CHRIST TUBE - ETH🇪🇹


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


"ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ፥ ሞትም ጥቅም ነውና።"
(ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 1:21)
🔍 የዚህ ቻናል አላማ ኢየሱስ ክርስቶስን መስበክ ነው፡፡
📌 በተጨማሪም
◈ኢየሱስን የሚያስናፍቁ ድንቅ ዝማሬዎች
◈ስለ ክርስቶስ የሚያሳስቡ ዘመን ተሻጋሪ መልክቶች
◈መፅሐፍ ቅዱሳዊ ጥያቄዎችና
◈ተስፋ ሰጪ ሀሳቦች ይቀርብበታል
✍️ ለሀሳብ እና አስተያየት👇
📩 @Christ_Tube_Bot
Creator @Beki_MW

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций




#የማለዳ_ቃል 🌤☀️

“ፊቴም ወደ እናንተ ይሆናል፥ እንድታፈሩም አደርጋችኋለሁ፥ አበዛችሁማለሁ፤ ቃል ኪዳኔንም ከእናንተ ጋር አጸናለሁ።”
  — ዘሌዋውያን 26፥9

መልካም ቀን !

ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ ነው
SHARE | @CHRIST_TUBE
SHARE | @CHRISTFAMILY


#የማለዳ_ቃል 🌤☀️

“እኔ ተኛሁ አንቀላፋሁም፤ እግዚአብሔርም ደግፎኛልና ነቃሁ።”
  — መዝሙር 3፥5

መኖር የቀለለው ለመኖር ምክኒያት ይሆነው ዘንድ አይኑን ከድኖ ቅስበታዊ በሆነ መንገድ ገልጦ መንቃት ችሏል ይህም በእግዚአብሔር ምህረት ተፈቅዶልናል እግዚአብሔር ይመስገን!!

እንደምን አደራችሁ ውዶች!

ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ ነው
SHARE | @CHRIST_TUBE
SHARE | @CHRISTFAMILY


ይነጋል!

ዝናብ ሲመጣ ደመና እንደሚያቀላ
ጨለማ ሲመጣ ጨረቃ እንደሚወጣ
ብርሃን ሲመጣ ፀሀይ እንደሚያፈካ ሁሉ

ጨለማው እንደ ጨለመ አይቀርም በእግዚአብሔር ብርሃን መንጋቱ አይቀርም ይነጋል!

ብሩህ ምሽት!

ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ ነው
SHARE | @CHRIST_TUBE
SHARE | @CHRISTFAMILY


#የማለዳ_ቃል 🌤☀️

“ጭንቀት ቀርባለችና የሚረዳኝም የለምና ከእኔ አትራቅ።”
  — መዝሙር 22፥11

መልካም ቀን !

ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ ነው
SHARE | @CHRIST_TUBE
SHARE | @CHRISTFAMILY


📚ርዕስ:- በተአምራትህ አምናለው
📝ጽሑፍ :- ካትሪን ኩልማን
📝ትርጉም ፦ሙሉ ደቦጭ
👏የገፅ ብዛት:- 108
#ክፍል29
ቀጣይ ባለታሪክ፦ሮዝ
═══════════

ይቀጥላል..........

ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ ነው
SHARE | @CHRIST_TUBE
SHARE | @CHRISTFAMILY

              


📚ርዕስ:- በተአምራትህ አምናለው
📝ጽሑፍ :- ካትሪን ኩልማን
📝ትርጉም ፦ሙሉ ደቦጭ
👏የገፅ ብዛት:- 108
#ክፍል28
  ባለታሪክ፦ሜሪ ሸሚትስ
═══════════

ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ ነው
SHARE | @CHRIST_TUBE
SHARE | @CHRISTFAMILY

              


📚ርዕስ:- በተአምራትህ አምናለው
📝ጽሑፍ :- ካትሪን ኩልማን
📝ትርጉም ፦ሙሉ ደቦጭ
👏የገፅ ብዛት:- 108
#ክፍል27
  ባለታሪክ፦ሜሪ ሸሚትስ
═══════════

ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ ነው
SHARE | @CHRIST_TUBE
SHARE | @CHRISTFAMILY

              


📚ርዕስ:- በተአምራትህ አምናለው
📝ጽሑፍ :- ካትሪን ኩልማን
📝ትርጉም ፦ሙሉ ደቦጭ
👏የገፅ ብዛት:- 108
#ክፍል26
  ባለታሪክ፦ሜሪ ሸሚትስ
═══════════

ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ ነው
SHARE | @CHRIST_TUBE
SHARE | @CHRISTFAMILY

              


#የማለዳ_ቃል 🌤☀️

“ልጄ ሆይ፥ ልብህን ስጠኝ፥ ዓይኖችህም መንገዴን ይውደዱ።”
  — ምሳሌ 23፥26

መልካም ቀን !

ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ ነው
SHARE | @CHRIST_TUBE
SHARE | @CHRISTFAMILY


የቅርብ!

የቅርቤ የተባለው ሁሉ እንድ ቀን ቅርብ መሆኑን ትቶ ሩቅ ይሆናል።

እኔ ግን የሚገርመኝ ጊዜው ቢሄድ፣ እድሜ ቢገፋ፣ ዕውቀት ባይኖርም፣ መልክና ቁመና ባይኖርም፣ ቅርብ ለመሆን ምንም አይነት መስፈርት ያላስቀመጠ
ጌታ!

ሁሉ ያየብንን ጉድፍ አይቶ ሲሸሽና ሲያጋልጥ እርሱ ግን ያየብንን የማያሳይብን!

የገዛ ልባችን አልታመን ሲል እርሱ ግን እንደ ታመነ የሚቆይ!

እኔ አንድ ነገር አውቄአለሁ ልጅ እያለው፣ እሁንም ወጣት ሆኜ፣ አቅም እንሶኝ እርጅና ቢመጣም፣ እግዚአብሔር ቅርብ ነው።



“ጌታ ቅርብ ነው..............”
  — ፊልጵስዩስ 4፥6


መልካም ቀን !

ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ ነው
SHARE | @CHRIST_TUBE
SHARE | @CHRISTFAMILY


#የማለዳ_ቃል 🌤☀️

“እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ቃሌን የሚጠብቅ ቢኖር ለዘላለም ሞትን አያይም።”
  — ዮሐንስ 8፥51


መልካም ቀን !

ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ ነው
SHARE | @CHRIST_TUBE
SHARE | @CHRISTFAMILY


እግዚአብሔር ምርጫን የሚፈቅድልን፣ እያንዳንዱን የመንፈስ ፍሬ በተቃራኒ ሁኔታ በመጠቀም ነው። መጥፎ ለመሆን ተፈትነህ የማታውቅ ከሆንክ፣ጥሩ ሰው ነኝ ለማለት አትችልም። ታማኝነትህን በሚፈትን አጋጣሚ ውስጥ ካላለፍክ፣ ታማኝ ነኝ ማለቱ ይሳንሃል። ሀቀኝነት፣እምነት የማጉደል ፈተናን በማሸነፍ ይገነባል፣ ትህትና የሚያድገው ደግሞ መታበይ አሻፈረኝ ሲባል ነው። ጽናት የሚያድገው ተስፋ ቆርጠህ እንድትተወው ለሚያደርግህ ፈተና የማትበገር በሆንህ ጊዜ ሁሉ ነው። አንድን ፈተና ድል ባደረግህ ጊዜ ሁሉ ይበልጥ ኢየሱስን እየመሰልክ ትሄዳለህ።


መልካም ምሽት !

እወዳችኋለሁ!❤❤

ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ ነው
SHARE | @CHRIST_TUBE
SHARE | @CHRISTFAMILY


#የማለዳ_ቃል 🌤☀️

“እግዚአብሔርን ፈልጉት ትጸናላችሁም፤ ሁልጊዜ ፊቱን ፈልጉ።”
  — መዝሙር 105፥4

መልካም ቀን !

ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ ነው
SHARE | @CHRIST_TUBE
SHARE | @CHRISTFAMILY


ቅርብ ወራጅ!

አንዲት እናት በጠዋት ተነስታ ወደ ስራዋ ለመሔድ ትራንስፖርት ትጠብቃለች ነገር ግን ታክሲ ስላላገኘች በባስ ቦታ አግኝታ ትሔዳለች ከአጠገቧ ባዶ ቦታ
ስለ ነበር የሆነች ወጣት ልትቀመጥ ብላ በያዘችው ጥላ ሹል ስለነበር በስለቱ እጇን ትተረትራታለች ከእናትየውም ትንሽ የማይባል ደም ይፈሳል እንደገና ቁጭ ልትል ስትልም ገፈተረቻት ተረጋግታ ተቀምጣ ሳለች ይህች ወጣት ዞር ስትል ከእናትየው ምንም አይነት ቁጣ የተኮሳተረ ፊት አላሳየቻትም ለዚህም ጨንቋት "ለምን አልተቆጡኝም "ለምንስ አይናገሩኝም "ስትል ትጠይቃቸዋለች በዚህ ጊዜ የእዚህች እናት መልስ ልቧን አስደነገጠው...."ቅርብ ወራጅ ነኝ!! "ስትል ትመልስላታች።


