይመጣል!!"
ኦሾ
አዘጋጅና አቅራቢ- ግሩም ተበጀ

"የኦሾ ድንቅ አስተምህሮ በግሩም ውብ የአተራረክ ጥበብ ቀርቧል።"
@zephilosophy


Forward from: Tesfaab Teshome


ካህሊል ጂብራን


ዶይስቶይቭስኪ አንድ እውነት ልንገራችሁ ብሎ ይጀምራል፦

‹‹ዓለም እንደ እናታችሁ አይደለችም ንዴታችሁን የመታገስ አመል የላትም፤ ቢርባችሁ ደርቃችሁ ትቀራላችሁ እንጂ ማንም ግድ አይሰጠውም!። እናት ግን ቀን ላይ ተናዳችሁ ትጮኹባታላችሁ፤ እናም ማታ በቀኑ መጨረሻ ሁሉንም እረስታ እራት ታቀርብላችኋለች..›› ❤‍🩹

መልካም የእናቶች ቀን


Forward from: መፅሀፍ አለሜ📚📚📖📖
“እነሱ የሚያምኑትን ሳትነቅፍ የነሱ ግልባጭ ስትሆን ብቻ ጥበበኛ እና ጥሩ ሰው ነው ይላሉ። ሰዎች እራሳቸውን መሆን ከሚፈልጉ ብሎም እጣ ፈንታቸውን መቆጣጠር ከሚችሉ ሰዎች ጋር ፈጽሞ አይስማሙም። ምክንያቱም የፈጠርከው መረጋጋት እና ማስተዋል አደጋ ላይ ይጥላቸዋል። የማሰብ መብቱን የተገፈፈ ሰው መሆን በማኀበረሰቡ ያሸልማል!።”

              ―Jean Paul Sartre




Never give up on urself


Forward from: ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy
"መብራቱን ይዛችሁ ጨለማው የት እንደሚገኝ ትፈልጋላችሁ።"
ኦሾ
..የቀጠለ

ብርሃን ሲኖር ጨለማ ይጠፋል፡፡ ጨለማ ጨርሶ የለምና የሚጠፋው ጨለማ አይደለም፡፡ ጨለማ የብርሃን አለመኖር ነው፡፡ የራስ ኩራት(የበላይነት ስሜት) ልክ እንደ ጨለማ ነው፤ ጨርሶ የለም፡፡ የራስ ኩራት የንቃት አለመኖር ነው፡፡

ስለዚህም ተመልከቱት እንጂ አጥፉት አልልም፡፡ ተመልካች፣ አስተዋይ ሁኑ. . .
ፖለቲከኛ ጭው ያለ የራስ ኩራተኛ ነው፤ ቅዱስ ነኝ ብሎ የሚያስብ ሰው በጣም የባሰ የራስ ኩራተኛ ሊሆን ይችላል፡፡ ፖለቲከኛው በቀላሉ ሊታወቅ ይችላልና ቅዱሱ ከፖለቲከኛው የበለጠ አደገኛ ነው፡፡

የእኔ ጠቅላላ የህይወት ተግባር የሰውን መሰረታዊ ችግሮች ፈልጎ ግንዛቤ ማስጨበጥ ነው፡፡ የሰውን መሰረታዊ ችግሮች አንዴ ካወቅን መፍትሄ መፈለጉ አስቸጋሪ አይሆንም፡፡
እኔ መሲህ ነኝ፣ እኔ አቫትራ ነኝ አልላችሁም ምክንያቱም እነዚህ የራስ ኩራት ወይም ራስን ከፍ የማድረግ ጨዋታዎች እንደሆኑ አውቃለሁ፡፡ እኔ እንደማንኛውም ሰው ተራ ወይም እንደ ማንኛውም ሰው ፍፁም ልዩ ነኝ፡፡

በህልውና ውስጥ አንዷ የሳር ሰበዝ ከትልቋ ኮከብ ጋር እኩል ጠቀሜታ እና ውበት አላት፡፡ በህልውና ውስጥ ተዋረድ የለም፡፡ ከፍተኛና ዝቅተኛ ብሎ ነገር የለም፡፡ እኔ ማንንም አልቃወምም፡፡ ነገር ግን የእኔ ዋና ስራ በሽታዎችን፣ እንቅፋቶችን በሙሉ ገልጦ ማሳየት ነው፡፡ ስለዚህም በእነዚህ ሳንካዎች አትያዙም፤ ነፃ ትሆናላችሁ ፤ ያለ ምንም እንቅፋት ከህልውና ጋር ትዋሃዳላችሁ፡፡ አንደኛው እንቅፋት ደግሞ ራስን ከፍ አድርጐ መመልከት ነው፡፡ እንደሚያታልላችሁ ካልነቃችሁ በብዙ መንገድ ይመጣባችኋል፡፡ እንደ ጥላ ጠንክሮ ሊከተላችሁ እና ነቅታችሁ ላታዩት ትችላላችሁ፡፡

