አስኳላ-💚💛❤️


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Психология


እዚህ Channel ላይ ያስተምራሉና ያዝናናሉ ብዬ የማስባቸውን ማንኛውም አይነት ፅሁፎች ከተለያዩ ቦታዎች እየለቀምኩ አቀርባለሁ። ስታነብ ታውቃለህ፣እራስህን ትመለከታለህ፣ክፉና ደጉን ትለያለክ። እዚህ የሚለቀቁ ፅሁፎች እኔ የተናገርኳቸው እና የፃፍኳቸው ብቻ አይደሉም። ከመፃፍ፣ከሶሻል ሚዲያ እና ከተለያዩ ሰዎች የሰበሰብኳቸው ጭምር ናቸው።

Comment▹ @Meklite21

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Психология
Статистика
Фильтр публикаций


ቀረበ አሉኝ ዳግም ገላሽ ለጨረታ
ተገለጠ ሀፍረትሽ ሀፍረትም ተረታ
ዋለ ከአደባባይ ተሽሞንሙኖ ቆዳሽ
ለሚጠጣሽ ሁሉ ያለቅጥ ተቀዳሽ።

ግን እንደው አንቺዬ ..
መፍረድ ቢሳነኝም በፍርዴ 'ባልለካሽ'
መመጠንም ባልችል በስፍር 'ባልተካሽ,
ስልጣኑም ባይኖረኝ ባላዝም በገላሽ
ለአፍታ ልጠይቅሽ.....
ውዱን ማረከሱ እንዴት ነው የደላሽ???

የሴትነት ልኩ...
የሴትነት ልኩ መሸፋፈን ሳለ
በአንቺ ሴትነት ውስጥ መገለጥ ተሳለ

በአዳም ለመታጀብ ፈቅደሽ ከፋፈትሺው
ሞቅ ይበለኝ በሚል አጉል አደረቅሺው
ያስወደደሽ መስሎሽ አስነካሽ ለማንም
እጅጅ ስትይ ኋላ ልታጪው አንዱንም

ይቅር ግድ የለሽም.....
ይቅር ቀነስ አርጊው የትም መጋደሙን
ከሁሉም ተዳርተሽ አታጥፊው ጣዕሙን

አያልቅብኝ እያልሽ.....
ተይ በአደለሽ ገላ አትጫወቺበት
መሽኛሽ ሁኖ ይቀራል ዛሬ የረካሽበት ።



......... @Meklite21
👇👇Telegram channel 👇👇
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee


Репост из: አስኳላ-💚💛❤️
በሂሳብ አታፈቅሪም!

በሰውነት ውስጥ የመውደድ፣ የማፍቀር፣ የመወዳጀት ፀጋ አብሮ ተሰቶናል። ነገር ግን አስበን፣ አውጥተን፣ አውርደን፣ አገናዝበን፣ ተገንዝበን አንወድም። አንዳንዴ ስላንተ አስባ የማታውቅን ሴት ከልብህ አፍቅረህ፣ መናገር አቀቶህ፣ ምላስህ ተሳስሮ፣ ማንነትህ ተቀያይሮ ልትገኝ ትችላለህ። የሆነ ጊዜ መፈጠርሽንም የማያቅ ሰው ወደሽ እርሱን ጥበቃ ሌላውን ህይወትሽን የምትረሺበት ጊዜ ሊፈጠር ይችላል። ፍቅር ሂሳብ አይደለም፤ እንዲሁም ሰቶ መቀበልም አይደለም። ባላሰብሽው መንገድ ከእራስሽ በላይ የምታስቀድሚው ሰው ወደ ህይወትሽ ይገባል፤ ሁሉ ነገርሽን ልትሰጪው ትፈቅጂያለሽ፤ ከጊዜያዊ የደስታ ስሜትሽ ውጪ የሚታይሽ ነገር የለም። በፍቅሩ መዓበል ትወሰጂያለሽ፤ የውቂያኖሱን እንቅስቃሴ የማቆም ሃይል ታጪያለሽ። ፍቅርን ብለሽ መሔድሽ ፍቅርን ለማግኘትሽ ዋስትና አይሆንሽም።

