ATC NEWS


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Образование


#ADDIS_ABABA : ETHIOPIA
ለመልዕክት 👇🏻
@mujaabot
For Advertisement👇🏿
@atcads

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Образование
Статистика
Фильтр публикаций


ባለፉት ሶስት ዓመታት የፈተና ስርቆትንና ኩረጃን ለመከላከል እንዲሁም ለረጅም ዓመታት ሲከሰት የነበረውን ፖለቲካዊና ማህበራዊ ቀውሶችን ለማስወገድ ጠንካራ ሥራ ተሠርቷል

ትምህርት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን በማረጋገጥ ረገጥ ዓይነተኛ ሚና አለው፡፡ በምክንያታዊነት የሚያምን እና ልዩነቶችን ማስተናገድ የሚችል አስተሳሰብ ያለውን ትውልድ በመቅረጽ የተረጋጋ ሰላም እንዲሰፍን በማድረግ ረገድም የማይተካ ሚና ይጫወታል፡፡ በአጠቃላይ ሳይንስና ስልጣኔ፣ ቴክኖሎጂና ፈጠራ፣ መማርና መመራመር ላይ ትምህርት ጉልህ ድርሻ አለው።

በመሆኑም ሀገራችን ኢትዮጵያ በትምህርት ልማት ላይ በተለይም የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ልዩ ትኩረት ሰጥታለች፡፡ በዚሁ መሠረት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ተማሪዎች በየደረጃው ባሉ ትምህርት ቤቶች ይገኛሉ፡፡ መንግስት ለትምህርት መሠረተ ልማት፣ ለትምህርት ቤት ምገባ እና ለሌሎች ጉዳዮች ከፍተኛ ወጪ ያወጣል፡፡ በትምህርት ሴክተሩም የትምህርት አዋጅን ጨምሮ የተለያዩ ህጎች የወጡና እየተተገበሩ ያሉ ሲሆን የስርዓተ ትምህርት እና ሌሎች ሪፎርሞችም በትምህርት ሚኒስቴር እና በክልል የትምህርት ቢሮዎችም እየተደረጉ እንዳሉ እንገነዘባለን፡፡ ይሁን እንጂ በትምህርት ቤት ያለው የነገው ሀገር ተረካቢ ትውልድ መማሩና አለመማሩ ሊረጋገጥ ይገባል፡፡ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ሚና በአግባቡ መታየት ያለበት እዚህ ጋር እንደሆነ ይታመናል፡፡

ባለፉት ሶስት ዓመታት የፈተና ስርቆትንና ኩረጃን ለመከላከል እንዲሁም በነዚህ ምክንያቶች ለረጅም ዓመታት ሲከሰት የነበረውን ፖለቲካዊና ማህበራዊ ቀውሶችን ለማስወገድ ጠንካራ ሥራ እንደተሰራ እንገነዘባለን፡፡ ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና 50% እና ከዚያ በላይ ውጤት ያስመዘገቡት ተፈታኞች በ2014 ዓ/ም 3.3%፣ በ2015 ዓ/ም 3.2% እና በ2016 ዓ/ም 5.4% ብቻ በመሆኑ ከ95% በላይ በሆኑ ተፈታኝ ተማሪዎቻችን ዝቅተኛ ውጤት በተደጋጋሚ ሲመዘገብ ሁላችንንም የሚቆጨን ጉዳይ ነው፡፡ በሪሜዲያል ፕሮግራም ለተጨማሪ ዝግጅት ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንዲገቡ የተደረጉ ተማሪዎችም እንደገና ተመዝነው የማያልፉት ቁጥራቸው ቀላል አይደለም፡፡ ስለሆነም ውድቀቱ የተማሪዎቹ ብቻ ሊሆን ፈጽሞ አይችልም፡፡ ተጠያቂነትና ኃላፊነትም በየደረጃው ሊሰፍን ይገባል፡፡
በመሆኑም 95% እና በላይ ተፈታኝ ተማሪ ዝቅተኛ ውጤት እያመጣ እስከመቼ ይቀጥላል የሚለው ጥያቄ የአብዛኛው ህዝባችን ጥያቄ በመሆኑ ምላሽ ይፈልጋል፡፡ በተጨማሪም አንድም ተፈታኝ ተማሪ 50% እና ከዚያ በላይ ውጤት ያላስመዘገበባቸው ትምህርት ቤቶች ቁጥር ቀላል ካለመሆኑ በተጨማሪ በየዓመቱ በሚፈለገው ደረጃ መሻሻል አለማሳየቱ ብቻ ሳይሆን ትምህርት ቤቶቹ በብዛት የሚገኙት በገጠር፣ በአርብቶ አደር እና መሠረተ ልማት ባልተዳረሰባቸው የሀገራችን አካባቢዎች መሆናቸው የትምህርት ፍትኃዊነት ላይ ጥያቄ ያስነሳሉ፡፡ ይህም ጥራት ያለው ትምህርት ፍትኃዊ ተደራሽነት ላይ በበቂ ጥናትና ምርምር ታግዞ አፋጣኝ የተግባር እርምጃ የሚፈልግ ጉዳይ ነው፡፡

