ታምሪን ሚዲያ(Tamrin Media)✍✍✍✍✍


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


Introducing daily news and information all over the world including our country ethiopia
ለፈጣን እና ተዓማኒ መረጃዎች ቻናላችንን ይቀላቀሉ። 🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
ቻናላችንን በመቀለቀል ወቅታዊ መረጃዎቸችን በፍጥነት ያግኙ👇👇👇
https://t.me/Tamrinmedia
✉️inbox 👉 @tamrin_bot

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


ዜና ሹመት‼️

1.ጃል ሰኚ (በትግል ስሙ) ያደሳ ነጋሳ........... በቢሮ ማዕረግ የኦሮሚያ ፕሬዝዳንት የሰላም ጉዳዮች አማካሪ
2.ኦሮሚያ ረቡማ........... የኦሮሚያ ም/ከቃቤ ህግ
3.ቶሌራ ረጋሳ ...........የክልሉ የሰላምና ፀጥታ ምክትል ሃላፊ በመሆን ተሹመዋል።


ፖፕ ፍራንሲስ በጠና ታመዋል!!!

የፖፕ ፍራንሲስ ልዩ ጥበቃ ቡድን የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት የቀብር ሥነ ሥርዓቱን ለምምድ እያደረገ እንደ ሆነ አር -ቲ ዘግቧል።

ፓፕ ፍራንስስ በሳምባ ምች ተጠቅተው ሆስፒታል መግባታቸውን ቫቲካን አስታውቋል።

የ88 ዓመቱ አዛውንት ፓፕ ፍራንሲስ ከሳንባ ምች ሊተርፉ እንደማይችሉ እየተነገረ ነው።

የካቶሊክ እምነት ተከታዮች ፓፕ ፍራንሲስ በሚታከሙበት ሆስፒታል የፀሎት ፕሮግራም እያደረጉ ነው።
https://t.me/Tamrinmedia


የግራር ጃርሶ ወረዳ የጤና ጥበቃ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ታደሠ ተፈሪ ተገደሉ

የኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በሁለት ሳምንታት ውስጥ ሁለት አመራሮችን በግድያ አጥቷል

ኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የሱሉልታ ወረዳ ዋና አሥተዳዳሪ የሆኑት አበበ ወርቁ ራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት በሚጠራው ቡድን የካቲት 6 ቀን መገደላቸው ይታወሳል።

በትናንትው ዕለት ደግሞ የግራር ጃርሶ ወረዳ የጤና ጥበቃ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ታደሠ ተፈሪ፣ ለጊዜው ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች ትናንት ምሽት 11 ሰዓት ገደማ በፈጸሙት የደፈጣ ጥቃት መገደላቸውን ታውቋል ታጣቂዎቹ የደፈጣ ጥቃቱን የፈጸሙት፣ በወረዳው አዲስጌ ቀበሌ ልዩ ስሙ ''ሲልሚ'' በተባለ ሥፍራ እንደኾነ ምንጮች ተናግረዋል። ከሟቹ ጋር አብረው የነበሩት የወረዳው የብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ዝናቡ በለጠ፣ ከታጣቂዎቹ የእሩምታ ተኩስ ለማምለጥ ሲሞክሩ ድንጋያማ ገደል ውስጥ ጉዳት እንደደረሰባቸውና ፍቼ ሆስፒታል ለሕክምና መግባታቸውን ምንጮቹ ገልጸዋል። አመራሮቹ ጥቃቱ የተፈጸመባቸው፣ ባካባቢው በሚገኝ አንድ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ምልከታ አድርገው ሲመለሱ ነው ተብሏል።


🇪🇹 🇸🇩

ኢትዮጵያ ለሱዳን የሰብዓዊ ድጋፍ 15
ሚሊየን ዶላር ለገሰች::

ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ ለሱዳን ህዝብ ሰላምና መረጋጋት ድጋፏን አጠናክራ እንደምትቀጥል ገልጸዋል።
በሱዳን የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦት ላይ የሚመክር የመሪዎች ጉባኤ

* በኢትዮጵያ
* በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች
* በአፍሪካ ህብረትና
* ኢጋድ

አዘጋጅነት በአዲስ አበባ የተካሄደ ሲሆን

ጉባኤው የሱዳንን ቀውስ ለማስቆም በተለይም በረመዳን የጾም ወቅት የተኩስ አቁም እንዲደረስ እና የሰብዓዊ ድጋፍ ለሱዳናውያን እንዲደርስ ለማስቻል የተደረገ ነው።