አዎ! ጀግኒት..! በሂሳብ አታፈቅሪም! አመዛዝነሽ የሰው ህይወት ውስጥ አትገቢም። ለዚህም ነው እደማይሆንሽ እያወቅሽ መውደድሽን የማታቆሚው፤ ለዚህም ነው እየተገፋሽ የምትፈለጊበትን ጊዜ በፅናት የመትጠብቂው፤ ለዚህም ነው የደረሰብሽን በደል ሁሉ ችለሽ በፍቅር መታከምን የመረጥሽው። ፍቅር ጥልቅ ስሜት ነው። ታስቦበት የሚደረግ፣ እየታዘዘ የሚኖር፣ በህግና ደንብ የሚመራ አይደለም። ውስጥሽ የተፈጠረው የተለየ ስሜት ፍቅርን ሲጭርብሽ፣ የተለየ ፍላጎትን ሲያስከትል፣ እይታሽን ሲቀይር ትመለከቺያለሽ። በሂሳብ ከመወዳጀት ታቀቢ፤ ይህን ስላለው፣ ያንን ስላለው፣ ይህንን ስለሚያደርግለኝ ከሚል በመስፈርት የተቃኘ ፍቅር ተላቀቂ። በእውነተኛው ስሜትሽ ስትመሪ የእውነት ፍቅርን መኖር፣ በፍቅር መሞላት፣ የፍቅርን ትርጉምም መረዳት ትጀምሪያለሽ።

አዎ! ጀግናዬ..! ፍቅር በፊት ያስቀመጥካቸውን መስፈርቶች አስጥሎ፣ ለእራስህ የሰጠሀውን ክብር አሳንሶ፣ በማትጠብቀው ሰዓት የማይሆን ሰው ላይ ቢጥልህም ማፍቀርህን ላታቆም ትችል ይሆናል፣ እንደማታገኛት እያወክም ከውስጥህ ለማውጣት ይከብድሃል። ለዘመናት ከአንድ ሰው ውጪ ሌላ መመልከት ያልቻሉ፣ በአንድ ሰው ፍቅር የታሰሩ፣ እራሳቸውን የሰወሩ፣ ማንነታቸውን ያስገዙ ሰዎች አሉ። እራሳቸውን መቆጣጠር ሲኖርባቸው ማንነታቸውን በሙሉ የሚሰማቸው ፍቅር እንዲቆጣጠራቸው ያደርጋሉ፤ ህይወታቸውን ቀምቶ በበዶ እንዲያስቀራቸው፣ በጭንቀት ብዛት ሰውነታቸውን እንዲያሳጣቸው ይፈቅዳሉ። የማያፈቅርህን ሰው ታፈቅራለህ ያምሃል፤ ከልብህ ያፈቀርከው፣ በሙሉ ልብህ ያመንከው ሰው ይከዳሃል ይባስ ትታመማለህ። ነገር ግን ይህን አስብ፣ መዝነህ ያልጀመርከው ፍቅር መዝኖ አይከፍልህም፤ እውነት ስታፈቅር አለመፈቀር፣ መከዳት፣ መገፋት አብሮ ሊመጣ እንደሚችል አስታውስ። ከልብህ ወደህ ብትጎዳ፣ በሰውነትህ አፍቅረህ ብትታመም የእውነት ፍቅርን አይተሃልና ዳግም ምላሹን በመጠበቅ እራስህን አታድክም፣ እራስህን አታሳምም። በምትኩ ለአዲሱ የህይወትህ ምዕራፍ እራስህን አዘጋጅ።

መልካም አዳር ይሁንልን!