በርግጥ ልታስወግዱት ከታገላችሁ እየጠነከረ ይሄዳል።ከአንድ ነገር ጋር ስትታገሉ የሚከሰተው ይህ ነው:: ወሲብ ሊሆን ይችላል፤ኢጎ ሊሆን ይችላል፡፡ ከመታገል በቀር ምን ልታደርጉት ትችላላችሁ? በሃይል ትገፉታላችሁ፤ ነገር ግን ወዴት ነው የምትገፉት የበለጠ በገፋችሁት ቁጥር የበለጠ ወደ ውስጣችሁ ይገባል ወደ ድብቁ ህሊና ጠልቆ የገባ ደግሞ ከንቃት ህሊና የበለጠ ሃይል አለው:: ድብቁ ህሊና ከንቁው ህሊና በዘጠኝ እጅ ይበልጣል፡፡ በንቃተ ህሊናችሁ ውስጥ ቢያንስ ምን እንዳለ ታውቃላችሁ:: ድብቁ አዕምሯችሁ ግን ጨለማ በመሆኑ በውስጡ ምን እንዳለ አታውቁም፤ ይሁንና ከንቁው ህሊና ዘጠኝ እጅ የሚልቅ ሃይል አለው፡፡ በማንኛውም ቅፅበት ንቁው ጥረታችሁን ሊውጠው ይችላል፡፡

ይህን ንቃት ነው የማስተምራችሁ:: ከራስ ወዳድነት፣ ከብስጭት፣ ከቅናት፣ ከጥላቻ ጋር አትታገሉ፡፡ ሃይማኖቶተኞች «ታገሏቸው፣ አጥፏቸው፣ ግደሏቸው፤ ጠላቶቻችሁ ናቸው›› እያሉ ይሰብኳችኋል፡፡ ልትገድሏቸው አትችሉም፣ ልታጠፏቸው አትችሉም፣ ልትታገሏቸው አትችሉም - በንቃት ልትመለከቷቸው እንጂ፡፡

ንቁ በሆናችሁ ቅፅበት እነዚህ ሁሉ ነገሮች ይጠፋሉ፡፡ በብርሃን ውስጥ ጨለማ አይኖርም፡፡

@zephilosophy




Forward from: የስብዕና ልህቀት
ቀስ በቀስ የምታጡት ነገር!

አላግባብ የአስተዳደራችሁትን (manage ያላደረጋችሁትን ወይም mismanage ያደረጋችሁትን) ነገር ቀስ በቀስ ታጡታላችሁ፡፡

በእጃችሁ ያለው የገንዘብ መጠን በዛም አነሰም፣ በትክክል manage ካደረጋችሁት ትጠብቁታላች፣ ታባዙትማላችሁ፡፡ አለዚያ ግን ቀስ በቀስ ከእጃችሁ ይወጣል፡፡

የእኔ ናቸው የምትሏቸው ቤተሰቦች፣ ቀድሞውኑ (by default) የእናንተ ስለሆኑ ብቻ የትም አይሄዱም ብላችሁ ችላ ካላችኋቸውና ግንኙነታችሁን በትክክል manage ካላደረጋችሁት ትዳርም ሆነ የቅርብ ቤተሰብ ሁኔታ ቀስ በቀስ ከእጃችሁ መውጣት መጀመሩ አይቀርም፡፡

በነጻ የተሰጣችሁ ጤንነት የተሰኘውን የፈጣሪ ስጦታ፣ ስሜትን በሚገባ በመያዝ፣ በጥሩ አመጋገብ፣ በስፖርትና በበቂ እረፍት በትክክል manage ካላደረጋችሁት፣ በኋላ ካጣችሁት በኋላ ነው የምትባንኑት፡፡ አብዛኛው ጊዜ ደግሞ ስትባንኑ ሁኔታውን ለመቀልበስ ጊዜው አንዳለፈበት ትገነዘባላችሁ፡፡

የምትመሩትና የምታስተዳድሩት የሰው ኃይልም ሆነ ሕዝብ በትክክል ካላስተዳደራችሁት (mismanage ካደረጋችሁት) አብሮነቱንና አጋርነቱን ቀስ በቀስ እያጣችሁት መሄዳችሁ አይቀርም፡፡

የጀመራችሁት ንግድ (business) ትንሽም ሆነ ትልቅ፣ በትክክል manage ካደረጋችሁት ታሳድጉታላች፡፡ ካላደረካችት ደግሞ ቀስ በቀስ እያሽቆለቆለ ይሄዳል፡፡

እያለ መርሁ ከብዙ ዘርፎች አንጻር እውነታነቱ ያው ነው፡፡

አንድን ነገር በትክክል manage ማድረግ ማለት፣ ትክክለኛውን መርህ መከተል፣ በእቅድ መኖር፣ ስህተት ሲኖር ቶሎ ማረም እና የመሳሰሉትን አስፈላጊ ሂደቶች ተግባራዊ ማድረግ ማለት ነው፡፡

