Фильтр публикаций


የምዕራብ ጎንደር ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ በዞኑ አጠቃላይ የ2017 የሰላምና ፀጥታ ስራዎች ዙሪያ የስድስት ወራት የተግባራት አፈፃፀም ግምገማ ማካሄደ ጀመረ

አማራ ፖሊስ፦ጥር 28/2017 ዓ.ም

የምዕራብ ጎንደር ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ በዞኑ አጠቃላይ የ2017 የሰላምና ፀጥታ ስራዎች ዙሪያ የ6 ወራት የተግባራት አፈፃፀም ግምገማ በገንዳ ውሃ በዛሬው ዕለት ማካሄደ ጀመሯል።

ሰላምና ፀጥታ መምሪያው በዞኑ የሰላምና ፀጥታ ግምገማ መክፈቻው ላይ የምዕራብ ጎንደር ዞን ተወካይ አስተዳዳሪና የዞኑ ትራንስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉአለም ታደሰ፣የምዕራብ ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ምክትል ኮማንደር ምስጋናው ካሴን ጨምሮ ሌሎች የዞን፣የወረዳና ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች እዲኹም የሰላምና ፀጥታ አጋር አካላት ተገኝተዋል።

በመርሃ ግብሩ አጠቃላይ የዞኑን ሰላም በዘላቂነት ለማጽናት የሰላም ማስከበር ተግባራትን ለማጠናር የሚስችሉ ተግባርና ስራዎች በዞኑ ምኒሻ መምሪያ ተወካይ ኃላፊ በአቶ ባይመሽ ሰንደቄ ሪፖርቱ እየቀረበ ይገኛል።

በግምገማው በዞኑ የ2017 የሰላምና የፀጥታ ተግባር ዕቅድ ላይ በመወያየት ማጽደቅና ቀጣይ አቅጣጫ እንደሚቀመጥም ተመልክቷል።

📷 West Gondar zone Communication


የክልሉን ሰላም በዘላቂነት ለመፍታት በቁርጠኝነት መሥራት እንደሚገባ የቋሚ ኮሚቴ አባላት አሳሰቡ።

አማራ ፖሊስ: ጥር 27/2017 ዓ.ም

የአማራ ክልል ምክር ቤት የሕግ፣ ፍትሕ እና አሥተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚከታተላቸውን ተቋማት የሥራ አፈጻጸም እየገመገመ ነው።

ቋሚ ኮሚቴው የአማራ ክልል ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ እና የተጠሪ ተቋማቱን የሥራ አፈጻጸም ገምግሟል።

የቋሚ ኮሚቴ አባላትም የጸጥታ ተቋሙ የክልሉን ሰላም ለማረጋገጥ እየከፈለው ያለው መስዋዕትነት ክብር የሚያሰጠው መኾኑን ገልጸዋል። በራስ አቅም የአካባቢን ሰላም ለማረጋገጥ እየተሠራ ያለው ሥራም የሚበረታታ ነው ብለዋል።

መስዋዕትነት እየከፈለ በሠራው ሥራ በክልሉ አንጻራዊ ሰላም እንዲመጣ አድርጓል ነው ያሉት። የጸጥታ ኀይሉ ለሕዝብ ሰላም እና ደኅንነት በጀግንነት እየታገለ ነው፣ ለዚህ ክብር ልንሰጠው ይገባል ብለዋል።

የጸጥታ ችግሩን ሕግ በማስከበር ብቻ ሳይኾን በእርቅ እና በይቅርታ ለመፍታት እየተሄደ ያለው ርቀትም የሚበረታታ ነው ብለዋል።

የጸጥታ ተቋሙ የክልሉን የጸጥታ ችግር በዘላቂነት ለመመለስ መስዋዕትነት ከመክፈል ባሻገር ውይይትን እንደ አማራጭ መጠቀም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ነው ያሉት።

