«ሱና የኑሕ መርከብ ናት »


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


✍🏽‏ قال العلامة ربيع المدخلي -حفظه الله- :

*《 ما ضاع شباب الأمة وما ضاع الناس ،*
*إلا بالسكوت على الباطل 》.‏*
📓 |[ المَـصـدَرُ : المجموع (436/15) ]|

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


ታላቅ ብስራት ለሰለፍዮች በሙሉ
~~~~>

በአይነቱ ልዩ የሆነ ታላቅ ኢስላማዊ ኮንፈረንስ

የኮንፈረንሱ መሪ ቃል “ዲናችንን ማወቅ መተግበርና ማስተማር”

🏝 የኢትዮጵያ አህለ ሱና ኢስላማዊ ማህበር ታላቅ ሀገር ቀፍ ኢስላማዊ ኮንፈረንስ ጥቅምት ላይ በአዲስ አበባ ከተማ ለማካሄድ አስቧል።
=> ለዚህ ፕሮግራም የአዳራሽ ኪራይ፣ ለተሳታፊዎች ሻይ ቡና ፣ ለዑለማዎች ትራንስፖርትና ማረፊያ ወዘተ የሚያስፈልገውን ወጪ ለመሸፈን እንዲቻል የአንድ ሰው መግቢያ ትኬት 1000 ብር ነው

🔹 ስለሆነም ትኬት በአካል መግዛት ለምትፈልጉ፦
➡️  አል ኢስላሕ መድረሳ
➡️  ዳሩ ሱና የሸሪዓ እውቀት ማዕከል

🔹በባንክ አካውንት ለምትጠቀሙ
የባንክ አካውንት ቁጥር፦ 1000650550718
          ሙሒዲን ሳሊሕ እና ዩሱፍ ኸድር

   የኢትዮዽያ አህሉ ሱና ኢስላማዊ ማህበር

https://t.me/alateriqilhaq


👉 ሬቻ ባህል ወይስ ባእድ አምልኮ

አብዛኞች ሬቻ የኦሮሞ ህዝብ ፈጣሪውን የሚያመሰግንበት ባአል ነው ይላሉ ። በዚህም ሙስሊሙም ክርስቲያኑም እንዲያከብረው ብዙ ይወተውታሉ ።
ለዚህም ይመስለኛል አብዛኛዎች ሙስሊሞች እንደውም ተውሒድን ተረድተናል የሚሉትም ጭምር ይህን ባአል ሲያከብሩ የሚታዩት ። ለማንኛውም ለባአሉ የሚሰባሰቡ አካላት የሚፈፅሙትን ተግባር በማየት ምንነቱን ማወቅ ይቻላል ።
በዚህ ባአል ላይ ከሚፈፀሙ ተግባራት ውስጥ የአባ ገዳ ምልክት የሆነውን ዛፍ ቅቤ መቀባት ፣ መሳለም ፣ አጠገቡ ደርሶ ስጁድ መውረድ ፣ እጅ ዘርግቶ መለመን እንዲሁም ወንዝ አጠገብ ስጁድ መውረድ ፣ በሳር ከወንዙ ነክሮ በራስ ላይ መርጨትና የመሳሰሉ ተግባራቶች ይገኙበታል ።
እነዚህ ተግባራት በየትኛው መመዘኛ ነው የፈጣሪ ማመስገኛ የሚሆኑት ? ምናልባት ፈጣሪዬ እንጨት ነው ብሎ የሚያምን ካልሆነ በስተቀር ። እንዴት አንድ ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ ሌላ አምላክ የለም ብሎ የምስክርነት ቃሉን የሰጠ ሙስሊም በእንደዚህ አይነት የባእድ አምልኮ ውስጥ ይዘፈቃል ?
እስልምና አላህ ማለት ሁሉን የፈጠረ ፣ የፍጥረተ ዐለሙ አስተናባሪ የሆነ ፣ አምሳያ የሌለው ፣ ያልወለደ ፣ ያልተወለደ ፣ ያማሩ ስምና ባህሪይ ያሉት ፣ በአምልኮት ብቸኛ የሆነ አምላክ እንደሆነ ነው የሚያስተምረው ። አማኞች አላህን የሚገዙባቸው የአምልኮ አይነቶች ፈርድና ሱና ( ግዴታና በፈቃደኝነት የሚሰሩ ) ብሎ ደንግጓል ።
የአላህ መልእክተኛ እኔ ባላዘዝኩት መልኩ አላህን የተገዛ ሰው ስራው ተመላሽ ነው አላህ ዘንድ ተቀባይነት የለውም ብለው አላህን የምንገዛባቸው የአምልኮ አይነቶች በመረጃ ላይ የተገደቡ መሆናቸውን ገልፀው ትልቅ መርህ አስቀምጠዋል ።
ለአላህ ብቻ የሚገቡ የአምልኮ አይነቶች እንደ ስጁድ ፣ ስለት ፣ ዱዓእ ( ሰላምን ፣ ፍቅርን ፣ ዝናብን ፣ ጤናን ፣ በረከትን ፣ ስኬትን ፣ መለመንን) ከአላህ ውጪ ካለ አካል ከመላኢካም ፣ ከነብይም ፣ ከወልይም ፣ ከጅንም ፣ ከአድባርም ፣ ከቆሌም ፣ ከጨሌም ፣ ከእንጨትም ፣ ከድንጋይም … ወዘተ መፈለግ ከእስልምና የሚያወጣ የሽርክ ተግባርና አላህ የማይምረው መሆኑን ቁርኣንና ሐዲስ አፅኖት ሰጥቶ ገልፆታል ።