ስለሆነም የትምህርት ልማት ሥራችን ዝቅተኛ ውጤት ያስመዘገበበትን በየደረጃው ያለው አመራርና ባለሙያው በአግባቡ በመፈተሽ ተጠያቂነትና ኃላፊነት የሰፈነበትን ሥርዓት ማረጋገጥ ይገባል፡፡ በተያያዘም የፈተናውን አወጣጥና አስተዳደርንም በሚመለከት ዘላቂ፣ አስተማማኝ፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና በተሟላ ሁኔታ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የትምህርት ምዘናና ፈተና ስርዓት እና ተቋም ከመገንባት አንጻርም ቀጣይነት ባለው መልኩ በአግባቡ እየፈተሹ ጉድለቶቹንም እያረሙ ያልተበጣጠሰ፣ የተደራጀና ጠንካራ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ስርዓት መገንባት ያስፈልጋል፡፡

በሌላው በኩል እአአ 2023 ላይ በተጠናው ሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘና ጥናት (Early Grade Reading Assessment (EGRA)) ሪፖርት መሠረት ሁለተኛ ክፍል ተማሪዎች 63% ሶስተኛ ክፍል 49% ተማሪዎች አንድም ቃል ማንበብ አልቻሉም፡፡ ይህም ቁጥራቸው ከፍተኛ የሆኑ ተማሪዎች መሠረታዊ የንባብ ክህሎት እንደሌላቸው ያሳያል፡፡ በመሆኑም ሳያነቡ መማርና መመራመር ከባድ በመሆኑ በቅድመ አንደኛና በታችኞቹ የክፍል ደረጃዎች ጀምሮ አሁንም ልዩ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ያስፈልጋል፡፡

በሌላው በኩል እአአ ከ2000 እስከ 2023 በተጠናው ሀገር አቀፍ የትምርት ምዘና (National Learning Assessment (NLA)) መሠረት በ4ኛ ክፍል (በእንግሊዘኛ፣ በአፍ መፍቻ፣ በሒሳብ እና አካባቢ ሳይንስ የትምህርት ዓይነቶች) እና በ8ኛ ክፍል (በእንግሊዘኛ፣ በሒሳብ፣ በፊዝክስ፣ በኬሚስትሪ፣ እና በባዮሎጂ የትምህርት ዓይነቶች) ተማሪዎች ያስመዘገቡት ሀገራዊ አማካይ ውጤታቸው ሲታይ 50% በታች ነው፡፡

እንደዚሁም የ2016 ትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተናዎች ውጤት ሪፖርቶ ሲታዩ አጠቃላይ ሀገራዊ አማካዩ 50% ነው፡፡ በተያያዘም የዩኒቨርሲቲ መውጫ እና የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተናዎችም ላይ የማለፊያ ውጤት የማያስመዘግቡ ተፈታኞች ቁጥር ቀላል አይደለም፡፡

በመሆኑም በተለያዩ ጊዜያት የሚመጡ ሪፖርቶች እንደሚያሳዩት በየደረጃው ያለው የትምህርት ምዘናም ይሁን የፈተናዎች ውጤት በዝቅተኛነት መመዝገብ ወይም የውጤት ማሽቆልቆል መሠረታዊ ተግዳሮቶቹ ብቁና በቂ መምህራን እጥረት፣ በቂ የተማሪዎች መማሪያ መጽሀፍት አለመኖር፣ በአንድ ክፍል ብዙ ተማሪዎች መኖር፣ ምቹና ሳቢ የመማር ማስተማር አከባቢ አለመኖር፣ በቂ የሆነ የተማሪ ቤተሰብ ድጋፍ አለመኖር፣ የቅድመ አንደኛ ትምህርት ተደራሽነት ጉድለት፣ የተጠያቂነትና ኃላፊነት ስርዓት በአግባቡ አለመስፈን ወዘተ ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡

ስለሆነም የትምህርት ስርዓቱ ስብራት ባለቤቱም መፍትሔ አመንጪውም በትምህርት ስርዓቱ ውስጥ በየደረጃው ያለ አመራርና የትምህርት ማህበረሰብ ነው፡፡ ተማሪውና የተማሪ ወላጅ በትምህርት ጥራት መረጋገጥ ላይ ከፍተኛ ሚና ያላቸው ቢሆንም ብቻቸውን ወሳኝ ግን አይደሉም። በመሆኑም የችግሩ ብቸኛ ገፈት ቀማሽ የማይሆኑበትን አሠራር መፍጠር ይገባል፡፡ መምህራን በትምህርት ስርዓት ውስጥ ቁልፍ ሚና አላቸው፡፡ በመሆኑም በመምህራን ልማት፣ በመምህራን ትምህርትና ስልጠና ላይ እንዲሁም የመምህራኑን ኑሮ ማሻሻል እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎቻቸውን በጋራ ሆኖ መፍታት ላይ ልዩ ርብርብ የሚጠይቅና ትኩረትም የሚሻ እንደሆነ እንገነዘባለን፡፡ በሀገራችን ያሉ ትምህርት ቤቶች አብዛኞቹ ከደረጃ በታች በመሆናቸው የተጀመረውን ትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ አጠናክሮ መቀጠልና የትምህርት ቤቶች አካባቢም ለተማሪዎች ምቹ ለማድረግ በቅንጅት መስራት የሚጠይቅ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡

በመጨረሻም በየዓመቱ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች እየተዘጋጀ ያለው እንደዚህ ዓይነት ሁሉንም ባላድርሻ አካላትን የመሰባስብና በጋራ ጉዳዮች ላይ በጋራ እንዲመክሩና ለችገሮቹም በጥናትና ምርምር ላይ መሠረት ያደረጉ ተግባራዊ የሚደረጉ የጋራ መፍትሔ በማስቀመጥ የሚደረጉ ጉባኤዎች ከፍተኛ ሀገራዊ ፋይዳ ያለቸው በመሆኑ ተጠናከረው ሊቀጥሉ ይገባል፡፡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ የሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴም ቁጥጥር፣ ክትትልና ድጋፍ ከሚያደርጋቸው ተግባራት መካከል አንዱ በመሆኑ አስፈላጊውን እገዛ የሚያደርግ መሆኑን በቋሚ ኮሚቴውና በራሴ ስም መግለጽ እወዳለሁ፡፡

# EAES
ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


በሶስቱም ቅርንጫፎቻችን ( መገናኛ፣ ሜክሲኮና ጀሞ) እንዲሁም በኦንላይን በምንሰጣቸዉ  ስልጠናዎች በ Advanced level እና 90% practical በሆነ ካሪኩለም እንዲሁም ዘመኑ ያፈራቸዉን ሙሉ የላብራቶሪና የስቱዲዮ እቃዎችን በማሟላት ከሁሉም ስልጠናዎቻችን ላይ ታላቅ የዋጋ ቅናሽ አድርገናል! አሁኑኑ ይመዝገቡና ትልቅ ለዉጥ ወደሚያመጡበት ተቋም ይቀላቀሉ!

ከትምህርትና ስልጠና ጥራትና ቁጥጥር ባለስልጣን ሙሉ ዕዉቅና ካለዉ ሰርተፊኬት ጋር!

እኛጋ ለመሰልጠን ኮምፕዩተር መግዛት አያስፈልግዎትም!

የብዙ አመት ልምድ እና ብቃት ባላቸዉ አሰልጣኞች!