@
t.me/Asresee
@
t.me/Asresee
@
t.me/Asresee


"እንደ እርጋታ ግን ደስ የሚል ነገር የለም በተናደድክ ሰአት ስትረጋጋ በቃ ሰው ነህ።.....
....... በህይወቴ ብዙ ገራሚ ሰዎችን አይቻለሁ ነገር ግን በተናደደ ሰአት ዝም እንደ ሚል ሰው የበሰለ የለም!.........
ዝም ስትል አዳማጭ ትሆናለህ ፣
ዝም ስትል ብዙ ነገር ትታዘባለህ ፣
ዝም ስትል ትማራለህ ፣
ዝም ስትል ትከበራለህ ፣
ዝም ስትል የሰዎችን ትኩረት ትስባለህ ፣
ዝም ስትል ሰዎች እንጂ አንተ አደለህም ሰዎችን ምትፈልገው ፣ በቃ አንዴ አንዴ ዝም በሉ።"


......... @Meklite21
👇👇Telegram channel 👇👇
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee


ህይወት እኮ መለወጥ እንደምትችል በየጊዜው አንድ የተለየ ነገር እያደረክ ማረጋገጥ ነው።ማፍቀር እንደምትችል አረጋግጠሀል።.....
....መርሳትም እንደምትችል አረጋግጥ።.......
 

መረቅ...
...አዳም ረታ
.... @Asresee
.... @Asresee
.... @Asresee


ዋጋህ ካልገባቸው ሰዎች ጎን ስትቆም አንተ ራስህ ዋጋህን አትረዳውም። ባቀለሉህ እና ዋጋቢስ እንደሆንክ አይነት ስሜት ባሳዩህ ቁጥር አንተም ዋጋቢስ እንደሆንክ የሚነግር መንፈስ ከነጓዙ ይጫንሀል። እውነት ግን ዋጋ አጥተህ ይመስልሀል?....

በእርግጠኝነት ያላወከው ቦታህን ነው። ሻይ ውስጥ ጨው ሆነህ ከገባህ ዋጋ ቢስ ነህ፤ ወጥ ውስጥ እንደ ስኳር ብትነሰነስ ወጡን አታጣፍጥም። በቃ..! ዋጋህን ካጣህበት ከባቢ ላይ አትቁም፤ ክብርህ እየነፈጉህ እያየህ ላለመራቅ ሙጥኝ አትበል። ዞር ብለህ ቦታህን ፈልግ... ልክ ቦታህን ያገኘህ  ዕለት በቦታህ እጅጉ ተፈላጊና ዋጋ ያለው ሰው ነህ።...አለቀ!



.......Abrham F. Yekedas

......... @Meklite21
👇👇Telegram channel 👇👇
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee

755 0 14 1 19

ወዳጄ ለመኖር ብቻ ሳይሆን ለመሞትም ጥሩ ቀን አለው...
.....ሰኞ ስትሞት እና እሁድ ስትሞት ቀብርህ አንድ አይደለም።


[👇Telegram channel 👇
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee


ለምናስተናግዳቸው ስሜቶች ትልቁን ድርሻ ሚወስደው " መጠበቅ " ነው....
    በመጠበቅ ውስጥ የማንቃኘው የስሜት ዓይነት የለም።....
   ያሰብነው ሲሆን ደስታ ፤ ያልገመትነው ሲፈጠር ደግሞ ሀዘንና ንዴት።....
የራሳችን ጠላት እራሳችኑ ነን በተሰቦቼ።........
  ብዙ ጠብቆ ብዙ ያጣ ሚያጣው የጠበቀውን ብቻ ሳይሆን ዕለቱንም ጭምር ነው።.....
    እንዴት እንዴት ሲል ቀኑን በመብከንከን ይፈጀዋል።.....

   ወዳጆቼ ከመጠበቅ በሽታ ካልተላቀቁ ትርፉ እየቆሰሉ መኖር ነው።.....
   ማንም የማንንም ህይወት ላይኖር ከሰው ባንጠብቅ መልካም ነው።.....
ለእኛ ህይወት ባለዕዳዎቹ እኛው እራሳችን ነን።............