ዶ/ር እዮብ ማሞ


Forward from: ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy
የጠየቁ ተሻግረው አሻገሩን

ስንቱ ይሁን የፖሟ ፍሬ ስትወድቅ እየተመለከተ “ለምን? እና እንዴት? ሳይል ያለፈ! አንድ ሰው ግን ጠየቀ፤ አይዛክ ኒውተን፡፡ ኒውተን አእምሮቸውን በተገቢው ተጠቅመው ማለትም ማወቅን ሽተው፣ ያወቁትንም ለወግ አብቅተውና ለማዕረግ አድርሰው ከራሳቸው አልፎ ለሌሎች ከተረፉት መካከል በምሳሌነት ሊነሳ የሚችል ግለሰብ ነው። ይህ ሳይንቲስት “በምን ምክንያት?፣ ከምን የተነሳ?' ብሎ፤ በመጠየቅ መንገድ ተጉዞ ምላሾችን ፈለገና ስለ መሬት ስበት እንዲገባን አደረገን። የፍጥነት እና የኃይል ምጥነት እንዲሁም የአድራጊ እና ተደራጊ እኩልነት ሕጎችን አጥንቶ ሚስጥራትን ገለጠልን። ይህን ማድረግ የቻለው አእምሮን በሚገባ ለመጠቀም ከሚያስችሉ መንገዶች መካከል የብልህ ምርጫ የሆነውን መጠየቅን በመምረጡ ነው ብዬ አምናለሁ፡፡

ይህን መንገድ በመምረጥ ብልህነታቸውን ካስመስከሩ መሃከል በምሳሌነት ኒውተንን ብጠቅስም በተመሳሳይ በመጠየቅ መንገድ ተራምደው መዳረሻቸውን ተሻጋሪ እና አሻጋሪ ያደረጉ ሌሎችም አሉ። ኾኖም አሳዛኙ ነገር ለተፈጠረባቸው ጥያቄ መልስ ለማግኝት ዳክረው እውቀትን ያገኙ ሳይንቲስቶች፣ ተመራማሪዎች፣ ፈላስፎች በርካታ አሊያም በቂ የሚባል አለመሆናቸው ነው። ግና ቀደም ብዬ እንደገለጽኩት እኚህ በቁጥር ውስን የሆኑ ብልሆች ለምን እንዴት የት ብለው በመጠየቃቸው እና ጥቂት የማይባል ምላሾችን ፈልገው በማግኝታቸው ዓለመ ሰማያትን፣ ምድራችንን እና ማንነታችንን እንድናውቅ ረድተውናል፤ እየረዱንም ይገኛሉ፡፡ ከተፈጥሮ ጋር ተስማምተን እንዴት ዘላቂ መሆን እንደምንችል በምርምር ውጤታቸው አስተምረውናል። ታመን እንድንድን እና እድሜያችንን እንዲዘልቅ መንገድ ጠርገውልናል። ኑሯችን በኋላቀርነት ገመድ ተተብትቦ እንዳይቀር፣ አኗኗራችን ምቹ እንዲሆን፣ እመርታችን እንዲጎለብት እና ዕይታችን እንዲሰፋ አድርገዋል።

አሁንም ቢኾን የመጠየቅ ጉዞን መከተል እንዳለበት ተረድቶ የወሰነ እንዲሁም ወስኖ መራመድ የጀመረ ሰው መዳረሻው ከላይ በምሳሌነት ካየነው የኒውተን ታሪክ የተለየ አይሆንም። እንግዲህ ይህን ያወቀ ተጓዥ በጨለማ ውስጥ ብርሃን ማግኝት እንደሚችል ያምናል፤ ያውቃልም። ይህ መንገደኛ ማምለጫ የለሽ በሚመስል ወጥመድ ውስጥ ቢገኝ እንኳን መውጫ እና ማምለጫ ዘዴን ያበጃል እንጂ በፍጹም ተስፋ አይቆርጥም፡፡ እንዲህ ዓይነት ተራማጅ ሰው መሬት ላይ የማያወርደው ህልም እንደሌለው ከእውነቶቹ አንዱ ነው፡፡ ወደ ኋላ ሊጎቱት የሚችሉ እልፍ አእላፍ ነገሮች እንደሚገጥሙት ቀድሞዎንም ያውቃል። ነገር ግን መሮጥ ቢያቅተው ተራምዶ፣ መራመድ ቢሳነው ተንፏቆ፣ መንፏቀቅ ቢያቅተው ወደ ፊት ወድቆ ካለመበት ይደርሳል፤ አሸናፊም ይሆናል። አሸናፊም ሲሆን ከራሱ አልፎ ለብዙዎች በነገሮቹ ኹሉ ይተርፋል።

✍️ፍሬው ማሩፍ
📚ጥያቄዎቹ

@zephilosophy


Forward from: ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy
ቡድናዊነት በድናዊነት?
ብርሀን ደርበው

የምንከተለው ፋሽን፣ የሚያስቁን ቀልዶች የምንወዳቸው ሙዚቃዎች ወዘተ ወዘተ... እውን የወደድነው የምንወደውን ነው? የምናደርገው ሁሉ በራሳችን ውሳኔ እና ፍላጎት የተደረገ ወይስ ቀልብያችን የሚለን ሌላ ሆኖ አንዳች ኃይል አስገድዶን?