ረጅም ጉዞ የምንጓዝ መስሎን በምድር ላይ በማይሆን በሚሆን ስንጨቃጨቅ አንተነህ አንቺ ነሽ ብለን እጅ ስንቀሳሰር በዘር በሀይማኖት ጥምብርቁሳችን ሲወጣ ጥልና ክርክር መለያየት አድማ ገኖ በሁሉ በዝቶ የፍቅር ውሀ ጠምቶት ወንድም ሲመጣ ምላሹ የጥላቻ ውሀ ስናጠጣው ይቅር ማለት መተው ትተን ቂማችንን በጀርባችን ተሸክመን ለመሔድ ለምን ወሰንን? እኮ ለምኔ ይሁሉ? ማቴው ሄነሪ እንዲህ አሉ"እያንዳንዱ ቀን ጉዳያችን ሊሆን የሚገባው ነገር ለመጨረሻ እለታችን መዘጋጀት ነው።"

....ለካ እረስተነው ነው አንጂ ሁላችንም ቅርብ ወራጅ ነን!

" የብርሃኑ ፍሬ በበጎነትና በጽድቅ በእውነትም ሁሉ ነውና ለጌታ ደስ የሚያሰኘውን እየመረመራችሁ፥ እንደ ብርሃን ልጆች ተመላለሱ፤"
-ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5: 9-10

#ትንሽ እንደሚቀረው ፣ብዙ እንደማይሔድ፣በቅርቡ እንደሚቆም፣ እያሰብን በብርሃን እንመላለስ !!!መልዕክቴ ነው


✍ Meron [@mercy1te]
      ተወዳጆች ተባረኩ! 👐


ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ ነው
@CHRIST_TUBE
@CHRISTFAMILY
ሼር በማድረግ ለሌሎች ያድርሱ!


ሰላም የተወደዳችሁ ወንድም እህቶቼ እህታችሁ ✍ሳባ ካሳሁን  ነኝ እስቲ ዛሬ በአንድ ርዕስ ላይ ትንሽ ልበላችሁ

  በህይወቴ በጣም በተደጋጋሚ የማሳልፋቸውን ነገሮች በዲያሪ ላይ ከማስፈር ይልቅ ለአንድ ሰው ማውራት ማካፈልን እመርጣለሁ አሁን የማወራችሁ

*እግዚያብሄር የቅርብ ነው
በሚል ርዕስ ላይ ነው።

ይህን ስታነቡ ዛሬ እንደልማድ እንድትኖሩ አይደለም ይህን ሚስጥር ያወቀ ማንኛውም ሰው
1.ህይወቱን አሳልፎ ለሚያምነው አምላክ ይሰጣል
2.በህይወቱ ስለሆነው እየሆነ ስላለው ስለሚሆነውም ነገር ፈፅሞ አይሰጋም
3.በየትኛውም ሰዐት በየትኛውም ቦታ በማን እንደሚመካ ሰለሚያውቅ አያፍርም
4.በችግሩ ሰዐት ሁሉ ጌታውን ያናግራል

በዚህ ዙሪያ አንድ ምስክርነትን ላካፍላችሁ: አንድ ለሊት ድንገት ከእንቅልፌ ባነንኩ ስባንን ራሴን ማታ እንደተኛችው ሳባ አላገኘሁትም መተንፈስ ልክ እንደሰማይ የምናውቀው የምናየው ግን የማናገኘው እንዲሁ የሚናፍቀን ብቻ ሆኖብኛል መጮህና ማልቀስ ጀመርኩ ሲፃፍ ወይ ሲወራ ይቀላል ሲገጥም ግን የሚያልፍ አይመስልም
በዚያ ሰዐት እንደ ክርስትያን ምን ማድረግ ነበረብኝ?
እየሮጥኩ ከአልጋዬ ወርጄ ቤተሰቦቼን ሁሉ ቀስቅሼ በእምባ የራሰ ፊቴን እየጠራረኩ እጆቻቸውን ይዤ በልቤ አምላኬ ሆይ እኔን ልትወስደኝ ነው እነርሱን ግን ጠብቅልኝ ብዬ ራሴን ለመሞት አዘጋጀሁ አባቴ ግን እጆቹን ጭኖ የኢየሱስን ስም ደጋግሞ እየጠራ አሁን ሄደሽ ተኚ አለኝ እኔም እየፈራሁ ጋደም አልኩ በዚያ ሰዐት እርግጠኛነቴ መሞቴ ላይ እንጂ ክርስቶስ ላይ አልነበረም። እግዚያብሔር ይመስገን ያ አስጨናቂ ለሊት ነግቶ በድጋሚ ስነቃ የከበበኝ የሞት ጭለማ ጠፍቶ በክርስቶስ ብርሀን ተሻግሬያለሁ።. . .