በጉባኤው የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያና ሱዳን ጎረቤት ሀገራት ብቻ ሳይሆኑ ጠንካራ ቁርኝት ያላቸው ሀገራት ናቸው ብለዋል።
ኢትዮጵያ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ከሱዳን ህዝብ ጎን ትቆማለች፤ ባላት አቅምም የምታደረገውን የሰብዓዊ ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ተናግረዋል።
በዚህም ኢትዮጵያ ለሱዳን የሰብዓዊ ድጋፍ 15 ሚሊየን ዶላር ለግሳለች ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)።

ዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ ለሱዳን ዘላቂ ሰላም መስፈን እንዲሁም የሱዳን ተፋላሚ ሃይሎች ለሰላማዊ መፍትሄ እንዲሰለፉ ጥሪ አቅርበዋል።

የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በበኩሏ ተጨማሪ
200 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ሰጥታለች😂😂😂😂


ሰበር_ዜና!!
ህወሓት ከፖለቲካ እንቅስቃሴ ታገደ
= = = = = = = = = = = =
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህ ወሓት ከፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ማገዱን በጻፈው ደብዳቤ አሳውቋል።


ዋና አስተዳዳሪው ተገደሉ

በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የሱሉልታ ወረዳ ዋና አሥተዳዳሪ የሆኑት አበበ ወርቁ ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ በሚጠራው አማጺ ቡድን በደረሰባቸው ድንገተኛ ጥቃት መገደላቸው ተሰማ

ታጣቂ ቡድኑ ጥቃቱን የፈጸመው ዛሬ የካቲት 5 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 9 ሰዓት አካባቢ መሆኑን ከወረዳ አሥተዳዳሪው ጋር የነበረ የወረዳው የጸጥታ ዘርፍ ኃላፊ በቡድኑ ታፍኖ መወሰዱን አስረድተዋል።

ዋና አሥተዳዳሪው፣ የጸጥታ ዘርፍ ኃላፊው እና በርካታ የጸጥታ ኃይሎች ታጣቂ ቡድኑ በስፋት ይንቀሳቀስበታል ወደተባለው "ሞዬ ጋጆ" በተባለው ስፍራ ሲደርሱ አማጺ ቡድኑ ድንገተኛ የእሩምታ ተኩስ እንደከፈተባቸው ተጠቁሟል።

ለጊዜው ቁጥራቸውን ማጣራት ያልቻለችው የጸጥታ ኃይሎች ሲገደሉ፣ በርካቶች ደግሞ ቆስለው ጫንጮ ሆስፒታል መግባታቸውን ምንጮች ተናግረዋል።

ከጸጥታ ዘርፍ ኃላፊው በተጨማሪ በርካታ የጸጥታ ኃይሎች በቡድኑ ታፍነው ተወስደዋል

ከወራት በፊትም በተመሳሳይ በዚሁ ታጣቂ ቡድን ጥቃት የወረዳው ፖሊስ አዛዥ የሆኑት ኮማንደር ለገሰ ሥዩም መገደላቸው ይታወሳል።

ሟቹ አበበ ከሁለት ዓመት በፊት የወረዳው ዋና አሥተዳዳሪ ሆነው ከመሾማቸው በፊት፣ የወረዳው የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ ነበሩ
https://t.me/Tamrinmedia


በደብረ ብርሃን ከተማ አሥተዳደር በመኪና ጋራዦች ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ የንብረት ውድመት ደረሰ።

ከለሊቱ 10:30 ገደማ የተነሳው እሳት ከ10 በላይ ተሽከርካሪዎችን ለውድመት ዳርጓል።

በእቴጌ ጣይቱ ክፍለከተማ አየማን መናፈሻ አቅራቢያ የነበሩ ሁለት ጋራዦች ላይ ነው የእሳት አደጋው የደረሰው። በአደጋው በጋራዦቹ ውስጥ ቆመው የነበሩ ተሽከርካሪዎች ናቸው ውድመት የደረሰባቸው።

የደብረ ብርሃን ከተማ እሥተዳደር ፖሊስ መምሪያ ኀላፊ ኮማንደር ታዬ ኀይለጊዮርጊስ የእሳቱ መነሻ ከጋራዦቹ ውስጥ ይሆናል ተብሎ የተገመተ ሲሆን አጠቃላይ መንስኤ እና የደረሰው ጉዳት ተጣርቶ ይገለፃል ሲሉ ተናግረዋል።
https://t.me/Tamrinmedia