አንዳንዴ እራሴን እንዲህ ብዬ ጠይቃለሁ የምትከተለው ፋሽን የሚያስቁህ ቀልዶች የምትወዳቸው ሙዚቃዎች ወዘተ ወዘተ... ያንተ ምርጫ ወይስ አንዳች ኃይል አስገድዶህ ምትመርጠው? እውን የወደድከው ሁሉ የምትወደውን ነው? የምታደርጋቸው ውሳኔዎች ባንተ ፍላጎት በቀልብያህ ፍቃድ ወይስ ሌሎች ስለወደዱት ላለመነጠል በዓለም ውስጥ
መናኒ ላለመሆን?

Solomon Asch የተባለ ሳይኮሎጂስት Confirmity Line Experiment የምትባል የሰውን ልጅ ውሳኔ አሰጣጥ የምትገመግም አንዲት የምትገርም ጥናት አለችው። እነሆ ጥናቱ A,B,C ሲል የሰየማቸውን ሦስት የተለያየ ቁመት ያላቸው መስመሮች አዘጋጀ።

ተሳታፊዎች በተዘጋጀላቸው ክፍል ውስጥ ሁሉም በየተራ የትኛው መስመር ረዥም እንደሆነ ጮክ ብለው ይናገራሉ። ታድያ ይሄ ሁሉ ሲሆን ክፍሉ ውስጥ በየዙሩ ከሚገኙት ተሳታፊዎች ከአንዱ ወይ ከሁለቱ በቀር ሁሉም ተዋናያን(ሆን ብለው ስህተት የሆነውን እንዲመርጡ) ይሆኑና በመጨረሻ የተቀረው መልሱን እንዲመልስ ይደረጋል።

ታድያ ውጤቱም ከቅጥረኛ ተዋናያን ጋር ከነበሩት ውስጥ በአማካይ 75% ተሳታፊዎች ቢያንስ አንዴ ስህተት የሆነ መልስ ሰጥተዋል። በአንጻሩ ያላንዳች ተጽእኖ ለብቻቸውን (control group) የመለሱ ተሳታፊዎች ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ትክክለኛውን መልስ መልሰዋል።

በጥቅሉ የጥናቱ ውጤት እንደሚያሳየው እውነታው ግልጽ እና እርግጥ ሆኖ ሳለ ከሌሎች ላለመነጠል ሲል እያወቀው አልያም ብዙ ሰው ካለውማ ልክ ነው (ሞት ከአገር ጋር እንቅልፍ ነው እንዲሉ አበው) በማለት ካለው እውነት የብዙኃኑን ስህተት ይቀላቀላል።

ግላዊነት በሚንቆለጳጰስበት በዚህ በዘመነ ሉላዊነት ምንበላውን ምግብ ፣የት መብላት እንዳለብን፣ ምንለብሰውን ልብስ፣ ማንን መጥላት፣ ማንን መደገፍ እንዳለብን ሁሉ ባንድም ይሁን በሌላ መንገድ የሚወስንልን ማህበራዊ ሚድያው ሆኗል። ፍቅራችን አድናቆታችን ጥላቻችን የኛ አይደለም። ከየትኛውም ጊዜ በላቀ የመንጋነት ስነልቡና በዓለም ላይ ተንሰራፍቷል። ሌሎችን ቀድሞ መከተል ሌሎችን እንደመምራት የሚቆጠርበት ዘመን ላይ ነን።

ቡድናዊ አስተሳሰብ የተለየ ሃሳብ ማመንጨትን ፣ በተለየ መንገድ ነገሮችን ተረድቶ የተለየ
መፍትሔ መስጠትን ፣ አዲስ እይታን፣ ልዩ ምልከታን በጥቅሉ በራስ መቆምን የሚገድል
ከቡድን ውጭ ያለን ሁሉ በድን የሚል ምልከታ ነው።

Hannah Arendt የተባለች ፖለቲካል ፊሎሶፊስት Adolf Eichman ስለሚባል የናዚ መኮነን የፍርድ ሂደት ላይ በጻፈችው Eichman in Jerusalem በተባለ መጽሐፏ እንዲህ ትለናለች ‘’The sad truth is that most evil is done by people who had never made up their minds to be good or evil. ‘’

የሚያሳዝነው ብዙ ክፋቶችና ጥፋቶች የተሠሩት ክፉና ደጉን ለይተው ክፋትን በሚፈጽሙ ክፉ ሰዎች እና አረመኔዎች ሳይሆን ኢየሱስ “የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው።” እንዳለው የሚያደርጉትን ሁሉ አስበውበት ሳይሆን አሳስበዋቸው በፈጸሙ ፤ ስማ በለው በሚመራቸው ጆሯቸው የአእምሮዋቸውን ቦታ በተካባቸው ብኩኖች ነው።