🎯 Graphics Design
🎯 Video Editing
🎯 Digital Marketing
🎯 Photography
🎯 Videography
🎯 Cinematography
🎯 Adobe photoshop
🎯 Fullstack Web app development 
🎯 Programming Language
🎯 Interior Design
🎯 English Language
🎯 Database
🎯 Basic Computer
🎯 Accounting Softwares
🎯 Engineering Softwares
🎯 SPSS & STATA
🎯 MS-Project
🎯  Foreign & Local Languages

አድራሻ:-
1. መገናኛ መተባበር ህንፃ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 419 (ሊፍት ይጠቀሙ)  ☎️ 0991929303

2. ሜክሲኮ ኬኬር ህንፃ 6ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 639 (ሊፍት ይጠቀሙ ሁለተኛዉን ሊፍት) ☎️ 0991929304

 3. ጀሞ 1 አንደኛ በር ካኩ ቢዝነስ ሴንተር 3ኛ ፎቅ ☎️ 0991926707

Join telegram https://t.me/topinstitutes

tiktok https://Tiktok.com/@topinstitute

Facebook https://www.facebook.com/Topinstitutes


#ቴምር ሪልስቴት
⚠️7ሳይቶችን ስርተን አስረክበናል አሁን ላይ ደግሞ ለሽያጭ ያወጣናቸው ቤቶቾ እና ሱቆች
‼️ፒያሳ (ሊሴ ገ/ማርያም ትምህርት ቤት) ጀርባ
         👉1 መኝታ 66ካሬ=
         10% ቅድመ ክፍያ 693,000ብር
         ሙሉ ክፍያ 6,930,000 ብር
         👉2መኝታ 71ካሬ
        10%ቅድመ ክፍያ 745,000ብር
        ሙሉ ክፍያ 7,455,000ብር
         👉2መኝታ 93ካሬ=
       10% ቅድመ ክፍያ 1,044,000ብር
       ሙሉ ክፍያ 10,044,000ብር
        👉3መኝታ 130ካሬ
      10%ቅድመ ክፍያ 1,365,000ብር
      ሙሉ ክፍያ 13,650,000ብር
        👉ቀሪውን 90% በ17ዙር ከፍለው         የሚጨርሱት
        👉30% እና ከዛ በላይ ለሚከፍል ከከፈሉት ላይ 25% ደረስ የሚደርስ ቅናሽ አዘጋጅተናል
‼️ፒያሳ ሱቅ ሽያጭ 
👉3.9ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ900,000ብር 4ተኛ እና 5ተኛ
👉4.2ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.2ሚሊዮን 3ተኛ
👉4.8ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.5ሚሊዮን 2ተኛ
👉5.5ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2ሚሊዮን 1ኛ
👉 7ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2.8ሚሊዮን ግራውንድ በውስጥ በኩል
👉10ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 4ሚሊዮን ግራውንድ በውጪ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
       👇👇👇👇👇👇
     +251939770177
     +251996856273


የ2017 የትምህርት ዘመን የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና የተማሪዎች ምዝገባ ሊጀመር መሆኑ ተገለጸ፡፡
===============

የ2017 የትምህርት ዘመን የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎችን በበይነ መረብ ለመመዝገብ የሚያስችል ስልጠና ለሚመለከታቸው ባለሙያዎች መሰጠቱን ከቢሮው የፈተና ክፍል የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

የትምህርት ዘመኑ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ምዝገባ ከመጭው የካቲት 3/2017 ዓም ጀምሮ እንደሚካሄድና ለምዝገባው ውጤታማነት ሁሉም የትምህርት ባለድርሻ አካላት እንዲተባበሩ ጥሪ ቀርቧል፡፡
የክልላዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ምዝገባ በ2011 ዓ.ም በጸደቀው የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ የፈተና አስተዳደር መመሪያ መሰረት የሚተገበር ነው ተብሏል፡፡


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2017 የትምህርት ዘመን የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የካቲት 3/2017 ዓ.ም ይጀምራል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2017 የትምህርት ዘመን የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የካቲት 3/2017 ዓ.ም የሚጀምር መሆኑን እናሳውቃለን፡፡


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


አዉሮፓ ጣልያን ሀገር ከፍተኛ የመሳካት እድል ያለው ነፃ ስኮላርሺፕ ለዲግሪ እና ማስተርስ ተማሪዎች እየተሰጠ እንደሆነ ሰምተዋል

👉 መሉ በሙሉ ነፃ የትምህርት እድል
👉 በአመት ከ6000€ በላይ የኪስ ገንዘብ እያገኙ የሚማሩበት
👉 ለ መጀመሪያ ዲግሪ እና ማስተርስ ተማሪዎች የተዘጋጀ

📌 እድሉ ሳያመልጥዎ ዛሬውኑ ይመዝገቡ!