........የእናቴ ልጅ(Tame)💚💛❤
........... @Meklite21

👇👇Telegram channel 👇👇
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee


.......ያልተካደ ልብ ክህደትን እንዴት ሊያውቅ ይችላል????..
ያልተጠላስ ልብ ከማፍቀር ውጪ መጥላትን አንዴት ይማረዋል????....
..  ሁላችንም የተወጋንበትን ጦር ነው ሌላ ላይ የምንሰካው። በተመረዝንበት በኩል ነው የምንመርዘው።.......

ወደ ህይወትህ የሚመጡትን ሰዎች ወደ ተፈጥሮህ ይገቡ ዘንድ አትፍቀድላቸው።....
  አለበለዚያ ንፁህ ተፈጥሯዊ  ማንነትህን ይነጥቁሃል።
   ቅንነትህን ያሳጡሃል።......
    እነሱን እየከሰስክ ሳታውቀው ከእነሱም በላይ ከፍተሃል።........


.............👇👇👇...........
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee


እነዛ የደስታ ግዜያት በፍጥነት አልቀው ተመሳሳይ አሰልቺ ቀኖችን እንደጋግማለን። እነዛ የዝናብ ላይ ሩጫዎች፣ የባህል ዋዜማ ጉጉቶች፣ የንጹህ ፈገግታ ድምሮች፣ እውነተኛ ወዳጅነት፣ ልብስ የሌለበት ልባዊ ፍቅር በጠቅላላ በመዳፍ ላይ እንዳለች እፍኝ ተበትኖ ተሰውሯል። እንደ እፉዬ ገላ በገዛ እድሜያችን ስሌት እፍ እፍ ተብለን ከልጅነታችን ጠፍተናል።

የድሮው ከረሜላ እንዳለ ነው፤ ነገር ግን ምላሳችን ስር ያለው የከረሜላን ጥፍጥና ዛሬ ላይ የለም። በቀላሉ አንደሰትም በከባዱም ደስታ ጠፍቷል። በትልቁም በትንሹም እርካታ የለሽ ደባሪ ሰው ሆነናል። አምነን የማንቀበለው እንዲህ ያለው እውነት ያማል!።



ቴሌግራም...
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee


"ጥላቻ ህይወትን ሽባ ያደርጋል፤"ፍቅር ግን ይፈውሳል።

ጥላቻ ህይወትን ግራ ያጋባል፤ ፍቅር ደግሞ አንድነትን ይፈጥራል።ጥላቻ ህይወትን ያጨልማል፤ፍቅር ደግሞ በብርሀኑ ጨለማን ይገፋል!

ወንድሜ ሆይ!! በህይወት ዘመንህ ደስተኛና ተወዳጅ ለመሆን ከፈለክ ማንንም አትጥላ"!!


ቴሌግራም...
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee


●† ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለፋሲካ በዓል በሰላም በጤና አደረሳችሁ አደረሰን እንላለን !

......ከመሸም ቢሆን......

     መልካም የትንሳኤ በዓል
!!