ከሕዝብ ጋር ጥብቅ ቁርኝት መፍጠር እንደሚጠበቅበትም አንስተዋል። የክልሉን ግጭት በውይይት እና በሰላማዊ መንገድ በመቋጨት ሕዝቡን ከተራዘመ ጦርነት መውጣት ይጠበቃል ነው ያሉት።

የሰላም እና የጸጥታ ተቋማት የሕዝብን መታገት፣ መገደል እና መጎዳት ማስተካከል እንደሚገባቸውም ገልጸዋል። የጸጥታ ኀይሉን መፈተሽ እና ታማኝነቱን ማረጋገጥ እንደሚገባ ነው የተናገሩት።

ለሕዝብ የሚሠሩ እንዳሉ ሁሉ መረጃ የሚያወጡ ከመንግሥት በተቃራኒ የሚሠሩ የጸጥታ ኀይሎች አሉ ነው ያሉት።

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.facebook.com/share/p/19qZHk8Zts/


በወረታ ከተማ በተደረገ ኦፕሬሽን ውጤታማ ተግባር መከናወኑን የወረታ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት አስታወቀ።

በወረታ ከተማ አስተዳደር ስር በሚገኘው ቋሃር ሚካኤል በተባለ የገጠር ቀበሌ ውስጥ በዛሬው ዕለት ማለትም ጥር 27/2017 ዓ.ም እረፋድ ላይ በነበረው የሰላም ማስከበር ኦኘሬሽን በፅንፈኛው ላይ የተሳካ ኦፕሬሽን መደረጉን የወረታ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት አስታውቋል።

የመንግስት ታጣቂ ኃይሎች በወሰዱት የጸጥታ ማስከበር ኦኘሬሽን እርምጃ ላይ 5 የፅንፈኛ ቡድን መደምሰሱንና 8 የጠላት ቡድን ደግሞ መቁሰሉን እንዲሁም 1 ብሬንና 4 ክላሽ የጦር መሣሪያዎች መማረካቸውን ጽ/ቤቱ ገልጿል።

በተደረገው ኦኘሬሽን ላይ ከመንግስት ጸጥታ አስከባሪና ታጣቂ ኃይሎች ላይ ምንም አይነት ጉዳት አለመድረሱንና ይህም ድል የተገኘው በተደራጀና በተቀናጀ የመረጃ መዋቅር ፣በወረታ ከተማ አስተዳደር ጸጥታ አስከባሪ ኃይሎችና አድማ ብተና እንዲሁም በፎገራ ወረዳ አጋዥ አድማ ብተናና የጸጥታ ኃይሎች አማካኝነት መሆኑን በጽ/ቤቱ ጨምሮ ገልጿል።

መረጃው፦የወረታ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬን ነው።


"ለፍትህ ስርዓቱ ውጤታማነት በትብብር መስራት ይገባል"
ምክትል ኮሚሽነርና የወንጀል ምርመራ ዘርፍ ኀላፊ ረ/ኮሚሽነር ውበቱ አለ
አማራ ፖሊስ፡ጥር/2017 ዓ.ም

የአማራ ክልል ወንጀል ምርመራ ዘርፍ የሰድስት ወራት አፈፃፀምን በገመገመበት ወቅት ንግግር ያደረጉት የኮሚሽኑ ወንጀል ምርመራ ዘርፍ ኀላፊ ረዳት ኮሚሽነር ውበቱ አለ በዘንድሮው ግማሽ ዓመት በተፈለገው አግባብ ተንቀሳቅሶ ለመስራት እንቅፋቶች ቢኖሩም በብዙ ችግሮች ውስጥ ሆኖ በግማሽ ዓመቱ ከቀረቡ 5453 መዝገቦች 4725ቱ ተጣርተው ለዐቃቤ ህግ ተልከዋል። ይህም የምርመራ የማጣራት ዐቅምን 86.9 በመቶ ያደርሰዋል ብለዋል።
ምንም እንኳን ወቅቱ ፈታኝ ቢሆንም በተፋጠነ የፍትህ ስርዓት መታዬት ከነበረባቸው 1108 መዝገቦች 956ቱን በማቅረብ 86.4 በመቶ መፈፀምም ተችሏል።