ህወሓት ጉባኤ ባለማድረጉ ምክንያት ይሰረዛል !
==== = == = = = =
ህወሓት እንደ ፓርቲ በነሓሴ 3/2016 ዓ/ም በልዩ ሁኔታ እንደ አዲስ መመዝገቡን ይታወቃል። በዚህ የልዩ ዳግመ ምዝገባ ሂደት ምርጫ ቦርድ የህወሓት ምዝገባውን ይፋ ከተደረገ በኋላ ባሉት ስድስት ወራት ጉባኤ ማደረግ እንዳለበት በፅሑፍ ተነግሮታል።
ሆኖም ህወሓት ማደረግ የነበረበትን ጉባኤ የመጨረሻ ቀኑ ዛሬ የካቲት 3/2017ዓ/ም ቢሆንም ህጋዊ ጉባኤ ሳያደርግ ቀነ ገደቡ አልፋል!
https://t.me/Tamrinmedia


ዶናልድ ትራምፕ የአፍሪካ መሪዎች ሰው መሆናቸውን እጠራጠራለሁ አሉ‼️

👉🏿 ከ50 ዓመታት የአህጉሪቷ የነጻነት ጉዞ በኋላ፣ ለህዝባችው አስፈላጊውን መሠረተ ልማት ካላሟላችው ሰው ነን ብላችው ታስባላችው?

👉🏿በወርቅ፣ በአልማዝ፣ በነዳጅ፣ በዩራኒየም፣ በብረት፣ በማዕድን፣ በብር፣ በማግኒዥየም፣ በነሐስ፣ በጋዝ የተፈጥሮ ሃብቶቻችው ላይ ተቀምጣችው፣ ህዝባችው በረሃብ፣ በትምህርት አለመዳረስ፣ በጤና አገልግሎት እጦት፣ ቢሞት፣ ሰው ነን ብላችው ታምናላችው?

👉🏿በስልጣን ላይ ቆይታችው፣የራሳችሁን ዜጎች ለመግደል ከውጭ የጦር መሣሪያዎችን ስታስገቡ፣ ሰው ነን ብላችው ታስባላችው?

👉🏿የገዛ ዜጎቻችሁን እንደውሻ ስታንገላቱና ስትገድሉ፣ ማን ዜጎቻችሁን እንዲያከብር ትጠብቃላችው?

👉🏿በራሳችው አገር ላይ ቀማኛና ሌባ በመሆናችው ፣ የሃገራችሁን ሀብቶች ሁሉ በመስረቅ፣ አብዛኞቹ ዜጋዎቻችው በስደትና በድህነት ውስጥ እንዲያልፉ ስታረጉ፣ የሰው ልጆ ነን ብላችው ታስባላችው?
ሲሉ ተናግረዋል😂😂😂


ስማቸውን ወደ “ትራምፕ” የቀየሩት ፖለቲከኛ

ቤን ዳውኪንስ የተባሉ የአውስትራሊያ ፖለቲከኛ ስማቸውን ወደ ኦሲ ትራምፕ ቀይረዋል።

ፖለቲካኛው ስማቸውን በአሜሪካው ፕሬዚዳንት ስም መሰየሙ ትኩረት ለማግኘት እና የትራምፕ የፖለቲካ አቋም ደጋፊ መሆናቸውን ለመግለጽ ነው ብለዋል።

በአዲሱ ስማቸው ኦሲ ትራምፕ የተባሉት ግለሰብ የምዕራብ አውስትራሊያ የላይኛው ምክር ቤት አባል ሲሆኑ የዶናልድ ትራምፕ ጸረ ግራ ዘመም ፖለቲካ አቋም አድናቂ እንደሆኑ ተናግረዋል።

ሰውዬው እንደ ዶናልድ ትራምፕ ሁሉ ነዳጅ እና ጋዝ በብዛት ማውጣትን የሚደግፉ ሲሆን “ዶናልድን ቢሮው ደውላችሁ አግኙት” ሲሉ “ክቡር ኦሲ ትራምፕ ኤምኤልሲ” በሚል በአዲሱ ስም በከፈቱት የኤክስ ገጻቸው አስፍረዋል።

ፖለቲከኛው ስማቸውን የቀየሩበት ምክንያት ለአገሪቱ ገዢ ፓርቲ ያለውን ተቃውሞ ለማሳየት ነውም ተብሏል።

ይህንንም ተከትሎ የምዕራብ አውስትራሊያ ገዢው ፓርቲ መሪ የሆኑት ሮጀር ኩክ የፖለቲከኛው ተግባር ትኩረት ፍለጋ የተደረገ አትርሱኝ ባይነት ነው ሲሉ ተችተውታል።