"ለግዜር የተፃፈ ደብዳቤ" የሚል ግጥም ከዓመታት በፊት ፅፌ ነበር። ሐሳቡ ለመጀመሪያ ጊዜ ውል ያለብኝ የምኖርበት ሰፈር የመድሃኒያለም ደብር አለ። ወደደብሩ መሄጃ መንገድ ላይ አንድ የአእምሮ ህመምተኛ  ሁልጊዜ ይቆምና ሊሳለም የሚሄደውን ሰው ሁሉ "እግዚአብሔርን ሰላም በሉልኝ፣ እኔ ጋር ተጣልተናል፣ እዚች ግድም እንዳትመጣ ብሎኛል" እያለ ይጮሃል። ለረዢም ጊዜ እንደዛ ይል ነበር። ከመደጋገሙ የተነሳ ፀቡ መታወቂያው ሆነ። አንዳንዶች "እውነትም ቢጣላው ነው ያበደው" ይሉ ነበር። አንድ ቀን የሰፈር ልጆች ሊሳለሙ ሲሄዱ  "እግዚያብሔር ጥሩት እታረቀዋለሁ ብሏል እንሂድ" ይሉታል። እነሱ እንዲሁ ለቀልድ ያህል ነው። ሰውየው ግን በደስታ ድሪቶውን ሰብስቦ ተከተላቸው።  ቤተክርስቲያኑ በር ላይ ሲደርሱ "ያውና እግዚያብሔር ያው ..." እያለ በፍርሃት ከልጆቹ ኋላ ተደበቀ። በሩ አካባቢ የማይጠፋ የብረት ዱላ በእጁ የሚይዝ ክፉ ሰካራም የኔ ቢጤ አለ። ሰው ጋር ሁሉ የሚጣላ ጉልቤ ነገር ነው። ያንን ምስኪን ከቤተክርስቲያ የሆነ ቀን ያባረረው እንግዲህ ይሄው አመለ ቢስ የኔ ቢጤ ነው። ለዛ ሚስኪን ግን ይሄ ለራሱም ደብሩን ተጠግቶ የዕለት ጉርሱን የሚለምን ጉልቤ እግዚያብሔር ሁኖበት ነበር።

* ማነው  ምንድነው እግዚአብሔርን ተመስሎ ከምህረቱ፣ ከፍቅሩ ከማዳኑ ፣ ከሰላሙ የለያችሁ? ኑሮ? ክፉ ሰወች? የደረሰባችሁ ውጣ ውረድ? ሰይጣን የሞላባችሁ ፍርሃት?  በምንም ሁኔታ ውስጥ ሁኑ ማንም ምንም ይበላችሁ፤  ኢየሱስ "መስቀሉ ላይ በከፈልኩላችሁ  ዋጋ ኑ  እንታረቅ  ብሏችኋል!! በምንም ሁኔታ ውስጥ ሁኑ ይወዳችኋል፤ እርሱ በወደዳችሁ ልክ ራሳችሁን እንኳን መውደድ አትችሉም!!

..✍ Alex Abraham

ቴሌግራም...
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
🎞 The Jesus Film 1979 | የኢየሱስ ፊልም
↪️ በአማርኛ
​​​​​​​​​​​ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉት👇👇👇
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee


የኢየሱስ ፊልም
↪️ በአማርኛ
​​​​​​​​​ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉት👇👇👇
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee


ተዓምር አይደለም?
~    ~     ~      ~      ~

ሲሸቀጥ ሲነገድ ፍቅር ጉልት ዋለ
በራሱ ቀይ ደም እንጨት ላይ ተሳለ፡፡

ተዘባበቱበት፡፡

ያን ሁሉ ዓለንጋ መቻሉን ረሱ
"እስቲ ይውረድ" አሉ ከመስቀል በራሱ::
እስቲ ተዓምር አድርግ ይሉታል በዓለም
በታናሽ መገረፍ ተዓምር አይደለም?

"እስቲ ድንቅን አድርግ" ይላሉ -
..... አይፈሩምና ጡር
ተዓምር አይደለም?....
......መቸንከር በፍጡር?

ልፍስፍስ ነው አሉት
ደካማ ነው አሉት
ወከባ ነው አሉት...
.... አይችልም ማስገረም
እናትን እያዩ መመታት....
......በራሱ ተዓምር አይደለም?

ተዘባበቱበት::...........
እንደራቆተ ዋለ ባደባባይ
ምድርን ያለበሰ በደመና ሰማይ፡፡
ከንፈር ስንት ገባ? ተጠምቶ አደረ
ውኃ ለሁለት ከፍሎ እንዳላሻገረ፡፡

ማቀፍ ስንት ገባ?
መሳም ስንት ገባ? 
ዋጋው ተወደደ ወይስ ቀዘቀዘ
ዓለምን የያዘ
     በዓለም ተያዘ፡፡

ተዓምር አይደለም?