በወንጀል ምርመራ ዘርፍ የታክቲክ ወንጀል ምርመራ ም/ዘርፍ ኀላፊ ረዳት ኮሚሽነር ክንዱ ወንዴ በበኩላቸው የነበሩንን ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመለዬት ድክመቶቻችንን አርመን የቀጣይ አቅጣጫ ማስቀመጥ ይኖርብናል ብለዋል።


የሕዝብን ሰላም እና ደህንነት ለማስጠበቅ የሚያስችል ወታደራዊ ሥልጠናዎችን መውሰዳቸውን የፍኖተ ሰላም ተመራቂ ሚሊሻዎች ተናገሩ።

አማራ ፖሊስ: ጥር 26/2017 ዓ.ም

በፍኖተ ሰላም ማዕከል ሥልጠናቸውን ሲከታተሉ የቆዩ የፍኖተ ሰላም ቀጣና የ2ኛ ዙር የሰላም አስከባሪ እና የሚሊሻ አባላት የምረቃ ሥነ ሥርዓት ተካሂዷል።

ተመራቂዎቹ የአካባቢያቸውን ሰላም እና ደህንነት ለማስጠበቅ የሚያስችል አካላዊ እና ወታደራዊ ሥልጠናዎችን በሚገባ ስለመውሰዳቸው በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ተገልጿል።

በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የመከላከያ ሠራዊት የሰላም ማስከበር ማዕከል ኀላፊ ሜጀር ጀኔራል አዳምነህ መንግስቴን ጨምሮ የዞን እና የፍኖተ ሰላም ከተማ አሥተዳደር መሪዎች ተገኝተዋል።


‘’የጸጥታ መዋቅሩን እና የኅብረተሰቡን አቅም አቀናጅቶ በመጠቀም ዘላቂ ሰላም የማፅናት ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል’’ የአዊ ብሔረሰብ አሥተዳደር

አማራ ፖሊስ፦ ጥር 26/2017 ዓ/ም
የአዊ ብሔረሰብ አሥተዳደር ሰላም እና ጸጥታ መምሪያ የ2017 በጀት ዓመት ባለፉት ስድስት ወራት ሕግ የማስከበር ሥራ አፈፃፀም እና የቀጣይ አቅጣጫዎችን ገምግሟል። ከሁሉም ወረዳዎች እና ከተማ አሥተዳደሮች የተውጣጡ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ነው ግምገማው የተካሄደው።

በግምገማ መድረኩ የተገኙት የአዊ ብሔረሰብ አሥተዳደር ምክትል አሥተዳዳሪ እና የከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ ኀላፊ አይተነው ታዴ እንደ ክልል የተፈጠረው የሰላም መደፍረስ በርካታ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ጉዳት ማስከተሉን ተናግረዋል።

የጸጥታ መዋቅሩ በጠንካራ ሕዝባዊ ድጋፍ ታጅቦ በከፈለው መስዋዕትነት የብሔረሰብ አሥተዳደሩ አብዛኛዎቹ አካባቢዎች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው መመለሳቸውንም ምክትል አሥተዳዳሪው ገልጸዋል።

የፀጥታ መዋቅሩን እና የኅብረተሰቡን አቅም አቀናጅቶ በመጠቀም የብሔረሰብ አሥተዳደሩን ዘላቂ ሰላም የማፅናት ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ምክትል አሥተዳዳሪው አንስተዋል።

የብሔረሰብ አሥተዳደሩ ሰላም እና ጸጥታ መምሪያ ኀላፊ ጌታቸው ቢሻው የሕይዎት እና የአካል መስዋዕትነት ተከፍሎበት የተገኘው ሰላም እንዳይቀለበስ ዘላቂ ሰላምን የማስፈን ሥራ ሕዝባዊ መሠረት እንዲኖረው እየተሠራ መኾኑን ተናግረዋል።