የምዕራብ አውስታራሊያ ግዛት በቀጣዩ ወር ምርጫ እንደምታካሂድም ስካይ ኒውስ ዘግቧል።
https://t.me/Tamrinmedia


አስገራሚ ዜና

የመቀሌ ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ መድህን በ75 ዓመታቸው ወለዱ።

ከዚህ ቀድም በ73 ዓመቷ ሕንዳዊ ተይዞ የነበረው ክብረ ወሰንም በእጃቸው ማስገባት ችለዋል።

"በዚህ ዕድሜየ ልጅ አገኛለው ብየ አስቤው አላውቅም፤ ከአርግዘሻል ስባልም ማመን አልቻልኩም ነበር፤ ስምንት ወር እስኪሞላኝ ድረስ በምስጢር ይዤ ነው የጤና ክትትል ያደረግኩ" ብለዋል ወይዘሮ መድህን ባርካ።

መረጃው የድምፂ ወያነ ቴሌቪዥን ነው


በጋምቤላ ክልል የመንግስት የሥራ ሰዓት ለውጥ ይደረጋል።

ከነገ ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆነው የሥራ ሰዓት ለውጥ በሙቀት መጨመር ሳቢያ ነው ተብሏል።

በክልሉ የሙቀቱ መጨመር ለሥራ ምቹ ባለመሆኑ ነገ የሚጀምረው የሥራ ሰዓት ለውጥ ለ3 ወራት ይቆያል።

በዚህ መሰረትም ቀደም ሲል የመደበኛው የሥራ ሰዓት ከጠዋቱ 1፡00 እስከ 6 ፡30 የነበረው ከ1፡00 እስከ 5፡30 ይሆናል።

እንዲሁም ከሰዓት በኋላ ከቀኑ 9፡00 እስከ 11፡30 የነበረው ከ10፡00 እስከ 12፡30 እንዲሆን የክልሉ አስተዳደር ወስኗል።

የሥራ ሰዓት ለውጡ በማጃንግ ዞን የመንገሺና ጎደሬ ወረዳዎችን እንደማይጨምር ተጠቁሟል።
https://t.me/Tamrinmedia


አርቲስት ቴዎድሮስ ተሾመ ፤ የግሮቭ ጋርደን ባለቤት እንደፃፈው!...
***

ግሮቭ ጋርደን ወደ ትዝታነት ተቀይሯል።
ለወንዝ ዳርቻ ልማት ቦታውን ለቋል።

ላለፉት አምስት አመታት አብራችሁን ለነበራችሁ የዕለት ተዕለት ደንበኞቻችን፣ ሠርጋችሁን በግሮቭ ጋርደን ለደገሳችሁ ሙሽሮቻችን፣ የፍቅር ጥያቄያችሁን በግሮቭ ጋርደን ያደረጋችሁ እጮኛሞቻችን፣ልደታችሁን እኛ ጋ ላደረጋችሁ ልጆቻችን፣
የጋብቻ በዓላችሁን በግሮቭ ላከበራችሁ አንጋፋዎቻችን፣ በኦፕን ኤር ሲኒማችን ተቃቅፋችሁ ለደመቃችሁ ፍቅረኞቻችን፣
በሰርከስ ዝግጅቶቻችን እርካታን ለሸመታችሁ ቤተሰቦቻችን፣ እግር ኳስ በሜዳችን ለተጫወታችሁም በስክሪናችን ለኮመኮማችሁም የስፖርት ወዳጆቻችን፣
መጽሐፎቻችሁን ላስመረቃችሁ ደራሲዎቻችን፣
ፊልሞቻችሁን ለቀረፃችሁ አርቲስቶቻችን፣
ክሊፖቻችሁን ላስከሸናችሁ ድምፃውያኖቻችን፤
ለሁላችሁም ከልብ የመነጨ ምስጋናችን ይድረሳችሁ።

በአገልግሎታችን ቅር ለተሰኛችሁ ምህረታችሁን እንሻለን።
ለተደሰታችሁ ደግሞ የትዝታችሁ አካል ስለነበርን ደስታችን ወደር የለውም።

የግዮን ሆቴል ሰራተኞችና አመራሮች ለነበረን ቆይታ እናመሠግናለን።
ባስከፋናችሁ ይቅርታችሁን እንሻለን።
ላስከፋችሁን ደግሞ ይቅር ብለናል።

ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን አብዝቶ ይባርክ!!
አሽቃባጭም አልተረፈም ዘንድሮማ😂😂😂
https://t.me/Tamrinmedia

Показано 13 последних публикаций.