ኤልያስ ሽታኹን
.......... @Meklite21 💚💛❤
ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉት👇👇👇
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee


“ቀድመውኝ አይደለም፤ ዘግይቼም አይደለም። ቀድሜያቸውም አይደለም፤ ወይም እነሱ
ዘግይተው።
… ትክክለኛው ሰዐት ላይ ነኝ።” በል!
:
ምናልባት አንዱ በ20 ዓመቱ ያገባ ይሆናል፤ ለመውለድ አስር አመታትን ይወስዳል።
አንዱ በ30 ዓመቱ ያገባል፤ በዓመቱ ይወልዳል።
አንዷ በ22 ዓመቷ ታገባለች፤ ጥሩ ባል አይደለም።
ሌላኛዋ በ34 ዓመቷ ታገባለች፤ ደስተኛ ትዳርንም ትመራለች።
ከፊሉ በ22 ዓመቱ ይመረቃል፤ ስራ ለማግኘት 5 ዓመታት ይፈጅበታል። ከፊሉ በ27 ዓመቱ
ይመረቃል፤ ከመውጣቱ ስራን ያገኛል።
ሌላው በ25 ዓመቱ የድርጅት ስራ አስኪያጅ ይሆናል፤ በ40 ዓመቱ ይሞታል።
ሌላኛው በ50 ዓመቱ የድርጅት አስኪያጅ ይሆናል፤ በ90 ዓመቱ ይሞታል።
:

ጊዜህን ብቻ ተከተል።
የቀደሙህ ወይም የዘገየህ አድርገው ይስሉሀል።
አንተ ከማንም አልተቀደምክም፤ ከማንም አልዘገየህም። ፈጣሪ በፈቀደልህ  ጊዜ ብቻ
እየሄድክ ነው። ይህንን እወቅ።
የአዕምሮ ረፍትና እርጋታህን ይዘህ ኑር።
:
ጊዜ በፈጣሪ እጅ ያለ መንገድ ነው። እንደፈለገ ያስኬደዋል። የፈለገውን ላንተ በፈለገልህ
ሰዓት ያደርግልሀል።
«ነገሩም ሁሉ በእርሱ ዘንድ በልክ የተወሰነ ነው።»

.....ተመስገን🙏🙏🙏


.......... @Meklite21 💚💛❤
ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉት👇👇👇
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee
https://t.me/Asresee


እናመስግን !

እኛ ከምናስበው የቀደመ ከእኛ በላይ ለአኛ ያለን ደግነቱ ከአእምሮም በላይ የሆነ ጭንቀታችንን የሚያቀልልን ከገባንበት ችግር ነቅሎ የሚያወጣን እንዳንወድቅ የሚደግፈን እንዳንሸነፍ የሚያበረታን ፈጣሪ አለን ታድያ እሱን ለማመስገን ምን እንጠብቃለን !
     🪄  ስላለኸን ተመስገን 🙏
     🪄 ልጆችህ ስላደረግኸን ተመስገን  🙏
     🪄  የእኛ ስለሆንክ እና ሁሉን ነገራችንን    ሽፍን አድርገህ ስለያዝከን ተመስገን እንበለው 🙏


........ተመስገን🙏🙏🙏


.......... @Meklite21 💚💛❤
ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉት👇👇👇
➱💚
https://t.me/Asresee
➱💛
https://t.me/Asresee
➱❤
https://t.me/Asresee


ስለሁሉም አመስግኑ!