በብሔረሰብ አሥተዳዳሩ አሁን እየመጣ ላለው ሰላም የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና የኅብረተሰቡ ሚና የጎላ እንደኾነም ኀላፊው አንስተዋል።

የሃይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች ከጸጥታ መዋቅሩ ጋር በቅንጅት በሠሩት ሥራ በብሔረሰብ አሥተዳደሩ ከ240 በላይ የታጠቁ ኀይሎች የመንግሥት እና ሕዝብ የሰላም ጥሪን ተቀብለው ወደ ማኅበረሰቡ ተቀላቅለዋልም ነው ያሉት።

የብሔረሰብ አሥተዳደሩ ፖሊስ መምሪያ ኀላፊ ኮማንደር እሱባለው መኮንን በበኩላቸው ለሕገ መንግሥቱ እና ለሕዝብ ዘብ የቆመ የጸጥታ መዋቅር በመገንባት ሕግ የማስከበር ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።


በፀጥታው ችግር ምክንያት ለጥቃት ተጋላጭ የሆኑ የሴቶችን የመደገፍ ስራ እየተሰራ መሆኑን የምዕራብ ጎጃም ዞን ሴቶች ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ገለፀ።

የምዕራብ ጎጃም ሴቶች ፣ ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ የሴቶች የተደራጀ እና ሁለንተናዊ ተሳትፎ ለዘላቂ ሰላም እና ልማት ግንባታ በሚል መሪ ቃል ከሴት የመንግስት ሰራተኞች ጋር የውይይት መድረክ በፍኖተ ሰላም ከተማ አካሂዷል።

መድረኩ ላይ የተገኙ በምዕራብ ጎጃም ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፓለቲካ ዘርፍ ኀላፊ አቶ ሙላት ጌታቸው በክልሉ የገጠመውን የሰላም እጦት በኢኮኖሚ ፣ በፓለቲካ እና ማህበራዊ ዘርፎች በርካታ ቀውሶች እያደረሰ መኾኑን ተናግረዋል።

ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት የመጀመሪያ ተጠቂዎች ሴቶች መኾናቸውን ገልፀው ለሰላም ግንባታ የሴቶች ሚና የጎላ በመኾኑ የበኩላቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።

ሴቶች በማህበራዊ ፣ በፓለቲካዊ እና ኢኮኖሚ ውስጥ ያላቸው ተሳትፎ ወሳኝ በመሆኑ ሰላምን ለመጠበቅ እና ለማሳደግ አይነተኛ አበርክቶ አለው ።

በፀጥታው ችግር ምክንያት ለጥቃት ተጋላጭ የሆኑ የሴቶች ማህበራትን በማስተባበር የመደገፍ ስራ እየተሰራ መኾኑን የምዕራብ ጎጃም ዞን ሴቶች ፣ ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኀላፊ ስለእናት ዘሪሁን ተናግረዋል ።

በተለይም የሴት አደረጃጀቶችን በማጠናከር ሴቶች ለሰላም ግንባታ የበኩላቸውን እንዲወጡ እየተደረገ መሆኑን ገልፀው ፤ ታጥቀው ወደ ጫካ የገቡ ኃይሎችም ፊታቸውን ወደ ሰላም እንዲያዞሩ ነው ወ/ሮ ስለእናት የጠየቁት።

ሴቶች በማህበራዊ ፣ ፓለቲካ እና ኢኮኖሚ ዘርፎች ላይ ጉልህ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክቱ ሁሉ አደረጃጀቶችን በመጠቀም የሰላም ግንባታ ሂደት ላይ ተሳትፏቸውን የማጠናከር ስራ እየተከናወነ መኾኑን የምዕራብ ጎጃም ዞን ሴቶች ሊግ ኀላፊ ወ/ሮ አክሊለ ዞማነህ ገልፀዋል።