እግዚያብሔርን ያመነ ሰው ውድቀትን አይፈራም ሁልጊዜም በአምላኩ ሀሴት ያደርጋል😍😍

አጫጭር ልዩ ልዩ ትምህርት፣ ጥያቄ ከህይወት ተሞክሮዎች ጋር እሁድ ከሰዐት ወደእናንተ እናደርሳለን እናንተም አብሮነታችሁን አሳዩን❤️❤️❤️❤️


አሁንም እኔን መማርህን አያደክምህ❌የወደቁ እጆቼን ከመያዝ ዝለህ የማታውቅ❌ ልቤን ከወረደው ታች ከፍ ከማድረግ ወደኋላ ማታፈገፍግ❌ እንደ ተዉኝ ሰዎች ሰዎች ሳይሆን እንደ ሆንከው እራስህን ሆነህ ያሳየኸኝ
መንገድ ከመንገዴ ርቆ ቢሄድም እንኳ በጠለቁ አይኖችህ ከማየት እቋርጠህ የምታውቅ.............................................................................................................................................................................................................
.........................................................................
.........................................................................
.........................................................................
ብዙ ሚባል እለ ግን ልል የምችለው ኢየሱስ ሆይ እወድሃለው!!❤❤



ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ ነው
SHARE | @CHRIST_TUBE
SHARE | @CHRISTFAMILY


ጫንቃ!

አንድ ትልቅ ሸክም በላዬ ላይ ለመሸከም በጀርባዬ አዝዬ ስንገዳገድ ደረጃውን ለመውረድ ብዙ ትግል ሳደርግ በህልሜ አያለው ያንን ሸክም ተሸክሜ ለመውረድ በጣም ብዙ ጥረትና ልፋት አድርጌአለው ነገር ግን ከባድ ከመሆኑ የተነሳ ሸክሙን ይዤው ልወርድ አልቻልኩም ይህን የተመለከተ አንድ ሰው እንዲህ በማለት ወደ እኔ መጣ "እኔ እቃውን ተሸክሜ ላውርድልሽ እስከየት ድረስ ነው የምትፈልጊው" አለኝ
አኔም ይህን ደረጃ ብቻ አልኩት በማይታመን ፍጥነት ለኔ ከባድ መስሎ የታየኝን ደረጃ በፍጥነት እየተራመደ ሲሔድ ተመለከትኩት ደረጃው ላይ ውሀ ነበረና አንሸራቶት ይወድቃል ግን ተነስቶ አንደገና ደረጃውን ይወርዳል በመጨረሻም ይወረውና ሸክሙን ይጥለዋል
እኔም ትኩር ብዬ ሳየው ለኔ ብሎ የኔን ሸክም መሸከሙ ለኔ ብሎ የኔን ውድቀት አይቶ ለራሱ የረገውን ለኔ ብሎ በጀርባዬ ያዘልኩት ጫንቃዬን ከላዬ አውርዶ ለራሱ ማድረጉ በጣም አስገረመኝ ይህ ብቻ አይደለም እስከመጨረሻው ላላየው አውጥቶ የጣለልኝ በእውነትም ይህ ሰው ሰው ሳይሆን ኢየሱስ መሆኑን ተረዳው የከበደው ሸክሜ በእየሱስ ቀሎ አየሁት

ዛሬም የከበዳችሁን ሸክም ሊያቀልላቹ እየሱስ ይጠይቃችኋል ምላሻቹ ምን ይሆን? አዎን እንካ ውሰደው ወይስ ራሴ በቂ ነኝ ብቻዬን ልታገል ብላቹ ታስባላቹ መልሱ ለእናንተው ይቆይ

እየሱስ ዛሬም እንዲህ ይላቹኃል “እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ።”
  — ማቴዎስ 11፥28

✍️Meron[@mercy1te]
        ተባረኩ👐

ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ ነው
@CHRIST_TUBE
@CHRISTFAMILY
ሼር በማድረግ ለሌሎች ያድርሱ!


የማለዳ_ቃል 🌤☀️

መዝሙር 90
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁴ በማለዳ ምሕረትህን እንጠግባለን፤ በዘመናችን ሁሉ ደስ ይለናል ሐሤትም እናደርጋለን።
¹⁵ መከራ ባሳየኸን ዘመን ፈንታ፥ ክፉም ባየንባቸው ዘመኖች ፋንታ ደስ ይለናል።

መልካም ቀን !

ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ ነው
SHARE | @CHRIST_TUBE
SHARE | @CHRISTFAMILY


"በምንም ሁኔታ ውስጥ ሁኑ እግዚአብሔር ግን እግዚአብሔር ነው!"


አሜን!

ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ ነው
SHARE | @CHRIST_TUBE
SHARE | @CHRISTFAMILY

Показано 20 последних публикаций.