📞 0934146000/0933099990

📍 ደንበል ቢትወደድ ባህሩ ህንፃ 8ተኛ ፎቅ

➘ ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ
  https://t.me/graceconsultancy


በጎንደር ዩኒቨርሰቲ የተጠኑ 14 የጥናት ውጤቶች ይፋ ሆኑ
********

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የጎንደር ከተማን ችግሮችን ሳይንሳዊ በሆነ ጥናታዊ ምርምር ለመፍታት፣ ከጎንደር ከተማ አስተዳደር ከንቲባና ከሌሎች የከተማው አመራሮች ጋር በጋራ በመምከር በ2016 ዓ.ም አስራ አራት ዋና ዋና ችግሮችን በመለየት ብሎም ለተለዩት ችግሮች መፍትሄ ለማፈላለግ የጥናትና ምርምር ቡድን በማዋቀር ወደ ስራ ገብቶ ቆይቷል፡፡ በመሆኑም የዩኒቨርሲቲው የጥናት ቡድን የደረሰበትን ውጤት ለሚመለከታቸው የጎንደር ከተማ አስተዳደር አካላት ጥር 28/2017 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲው አሉምንየም ህንጻ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይፋ አድርጓል፡፡ የጥናቶቹን ውጤትና ምክረ ሀሳቦች መሰረት በማድረግም ዩኒቨርሲቲውና ከተማ አስተዳደሩ የድርሻቸውን እንዲወስዱ ለማስቻል ያለመ እንደሆነ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
በዕለቱ መርሀ ግብር የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አስራት አፀደወይን፣ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ ወ/ሮ ደብሬ የኋላ፣ የዩኒቨርሲቲው ም/ፕሬዚዳንቶች፣ ዳይሬክተሮችና ዲኖች፣ የጎንደር ከተማ አስተዳደር የከንቲባ ኮሚቴ አባላት፤ እንዲሁም የዩኒቨርሰቲው የምርምርና የጥናት ቡድን አባላት ተሳትፈዋል፡፡
ጎንደር ከተማ ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ጋር ያለውን ተነጣጥሎ ሊታይ የማይችል ሁለንተናዊ ትስስር በእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግራቸው የገለጹት ዶ/ር አስራት፣ ዩኒቨርሲቲው ለጎንደር ከተማ አስተዳደር ያደረገውን አንኳር አስተዋጽኦ አውስተዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ በተመሳሳይ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ለጎንደር ዩኒቨርሰቲ ያደረገውን አበርክቶ ገልጸዋል፡፡
በጤናው ዘርፍ የ 100 ዓመታት አገልግሎቶችን ከመስጠት ጀምሮ በትምህርት፣ በግብርና፣ በማህበረሰብ አገልግሎትና በቴክኖሎጂ ሽግግር ተግባራት ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ለጎንደር ከተማ ያደረገውን አብይ አስተዋጽኦ በምሳሌ በማስደገፍ ዶ/ር አስራት አብራርተዋል፡፡ የጎንደር ከተማ አርሶአደሮች የእርሻ መሬት እርስታቸውን በነጻ በማስረከብ ያሳዩት ጌዜ የማይሽረው አስተዋጽኦ እንዲሁም የከተማ አስተዳደሩ የሰጠው ማስፋፊያ ቦታና ለንጹህ መጠጥ ውሀ አቅርቦት የሚያደርገው ተባባሪነት፣ ጎንደር ከተማ- ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ ካደረገው አስተዋጽኦ መካከል የሚጠቀሱ መሆናቸውን ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል፡፡
ከጎንደር ዩኒቨርሰቲ ጋር በሚያስተሳስሩ ጉዳዮች ላይ በአብሮነት በመስራታቻው ኩራት እንደሚሰማቸው በመክፈቻ ንግግራቸው የገለጹት የጎንደር ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ ወ/ሮ ደብሬ የኋላ ናቸው፡፡ ም/ከንቲባዋ በሁሉም ዘርፍ በበቂ ሁኔታ የተማረ የሰው ኃይል ካለ ብሄራዊ ጥቅምን ያለምንም ችግር ማስከበር እንደሚቻል ተናግረዋል፡፡
በመርሀ-ግብሩ መሰረት በጎንደር ከተማ ተግባራዊ የሚደረጉት 14ቱ የጥናት ውጤቶች ይዘት እና የደረሱበትን ደረጃ የገለጹት የጎንደር ዩኒቨርሰቲ የምርምር እና ቴክኖሎጅ ምክትል ፕሬዚዳንት ፕ/ር ቢኒያም ጫቅሉ፣ የጎንደር ከተማና የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ያላቸው መልካም ግንኙነት ለሌሎች ምሳሌ ሊሆን እንደሚችል ገልጸዋል፡፡ የዩኒቨርሲቲው ወጣትና አንጋፋ መምህራንና ተመራማሪዎች በሀገር አቀፍና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪነታቸው እየጨመረ መምጣቱንም አያይዘው ተናግረዋል፡፡
በትምህርቱ ዘርፍ የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ውጤታማ ማድረግ፣ የጤና ተቋማትንና አገልግሎትን ማዘመን፣ ቱሪዝምን፣ የንግድ ስርዓቱንና ኢንቨስትመንትን ማስፋፋት፣ ማዘመንና ማሳደግ፣ በግብርናና በከተማ ውበት-ከተማዋን ማልማትና ማስዋብ፣ ከተማዋን ማሳደግ፣ ስራ ፈጠራን በተመለከተ፣ ሲቪል ሰርቪስን በተመለከተ፣ ፍትህና መልካም አስተዳደር እንዲሁም ሰለምና አስተዳደርን የተመለከቱ አብይ ርዕስ ጉዳዬች በጎንደር ከተማ ከተዳሰሱት ጥናቶች ምካከል እንደሚጠቀሱ ከፕ/ር ቢንያም ጫቅሉ ገለጻ ለመረዳት ተችሏል፡፡
በመጨረሻም በዶ/ር አስራትና በወ/ሮ ደብሬ በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት በመጪው አምስትና ስድስት ቀናት ውስጥ በየሴክተር መስሪያ ቤቶች ውይይት ተደርጎ ለአጠቃላይ ውይይት ቀጠሮ ከተያዘ በኋላ የፖሊሲ መግለጫ (Policy Brief) ርክክብ በማድረግ የዕለቱ መርሀ-ግብር ተጠናቋል።