ከሶቅራጥስ ግድያ እስከ ክርስቶስ ስቅላት፣ከጆርዳኖ ቡሩኖ ቃጠሎ እስከ ስልሣዎቹ መረሸን፤ ከናዚ የዘር ፍጅት እስከ አገራችን ፍጅት በፍራቻ በጥላቻ ና በስጋት
ቡድኖች በባህል በፖለቲካ እና በሃይማኖት ስም የመንጋ ውሳኔዎችን በማስተላለፍ ታላቅ ጥፋት
አድርሰዋል እያደረሱም ነው።

ብዙኃንን መከተል ለምን?

የሰው ልጅ ተፈጥሮ(Human natures need to belong) Aristotile(አርስጣጣሊስ) Man is by nature a social animal ሰው በተፈጥሮው ማህበራዊ እንስሣ ነው ይለናል።

በሰው ልጅ ዝግመተ ለውጥ ውስጥ ለአደን ለመሄድም ሆነ ከአራዊት ጥቃት እራስን ለማዳን የሰው ልጅ ሕይወቱን ለማስቀጠል የሄደበት መንገድ በቡድን መሆንን ነው። ታድያ በስነ ተረክ እና በባህል ተጠቅሞ ኃይልን ለማንበር ፣ ሰላምን ለማስፈን እና ነውጥን ለመግራት የሚያደርገው ትግል በ DNAያችን እና በ ንቃት ህሊናችን ውስጥ ስለሚታተም ከመንጋው መነጠል ወደ ሞት መጓዝ ነው ብሎ እንዲያስብ እና እንዲደምድም ያደርዋል።

ታድያ እርግጠኛ ባለመሆን ፤ተቀባይነትን ለማግኘት፤ መጣልን/መገለልን ፍራቻ በጥቅሉ ክብርን ለማግዘፍና ህላዌን ለማስቀጠል ሲል ብዙኃኑን ይከተላል።
የማህበራዊ ሚዲያን መስፋፋት ተከትሎ የዲጂታል መንጋነትም ለመቆጣጠር በማያስችል ሁኔታ እየተስፋፋ ነው። ጭብጨባችን እንኳ የራሳችን አይደለም። የገደል ማሚቶዎች ሆነናል ፤ በቀቀናዊ ማንነትን ተላብሰናል። ነገሩን ተረዱትም አልተረዱትም ሃሳብን በሃሳብ ከመሞገት ይልቅ በስድብ፣በዛቻ እና በማስፈራራት የሚመልሱ ከልቡናቸው/በጣታቸው በኩልም ይሁን በአፋቸው/ ከጸያፍ ነገር በቀር የሌለ የሚመስል ባለማእረግ ተራጋሚዎችን እያፈራን ነው።

ዲጂታል መንጋዎች ተከታዮቻቸው እንዲነኩባቸው አስተያየት እንዲሰጥባቸው አንዳች ትችት እንዲደርስባቸው አይፈልጉም። የሚከተሉትን ሰዎች ከፈጣሪያችው እኩል አንዳንዴም በላይ እንከን የለሽ አድርገው ስለሳሏቸው እነሱን ለነካባቸው እንጦሮንጦስ ድረስ ወርደው በቀል የመሰላቸውን ነገር ለማድረግ ሁሌም ዝግጁ ናቸው።

ኒቼ Beyond Good and Evil መጽሐፉ ላይ እንዲህ ይላል “Insanity in individuals is something rare - but in groups, parties, nations and epochs, it is the rule.” ቡድኖች እብደታቸውን ሕግ ያደርጉታል።

በማህበር ሲታበድ፤ በጎራ ሲወፈፍ፣ በወል ሲነሆለል፤ ስሜት ይነግሣል ምክንያት ቦታ ያጣል። መቃወም ያስወግራል ፣ መለየት ያስቀጣል ፣መሞገት ያሠድዳል፣ መመርመር ያስቀስፋል ። ከኛ ወዲያ ክንደብርቱ ከኛ ወድያ ኃያል ርቱዕ ከኛ ወድያ ጎራሽ... ፣ ከኛ ወዲያ ላሳር ከኛ ወድያ... ። የሁሉ ነገር መለኪያ ፣ የሁሉ ነገር መተኪያ፣ እና ሁሉ ነገር በራሱ እኛ ነን የሚል የተደፈነ አስተሳሰብን ያጸናል።

እኛ ደሞ(የመተርጎም ነጻነቱን ላንባቢው ትተን) መኖርን የሚያክል ጥናት የለምና ኖረን ካየነው እንዲህ እንላለን Even a pacifist in a mob could become a warmonger.
ቡድናዊነት/የመንጋ እሳቤ በግለሰቦች ውስጥ ያለን እውነት፣ ለውጥ ፣ሂደትና ፈጠራ ወደ በድንነት በመለወጥ በራስ መቆምን የሚያሽመደምድ ነው። መንጋነት ሲነግሥ ሰውነት ይረክሳል፣ ፍትሕ ትንጋደዳለች፣ ስልጣኔ አፈር ይበላዋል።የወል እሳቤ ማጤን መመርመርን በጥቅሉ ሰው መሆንን የሚገድል ነቀርሳ ነው።