በውይይት መድረኩ ላይ የተሳተፉ ሴት የመንግስት ሰራተኞችም የፀጥታ ችግሩ እያደረሰ ያለውን ጉዳት ቅድሚያ በመስጠት እና ከዚህ የከፋ ችግር ሳይከሰት ሁሉም አካላት ለውይይት እና ለድርድር ዝግጁ መሆን አለባቸው ለዚህ ደግሞ ሁሉም ማህበረሰብ ሊረባረብ ይገባል ነው ያሉት።


13 ታጋቾች እንዲለቀቁ ተደረገ።

13 ታጋቾችን ከእገታ ማስለቀቁን የጭልጋ ወረዳ ሰላም እና ደህንነት ጽሐፈት ቤት አስታውቋል።

መነሻውን አዘዞ አድርጎ ወደ መተማ እየሄደ ባለ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ተሳፍረው ከነበሩት ተሳፋሪዎች 13ቱ ታግተው እንደነበር ተገልጿል።

የጭልጋ ወረዳ ሰላም እና ጸጥታ ጽሕፈት ቤት ምክትል ኀላፊ መላኩ አብዬ የጭልጋ ወረዳ የጸጥታ ኃይል በደረሰው መረጃ ወደ ቦታው በመግባት ባደረገው የተኩስ ልውውጥ 13ቱን ታጋቾች ማስለቀቁን ተናግረዋል።

መንገድ ላይ እየተደረገ ያለው እገታ ማኅበረሰባችን ጉዳት ላይ የሚጥል ነው ያሉት ምክትል ኀላፊው ማኅበረሰቡ መረጃ በመስጠት ከጸጥታ ኀይሉ ጋር እንዲሠራ አሳስበዋል።

የጭልጋ ወረዳ ሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ጋሻው ብርሀኔ እገታ የማኅበረሰቡን ኢኮኖሚ ከመጉዳት ባሻገር በሥነ ልቡና ላይም ትልቅ ተፅእኖ እንደሚያሳድር ተናግረዋል።

ሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል የእገታ ተግባርን በማውገዝ እና መረጃ በመስጠት ከጸጥታ መዋቅሩ ጎን እንዲሰለፍ ጠይቀዋል።

ከማዕከላዊ ጎንደር ዞን ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ የተገኘው መረጃ እንደሚያመላክተው ከእገታ የተለቀቁ ወገኖች በሕይወታቸው ለደረሰላቸው የወረዳው የጸጥታ ኀይል ምስጋና አቅርበዋል።

እገታን ሁሉም ማኅበረሰብ ሊያወግዘው እና ሊከላከለው የሚገባ ተግባር መኾኑንም ተናግረዋል።


❝የሰላም ሂደቱን አጠናክሮ በመቀጠል የማህበረሰባችንን ችግር መፍታት የሁላችንም ድርሻ ነው።❞የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ፖሊስ መምሪያ ኀላፊ ኮማንደር እሱባለው መኮንን

የብሄረሰብ አስተዳደሩ ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር እሱባለው መኮንን እንደገለፁት በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎች ከ162 በላይ በተሳሳተ መንገድ ወደጫካ የገቡ ታጣቂዎች እጂ የሰጡ ሲሆን ይህንንም ፈር ቀዳጅ ተግባር እንደ ተሞክሮ በመውሰድ አሁንም በጫካ ያሉ ታጣቂዎች በሰላማዊ መንገድ ወደ ማህበረሰቡ ሊቀላቀሉ ይገባል ብለዋል።

እነዚህ ታጣቂዎች ወደ ማህበረሰቡ ሲቀላቀሉ መንግስት እና ማህበረሰቡ በደመቀ ሁኔታ የተቀበላቸው ሲሆን ይህንንም ኹነት በመረዳት ቀሪዎቹም ከመጠራጠርና ከመፈራራት በመላቀቅ ወደማህበረሰቡ በሰላም መምጣት ይኖርበታል ነው ያሉት ኃላፊው።