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


የትምህርት ሚንስቴር ማስታወቂያ

የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች የመዉጫ ፈተና (EXIT EXAM) የሰዓት ለውጥ ማድረግን ይመለከታል።

ዓርብ ጥር 30/2017 ዓ.ም ጠዋት 5፡30 የሚጀምረው ፈተና ወደ 7፡30 እንዲሁም ከሰዓት በኋላ 8:30 የሚጀምረው ወደ 10፡30 የተቀየረ ሲሆን የመፈተኛ ማዕከላት በነበሩበት የሚቀጥሉ መሆኑን እንገልጻለን። (ትምህርት ሚኒስቴር)

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


#ቴምር ሪልስቴት
⚠️7ሳይቶችን ስርተን አስረክበናል አሁን ላይ ደግሞ ለሽያጭ ያወጣናቸው ቤቶቾ እና ሱቆች
‼️ፒያሳ (ሊሴ ገ/ማርያም ትምህርት ቤት) ጀርባ
         👉1 መኝታ 66ካሬ=
         10% ቅድመ ክፍያ 693,000ብር
         ሙሉ ክፍያ 6,930,000 ብር
         👉2መኝታ 71ካሬ
        10%ቅድመ ክፍያ 745,000ብር
        ሙሉ ክፍያ 7,455,000ብር
         👉2መኝታ 93ካሬ=
       10% ቅድመ ክፍያ 1,044,000ብር
       ሙሉ ክፍያ 10,044,000ብር
        👉3መኝታ 130ካሬ
      10%ቅድመ ክፍያ 1,365,000ብር
      ሙሉ ክፍያ 13,650,000ብር
        👉ቀሪውን 90% በ17ዙር ከፍለው         የሚጨርሱት
        👉30% እና ከዛ በላይ ለሚከፍል ከከፈሉት ላይ 25% ደረስ የሚደርስ ቅናሽ አዘጋጅተናል
‼️ፒያሳ ሱቅ ሽያጭ 
👉3.9ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ900,000ብር 4ተኛ እና 5ተኛ
👉4.2ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.2ሚሊዮን 3ተኛ
👉4.8ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.5ሚሊዮን 2ተኛ
👉5.5ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2ሚሊዮን 1ኛ
👉 7ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2.8ሚሊዮን ግራውንድ በውስጥ በኩል
👉10ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 4ሚሊዮን ግራውንድ በውጪ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
       👇👇👇👇👇👇
     +251939770177
     +251996856273