በጅምላ ማሰብ፤ የሰው ልጅ የመጀመርያው ሞቱ ነው። ቆም ብለህ አስብ።ከእሳቱ ከልለው ከጨለማው የዶሉህን ትተህ የራስህን ሻማ ለኩሰህ ብርሃንህን አብራ።ሰው ሆነህ ሳለህ እራስህን ስለምን ታሳንሳለህ? ራስህን ችለህ አስብ! በራስህ ተጠራ! ሰው ሁን!

ብዙኃን በመንጋ ፣በቡድን፣ በጎራ ሲያስቡና ሲወስኑ ብቻቸውን መቆም የቻሉ ምንኛ የታደሉ ናቸው። የሰውነት ምልአት የመሻገር ከፍታ እነርሱ ጋር ናትና።

ቸር ያቆየን!

Credit to ባይራ ዲጂታል መፅሄት

@Bayradigital
@Zephilosophy


Forward from: መፅሀፍ አለሜ📚📚📖📖
-እንዲህም አለ፦ “I am not God. I am not a Deva.  I am a Human… I am the Awakened one, who has seen the Truth of the world.” በሰውነቱ ውስጥ ያሉትን አተሞች ሁሉ ለመቁጠር በሚያስችል መልኩ ስለ አእምሮው ጥልቅ ትንታኔ አድርጓል።


-“Noting in this world is solid” ለዚህ አባባሉ ዘመናዊ ትርጓሜውን ልተነትን ብነሳ ረጅም ነው። ነገር ግን አሳጥሬው እንዲህ ያለህ ነው፦ ሁሉም ነገር ባዶ ቦታ ባላቸው ጥቃቅን ቅንጣቶች ተከቧል። እና እነዚህ ቅንጣቶች በቋሚ እንቅስቃሴ እና ፍሰት ውስጥ ከሚገኙ ጥቃቅን የኃይል ኳሶች በስተቀር ምንም አይደሉም። የሰው ልጅን ጨምሮ ለትንሽ ነፍሳት የምንታየው ልክ እንዲህ ባለ ኤሌክትሮኒክስ ኃይል ተበታትነን ነው። እናም አንዲት ትንሽ ነፍሳት ስላየችው አንድ ሰው አቋም ብንጠይቃት፤ ጥቃቅን የኤሌትሪክ ኳሶች በአንድ ቦታ ተሰብስበው እንደተመለከተች ነው የምትነግረን።

-ይህ ሰው የሚያገኛቸውን ሰዎች በጠቅላላ ቋንቋቸውን በአንዴ የመልመድ ብቃት ነበረው። ነገር ግን ሁሌም ሲሰበሰቡ የሚናገረው ንግግር የፓሊ ቋንቋ ብቻ ነበር። በጥቅጥቅ ጫካ ውስጥ ተመስጦ ሲያደርግ የትኛውም እንስሳ አይጎዳውም ነበር። እንስሳቱ እሱ ጋር ሲደርሱ ቦዲ ትራዛክሽናቸው እና ኬሚካል ሪአክሽናቸው ይዳከማል። በሜታ
“Amity benevolence” የተጠራቀመው ኃይሉ በእንስሳቱ ላይ እርጋታ ይለቅባቸዋል።

-“Rebirth” የዳግም የመወለድን ጽንሰ ሐሳብ በሰፊው አጋርቷል። ራሱን በራሱ ተመልክቷል እናም በዚህ ህይወት ውስጥ “ቡድሃ:የበራለት” ለመሆን የበቃው ቀደም ባሉት ህይወቶች ሁሉ በሰራቸው መልካም ስራዎች ምክንያት እንደሆነ ደጋግሞ ተናግሯል።

-እንደ አንጉሊማላ ያለ የ999 ሰዎችን ነፍስ ያጠፋ፤ እንደ አምራፓሊ ያለች የከተማዋ ዝሙተኛ ሴት፤ እንደ ሳካካ ያሉ ፀባየ ጥፉ ተከራካሪ እና ቡድሃን በየቀኑ የሚያሽጓጥጠው ሁሉም በጠቅላላ ወደ ሀይማኖቱ ገብተው “አርሃንት” ሆኑ።

-ገና ከልጅነቱ ጀምሮ ቀልድ የማይቀልድ፣ ሐሜት የማይወድ እና በሰው የማያሾፍ ነገር ግን ሁልጊዜ ፊቱ ላይ በሚበራው ፈገግታ ያገኙትን ሁሉ መማረክ የሚችል፤ ድንቁ አስተማሪ ሲድሃርታ ጓተማ ቡድሃ ነበር።