የዞኑ ብሎም የክልሉ ሰላም ይመለስ ዘንድ ከነፍጥና ሸፍጥ ባሻገር ጊዜ መጣኝ ተግባሩ ሰላምን አማራጭ ሳይሆን ምርጫ ማድረግ ግደታችንና ብቸኛው መፍትሄ መሆኑንም አክለው ገልፀዋል።

እንደ ኮማንደር እሱባለው ገለፃ አሁናዊ የዞኑ የፀጥታ ሁኔታ አንፃራዊ ሰላም የሚስተዋልበት ሲሆን ይህም በፀጥታ ኀይሉ እና በማህበረሰቡ ልዩ ትጋትና ቅንጂት የተገኘ አንፀባራቂ ድል ነው ብለዋል።


የ6 ዓመት ህፃን ያገተ ግለሰብ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሏል።

ህፃን ኢብራሂም ጀማል የሱፍ ዕድሜው 6 ዓመት ሲሆን በደ/ወሎ ዞን ወራኢሉ ወረዳ ቀበሌ 01 ጥር 23 /2017 ዓ/ም ከቀኑ 5:00 ሰዓት ገደማ የጠፋ መሆኑን ወላጅ አባቱ አቶ ጀማል የሡፍ ገልፀዋል።

የህፃኑ አባት ልጁ መጥፋቱን እንዳረጋገጡ በጠፋ ከ5 ሰዓታት በኋላ ማለትም ጥር 23/2017 ዓ/ም ከቀኑ 10 ሰዓት ገደማ በኮምቦልቻ ከተማ ለአቢሻገር ክ/ከተማ ፖሊስ እንዳሳወቁ ተመላክቷል።

በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርናቸው የአቢሻገር ክ/ከተማ ፖሊስ አዛዥ የሆኑት ም/ኢ/ር ሁሴን መብራቱ እንዳሉት የእግታ ወንጀሉ መረጃ እንደደረሰ ፖሊስ በኬላና በሁሉም አጠራጣሪ ቦታዎች ጥብቅ ክትትል ሲያደረግ እንደነበር ገልፀዋል።

ሀላፊውም እንዳሉት ከተጠናከረ ክትትልና ፍተሻ በኋላ በ2ኛው ቀን ጥር 24/2017 ዓ/ም ከጧቱ 2 ሰዓት በኬላ ፍተኛ ህፃኑን ከአጋች ሰይድ ኡመር ጣሂር ጋር በቁጥጥር ስር እንዳዋሉ እና ህፃኑን ከነ ሙሉ ጤንነቱ ለወላጅ አባቱ ያስረከቡ መሆኑን አስረድተዋል።

እንደ ኢንስፔክተሩ ገለፃ በአጋቹ ላይ ምርመራ እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።

ያነጋገርናቸው የታጋች ህፃን አባት አቶ ጀማል የሱፍ ልጃቸውን በማግኘታቸው ደስታቸው እጥፍ መሆኑን ገልፀው ልጃቸውን የታደገላቸውን ፖሊስ ታላቅ የሆነ አክብሮትና ምስጋና ሰጥተዋል።

በመጨረሻም የአቢሻገር ክ/ከተማ ፖሊስ አዛዥ ም/ኢ/ር ሁሴን መብራቱ እንዳሉት ለፖሊስ ሀይሉ የሚሰወር የወንጀል ድርጊት አይኖርም ማህበረሰቡ በአካባቢያቸው ፀጉረ ልውጥ እና አጠራጣሪ ሰዎች ሲያጋጥም ለፖሊስ ጥቆማ መሥጠት፤ ራሥን፣ ቤተሰብን እና ንብረትን መጠበቅ እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል።

በጀግንነት መጠበቅ በሰባዊነት ማገልገል!!

#መረጃው በኮምቦልቻ ከተማ የአቢሻገር ክፍለ ከተማ ፖሊስ ነው።



Показано 11 последних публикаций.