በሶስቱም ቅርንጫፎቻችን ( መገናኛ፣ ሜክሲኮና ጀሞ) እንዲሁም በኦንላይን በምንሰጣቸዉ  ስልጠናዎች በ Advanced level እና 90% practical በሆነ ካሪኩለም እንዲሁም ዘመኑ ያፈራቸዉን ሙሉ የላብራቶሪና የስቱዲዮ እቃዎችን በማሟላት ከሁሉም ስልጠናዎቻችን ላይ ታላቅ የዋጋ ቅናሽ አድርገናል! አሁኑኑ ይመዝገቡና ትልቅ ለዉጥ ወደሚያመጡበት ተቋም ይቀላቀሉ!

ከትምህርትና ስልጠና ጥራትና ቁጥጥር ባለስልጣን ሙሉ ዕዉቅና ካለዉ ሰርተፊኬት ጋር!

እኛጋ ለመሰልጠን ኮምፕዩተር መግዛት አያስፈልግዎትም!

የብዙ አመት ልምድ እና ብቃት ባላቸዉ አሰልጣኞች!

🎯 Graphics Design
🎯 Video Editing
🎯 Digital Marketing
🎯 Photography
🎯 Videography
🎯 Cinematography
🎯 Adobe photoshop
🎯 Fullstack Web app development 
🎯 Programming Language
🎯 Interior Design
🎯 English Language
🎯 Database
🎯 Basic Computer
🎯 Accounting Softwares
🎯 Engineering Softwares
🎯 SPSS & STATA
🎯 MS-Project
🎯  Foreign & Local Languages

አድራሻ:-
1. መገናኛ መተባበር ህንፃ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 419 (ሊፍት ይጠቀሙ)  ☎️ 0991929303

2. ሜክሲኮ ኬኬር ህንፃ 6ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 639 (ሊፍት ይጠቀሙ ሁለተኛዉን ሊፍት) ☎️ 0991929304

 3. ጀሞ 1 አንደኛ በር ካኩ ቢዝነስ ሴንተር 3ኛ ፎቅ ☎️ 0991926707

Join telegram https://t.me/topinstitutes

tiktok https://Tiktok.com/@topinstitute

Facebook https://www.facebook.com/Topinstitutes


Репост из: ATC NEWS
#Remedial_Tutorial

የMathematics የሪሜዲያል ቲቶርያል ቪዲዮ ለምትፈልጉ ከላይ ባለው መማሪያ መሰረት በ100 ብር የአንድ ጊዜ ክፍያ ብቻ አቅርበንላቹሃል🥳

ቪዲዮዎቹን የምትፈልጉ 👉 @muedu


ትምህርት ሚኒስቴር የመውጫ ፈተናን (Exit Exam) ነገ ማለትም ከ5:30-8:00 ለመስጠት ያወጣውን ፕሮግራም መቀየሩ ተገለፀ‼️


ትምህርት ሚኒስቴር የመውጫ ፈተናን (Exit Exam) ነገ ማለትም ከ5:30-8:00 ለመስጠት ያወጣውን ፕሮግራም የሰአት ለውጥ በማድረግ ወደ ከሰዓት በኋላ የቀየረ መሆኑ ታውቋል።

⚡️ተፈታኞች ዩንቨርሲቲዎቻቹህ እያወጡት ያለውን የተስተካከለ የፈተና ፕሮግራም (የሰዓት ለውጥ) አረጋግጡ።

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የዶ/ር አንዱአለም ዳኘን ህልፈት ተከትሎ መሰራት ባለባቸው ስራዎች ዙሪያ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አሳለፈ