-ቡድሃ አንድ ቀን ለምጽዋት ሲሄድ አንድ ትንሽ ልጅ  ከፊት ለፊቱ አንድ አቧራ የለበሰ ሳህን አነሳ። ቡድሃ በቀስታ ፈገግ አለና የምጽዋውን ሳህኑን ወደ ፊቱ አስጠጋው። ደቀመዝሙሩ አናንዳ የፈገግታውን ምክንያት ምን እንደሆነ ጠየቀው። ቡድሃም፦ “ይህ ልጅ በፓታሊፑታ ከተማ የኔፓሪኒባና ሞት በማስከተል ይሞታል። ከሁለት አመት ተኩል በኋላ እንደገና ይወለዳል። እና ቻካቫቲ “wheel turning” ንጉሠ ነገሥት ይሆናል። እና ለቡድሂስት አገዛዝ ጥቅም 84,000 የብረት ቤተመቅደሶችን በመገንባት ታሪክ ይሰራል። ይሄም ልጅ በነሱ ዘንድ ታላቁ አሾካ የሚባለው ንጉስ ነበር። አሾካም በጣም ጥሩ መልክ የነበረው፣ የተመጠነ ቁመት፣ ሰፊ ትከሻዎች፣ ረጃጅም ጆሮዎች፣ ሰማያዊ አይኖች፣ ፀጉሩ ላይ መለስተኛ ጠባሳ እና በቸርነት እና ምህረት የተሞላ ንጉስ ነበር። ከአስደናቂው ገላው ውስጥ ማራኪ ጠረን እንደሚወጣው ተነግሯል።

-ከቡድሃ ብዙ ደቀ መዛሙርት መካከል አናንዳ የማስታወስ አቅሙ የጎላ እንደነበር ይነገራል። አብዛኞቹ የቀደሙት የቡድሂስት ሱታ ፒታካ ጽሑፎች በአንደኛው የቡድሂስት ምክር ቤት የቡድሃ ትምህርቶችን ጨምሮ አንድ ላይ ለአስተምህሮ ያበቃው አናንዳ ነው።

-ዛሬ የቡድሃ ሃይማኖት እጅግ በጣም ሳይንሳዊ አስምህሮ ተደርጎ ይወሰዳል። እና አንዳንድ ልዩነቶችም እንዳሉ መካድ አያስፈልግም። በጊዜ ሂደት የተከሰተ ነው። ቡድሃ የሰጠው የአዕምሮ እና የአካል እውቀት የልቡ እምነት እውነታ እንጂ ለየትኛውም የሃይማኖት ህግጋት የሚውል አስተምህሮ አልነበረም!።

-አናንዳ ከመነኩሴው ቡድሃ የህይወት ክህሎት በመነሳት፤ ሁል ጊዜ ቢሆን ይጾማል እናም እስከ ፓሪኒባና ድረስ በባዶ እግሩ ረጅም ርቀት በመጓዝ ያስተምርም ነበር። መገለጥን ካገኘ በኋላ ከቤተሰቡ ጋር ተገናኘና አባቱን፣ እናቱን፣ አሳዳጊ እናቱን፣ ሚስቱን እና ልጁን ወደ ኒባና መራቸው። የአገሩ ሰዎች ሲናገሩ እንደነሱ አይነት ደስተኛ ቤተሰብ አጋጥሞን አያውቅም ይላሉ። የዚህ ሁሉ ስነ መሠረት የሆነው መምህሩ  ቡድሃ ታላቁ ሳይንቲስት ከ2600 ዓመታት በፊት የተወለደ ሲድሃርታ ጓተማ ነበር፤ የእሱን ፈለግ የተከተሉት ሰዎች በጠቅላላ የመገለል፣ የመረጋጋት አስተምህሮ እናም ደግሞ የተመስጦ ቴክኒኮችን አሁንም በመተግበር ላይ ይገኛሉ ይህም በዓለም ዙሪያ አድናቆት ያለው ስብስብ ነበር።

-በቡድሃ ውስጥ በጣም የሚያስደንቀው ነገር ከምቾት ቀጠና ወጥቶ እውነትን የፈለገ ብቸኛ ሰው መሆኑ ነው። ይህ ብሩህ አእምሮ ያለው ሰው አምላክም አይደለም፣ ነቢይም አይደለም፣ እሱ ተፈጥሮውን የተረዳ አንድ ሰው ነው። ታድያ እንደ ሰው ኖረና ሞተ። በሃይማኖቱ ውስጥ የገነት ተስፋ የለም፤ የገሃነም ስጋት አልተቀመጠም። ለመጸለይ አገልግሎት የተቀመጠ መፅሃፍ የለም። እሱንም መከተል ግዴታ አልተደረገም። ምንም አስገዳጅ የአምልኮ ሥርዓቶች አልተቀመጡም። ብቻ የቡድሃን ትምህርቶች መከተል አንድ ሰው የተሻለ ሰው ያደርገዋል። “ድሃማ” የሚባለው አስተምህሮቱን አንድ ሰው መማር ካልፈለገ አይጎዳውም፤ ነገር ግን እሱ ወይም እሷ የተሻለ ሰው የመሆን እድላቸውን ያጣሉ!።