ስለሆነው ስለሚሆነው ስለማይሆነው፣ ስላጣናቸው ስላገኘናቸው ፈልገንም ስላላገኘናቸው ስለተሰጠን ስለሚሰጠን፣ ስለማይሰጠን፣ ስላልተሳካልን ስለተሳካልን፣ ስለከሰርነው ስላተረፍነው ነገር በሙሉ ፈጣሪ ይመስገን። ስለሔደው በማልቀስ፣ ስለሚመጣውም በመጨነቅ ጊዜ ማጥፋት አያስፈልግም። ሁሉ ለበጎ ሁሉ ለመልካም እንደሚደረግ ማመን ከሁሉ ነገር ነፃ ያወጣል። ስለእራሳችን በሚገባ የምናውቅ ሊመስለን ይችላል ለእኛ የሚበጀንን ግን ከእኛ በተሻለ እግዚአብሔር አምላካችን እንደሚያውቅ ማስታወስ ያስፈልጋል። በህይወታችን የሚከሰቱ እያንዳንዱ ነገሮች በምክንያት የሚፈጠሩ ናቸው። ወደዳችሁም ጠላችሁም ከትናንት ጥፋታችሁና ከዛሬ ተግባራችሁ ጀርባ በቂ ምክንያት ነበረ::

   ,,,,,,,,,ሁሌም ተመስገን በለው .....🙏🙏



.........Telegram Channel
👉
https://t.me/Asresee
👉
https://t.me/Asresee
👉
https://t.me/Asresee


ሰላም ለእናንተ ይሁን.........
  ...........
#እንዴት አደራችሁ...🙏🙏

........9ቁጥር 8 ቁጥርን በጥፊ መታው 8 ለምን ትመታኛለህ ብሎ ሲጠይቀው ከኔ በታች ሰለሆንክ ብሎት እርፍ!....ይሄን የሰማ 8 ቁጥር 7 ቁጥርን በጥፊ ይመተዋል ምን አደረኩኝ ቢለው ከኔ በታች ስለ ሆንክ ይለዋል። ሰባትም በተራው ስድስትን ስድስትንም አምስትን አምስት አራትን አራት ሶስትን ሶስት ሁለትን ሁለት አንድን የበታቼ ነህ እያሉ ይመቱ ጀመር።

ከሁለት ቁጥር የመመታት አደጋ የደረሰበት አንድ ቁጥር 0 ሊመታ አሰበና ለምን በፍቅር አላሸንፈውም ብሎ ና ከጎኔ ቁም ቢለው 10 ሆኑና ልቀው ታዩ።....

ከፍቅር የማይገኝ ትርፍ የለም...ፍቅር ያሸንፋል❤

#በፍቅር_ዋሉልኝ


👇👇Telegram channel 👇👇
✍️
https://t.me/Asresee ✍️
✍️
https://t.me/Asresee ✍️
✍️
https://t.me/Asresee ✍️


ንጹሕ ሆነን የረከሰ ምራቅን አለመጠየፍ እንዴት ይቻለናል? ያለ በደል የሚደረግ ውንጀላ እና ግፍንስ "በቃ" አለማለት እንዴት ይሆናልናል?

ያለ ጥፋት የሚመጣብንን ምን ያህል ጥፊዎች እንታገሳለን? ስንት ጅራፎችንስ እንቀበላለን? ስንት ውርደቶችንስ እንሸከማለን? መድኃኔዓለም ይህን ሁሉ ነገር የተቀበለው ስለ እኛ መዳን ነው።

እኔ ግን ስለ ራሴ መዳን በጀርባህ ላይ ካረፉት ጅራፎች የአንዲቱን ሰንበር ያህል እንኳን መከራ ለመቀበል ትዕግስቱ የለኝም።

"ተሰሃለኒ እግዚኦ በከመ ዕበየ ሳህልከ" - "አቤቱ እንደ ቸርነትህ መጠን ማረኝ"  መዝ 50፥1

..........ዲያቆን አቤል ካሳሁን



👇👇Telegram channel 👇👇
✍️ https://t.me/Asresee ✍️
✍️
https://t.me/Asresee ✍️

Показано 20 последних публикаций.