👉የዶ/ር አንዱአለም ልጆች ለከፍተኛ ትምህርት ሲደርሱ በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ በነጻ እንዲማሩ፤

👉ባለቤታቸው ከትምህርት ዝግጅት አንጻር በሲቪል ምህንድስና 2ኛ ዲግሪ እና ጥሩ አቅም ያላት በመሆኑ በዩኒቨርሲቲው የባሕር ዳር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በሲቪል ምህንድስና ትምህርት ክፍል የምትቀጠርበት ሁኔታ እንዲመቻች፤

👉ዶ/ር እንዱአለም በጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ታሪክ የመጀመሪያውን ቀዶ ህክምና የሰሩ በመሆኑና ክፍሉን እስከ ህልፈታቸው ድረስ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ለማሳደግ ከፍተኛ ጥረት በማድረጋቸው የጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የቀዶ ህክምና ዋርድ በስማቸው ዶ/ር አንዱአለም ዳኘ ቀዶ ህክምና ዋርድ ተብሎ እንዲሰየም፤

👉የዶ/ር አንዱአለምን የአገልጋይነት ጥግ እንዲሁም ለሙያው የተሰጠ ተምሳሌታዊነቱን በቋሚነት ለመዘከርና ማስተማሪያ እንዲሆን በጥበበ ጊዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ግቢ ሃውልት እንዲቆም፤

👉በህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጁ School of Medicine ውስጥ በስማቸእ Talent Scholarship እንዲቋቋም ተወስኗል።

ውሳኔው አስቀድሞ በዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት በኋላም ለዩኒቨርሲቲው ሴኔት ቀርቦ ውይይት ከተደረገበት በኋላ ይሁንታን አግኝቶ በሙሉ ድምጽ ጸድቋል።

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የጠቅላላ ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስት እና የጉበት፣ የቆሽት እና የሃሞት መስመር ሰብ ስፔሻሊት ሃኪም፣ ተመራማሪ እና መምህር እንዲሁም በጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የቀዶ ሕክምና አገልግሎት ክፍል ዳይሬክተር የነበሩት ዶ/ር አንዷለም ዳኘ በተወለዱ በ37 ዓመታቸው ባሳለፍነው ቅዳሜ በተፈፀመባቸው ጥቃት መገደላቸው ይታወሳል።

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


የዋቻሞ ዩንቨርሲቲ የአርብ ፈተና የሰዓት ለውጥ ተደርጓል‼️


አርብ ጥር 30/2017 ዓ/ም ጠዋት 5፡30 ይጀምር የነበረው ፈተና ወደ ከሰዓት በኋላ 7፡ 30 እንዲሁም ከሰዓት በኋላ 8፡30 ይጀምር የነበረው ፈተና ወደ 10፡30 የተቀየረ መሆኑን ዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ገልጿል።


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


አዉሮፓ ጣልያን ሀገር ከፍተኛ የመሳካት እድል ያለው ነፃ ስኮላርሺፕ ለዲግሪ እና ማስተርስ ተማሪዎች እየተሰጠ እንደሆነ ሰምተዋል

👉 መሉ በሙሉ ነፃ የትምህርት እድል
👉 በአመት ከ6000€ በላይ የኪስ ገንዘብ እያገኙ የሚማሩበት
👉 ለ መጀመሪያ ዲግሪ እና ማስተርስ ተማሪዎች የተዘጋጀ

📌 እድሉ ሳያመልጥዎ ዛሬውኑ ይመዝገቡ!

📞 0934146000/0933099990

📍 ደንበል ቢትወደድ ባህሩ ህንፃ 8ተኛ ፎቅ

➘ ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ
  https://t.me/graceconsultancy


የአርብ ፈተና የሰዓት ለውጥ ተደርጓል‼️


አርብ ጥር 30/2017 ዓ/ም ጠዋት 5፡30 ይጀምር የነበረው ፈተና ወደ ከሰዓት በኋላ 7፡ 30 እንዲሁም ከሰዓት በኋላ 8፡30 ይጀምር የነበረው ፈተና ወደ 10፡30 የተቀየረ መሆኑን ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ባወጣው ማስታወቂያ ገልጿል።


👉 ለግቢው ተማሪዎች የመፈተኛ ቦታው በነበረበት ይቀጥላል።


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news

Показано 16 последних публикаций.