Forward from: ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy
"ብዙሀኑን የሚያታልል ጌታቸው ይሆናል ፤ ከዓይናቸው ላይ ቅዠትን ለማጥራት የሚሞክረው መቀጣጫ ይሆናል!።"
ኒቼ
 @zephilosophy


ዶናልድ ትራምፕ የአፍሪካ መሪዎች ሰው መሆናቸውን እጠራጠራለሁ አሉ‼️

👉🏿 ከ50 ዓመታት የአህጉሪቷ የነጻነት ጉዞ በኋላ፣ ለህዝባችው አስፈላጊውን መሠረተ ልማት ካላሟላችው ሰው ነን ብላችው ታስባላችው?


👉🏿በወርቅ፣ በአልማዝ፣ በነዳጅ፣ በዩራኒየም፣ በብረት፣ በማዕድን፣ በብር፣ በማግኒዥየም፣ በነሐስ፣ በጋዝ የተፈጥሮ ሃብቶቻችው ላይ ተቀምጣችው፣ ህዝባችው በረሃብ፣ በትምህርት አለመዳረስ፣ በጤና አገልግሎት እጦት፣ ቢሞት፣ ሰው ነን ብላችው ታምናላችው?

👉🏿በስልጣን ላይ ቆይታችው፣የራሳችሁን  ዜጎች ለመግደል ከውጭ የጦር መሣሪያዎችን ስታስገቡ፣ ሰው ነን ብላችው ታስባላችው?

👉🏿የገዛ ዜጎቻችሁን እንደውሻ ስታንገላቱና ስትገድሉ፣ ማን ዜጎቻችሁን እንዲያከብር  ትጠብቃላችው?

👉🏿በራሳችው  አገር ላይ ቀማኛና ሌባ በመሆናችው ፣ የሃገራችሁን  ሀብቶች ሁሉ በመስረቅ፣ አብዛኞቹ ዜጋዎቻችው በስደትና በድህነት ውስጥ እንዲያልፉ ስታረጉ፣ የሰው ልጆ ነን ብላችው ታስባላችው?
ትራምፕ ይሄን የተናገሩት ሰሞኑን በዋሽንግተን ዋይት ሀውስ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ መሆኑን ተመልክቻለሁ።
[አዩዘሀበሻ]
===================


Forward from: የስብዕና ልህቀት
አንዳንዴ . . . ያለ ነው!

አንዳንድ ጊዜ ማመንታት ያለ ነው - በፍጹም ግን ወደ ኋላ አንመለስም!

አንዳንድ ጊዜ መፍራት ያለ ነው - በፍጹም ግን አንንበረከክም!

አንዳንድ ጊዜ ተስፋ መቁረጥ ያለ ነው - በፍጹም ግን አናቆምም!

አንዳንድ ጊዜ መሸነፍ ያለ ነው - በፍጹም ግን ሕይወት ከሚያቀብለን የየእለት ጦርነት አንሸሽም!

አንዳንድ ጊዜ መድከም ያለ ነው - በፍጹም ግን ዝለን አንወድቅም!

አንዳንድ ጊዜ ግራ መጋባት ያለ ነው - በፍጹም ግን አንቅበዘበዘም!

አንዳንድ ጊዜ በሰው መገፋት ያለ ነው - በፍጹም ግን ከዚያ ሰው ውጪ መኖር አየቅተንም!

አንዳንድ ጊዜ ድብርት ያለ ነው - በፍጹም ግን ደንዝዘን አንቀርም!

አንዳንድ ጊዜ ለጥያቄ መልስ ያለማግኘት ያለ ነው - በፍጹም ግን ከመጠየቅ አናርፍም!

አንዳንድ ጊዜ ክፋት ያሸነፈ መምሰሉ ያለ ነው - በፍጹም ግን መልካምነትን አንጥልም!

@Human_Intelligence
@Human_Intelligence


Forward from: ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy
ኑሮ አያሻግርም!

እኮ ማነው!
የሰውነት ድልድይ እንዲህ እየፈረሰ፣
የሰውነት መንገድ እንዲህ እየሻከረ፣
መንገዱን ሊያስውብ  እንዲህ ያሳመረ?
ይልቅ ንገሩልኝ!!
ለእንደኔ ዓይነቱ ሰው፤
በግርግር ደቦ ትልሙ ለፈረሰ፤
የአበባ ዘመኑን በነጠላ መንገድ ሲጓዝ ለጨረሰ፡፡
በቁስ መደራረብ፣
            በዜና ጋጋታ ተስፋ አይሰፈርም፤
“አስፓልት” እግር እንጂ ኑሮ አያሻግርም!

በረከት በላይነህ
የመንፈስ ከፍታ

@Zephilosophy

20 last posts shown.