ታዲያ እንዴት ከላይ የተጠቀሱት ተግባራት የሚከናወኑበትን ሬቻ ሙስሊሞች ያከብሩታል ? እንዴትስ ለእንጨት መስገድና ቁርባን እያቀረቡ ችግራቸውን ነግረው ፈረጀት መጠየቅ ባህል ሊሆን ይችላል ? ለወንዝ እየሰገዱ ፈውስ ፍለጋ ከውሀው መረጨት እንዴት ከአምኮትነት ወጥቶ ባህል ይሆናል ? ከሆነም የሽርክና የኩፍር ባህል ነው ሊሆን የሚችለው ። ኢስላም የዚህ አይነቱን አምኮ ፈጣሪን ሳይሆን ሸይጣንን ማምለክ እንደ ሆነ ነው የሚያስተምረውና ሙስሊሞች አኼራችሁን እንዳትከስሩ ተጠንቀቁ !!! ።

http://t.me/bahruteka


🔴 ቀጥታ ስርጭት

📚 كتاب الداء والدواء

👉 ደርሱ በቀጥታ ስርጭት ይተላለፋል

ደርሱ የሚጀምረው ከገፅ 104

فصل ـ المعاصي مدد من الإنسان لعدوه

عند قوله رحمه( وجماع هذه الثلاثة وعمودها التي تقوم به هو تقوى الله تعالى

{ክፍል 38}

የኪታቡን pdf ሊንክ ለማግኘት👇

https://t.me/abuabdurahmen/4883


የጁሙዓ ኹጥባ
(ርዕስ መውሊድ ቢድዓ ነው)

🎙አቡአብዲረህማን አብዱልቃዲር ሐሰን (ሀፊዘሁሏህ)

https://t.me/abuabdurahmen


#ስለ_መውሊድ_በኡለሞቻችን
➪➩➪➩➪➩➪➩➩➩

በአለም ላይ ታዋቂ የሆኑና በአላህ ፍቃድ ባላቸው እውቀት ከጥመት ባለቤቶች ውጭ ትንሽ ትልቁ፤ ሴት ወንዱ የሚያከብራቸው ውድና የተከበሩ የሱና መሻይኾች በአሁኑ ሰዓት እየተደገሰ ስለሚገኘው መውሊድ የሰጡት የተለያዩ ትምህርት ሲሆን ከታች በሊንክ ቀርቦላችኋል

ታላላቅ ኡለሞች ስለ
መውሊድ ምን አሉ?

╭─••─═••═─•••─╮
✅ ክፍል ❶ እስከ ⓯
╰─••─═
••═─•••─╯

❶ኛ ➦ በታላቁ ዓሊም አንደበት
ስለ
#መውሊድ
🎙 سماحة الشيخ عبدالعزيز بن باز رحمه الله
🎙 በሸይኽ አብዱል አዚዝ ኢብኑ ባዝ ረሂመሁሏህ

በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3911

➋ኛ መውሊድ ቢድዓ ስለመሆኑ ስለ አጀማመሩም
↩️ هل الإحتفال بالمولد بدعةٌ أو سُنّةٌ؟ومتىٰ عُرف هذا الإحتفال، ومتىٰ بدأ؟
🎙 فضيلة الشيخ العلامة محمدأمان بن علي الجامي رحمه الله تعالى

🎙 በሸይኽ ሙሐመድ አማን ቢን አልይ አልጃሚ ረሂመሁሏህ

በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3920

➌ኛ ለነብዩ መውሊድ መሰባሰብ ይቻላልን?
↩️ هل يجوز أن نحتفل بالمولد النبوي؟
🎙 فضيلة الشيخ  سليمان الرحيلي حفظه الله

🎙 በሸይኽ ሱለይማን አሩሃይሊ ሀፊዘሁሏህ

በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3924

➍ኛ  ነብዩ ﷺ ረቢዕ 12 ቀን ተወልደዋልን?
↩️ هل ولد النبي ﷺ يوم ١٢ ربيع الأول؟
🎙  فضيلة الشيخ سليمان الرحيلي حفظه الله

🎙 በሸይኽ ሱለይማን አሩሃይሊይ ሀፊዘሁሏህ

በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3938

❺ኛ አጠር መጠን ባል ገለፃ የቀረብ ወሳኝ ነጥብ መውሊድ ቢድዓ ለመሆኑ
🎙الشيخ الدكتور عبد العزيز الريس حفظه الله
🎙 በሸይኽ አብዱልአዚዝ አረይስ ሀፊዘሁሏህ

በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3943

❻ኛ በዲናችን ላይ የፈለሰፈ በሚለው ሀዲስ ላይ ተዕሊቅ በዛውም ለመውሊድ ምላሽ ተሰጥቶበታል።
↩️ تعليق مهم على حديث "من أحدث في أمرنا" وفيه الرد على بدعة المولد
🎙 الشيخ محمد بن علي بن آدم الإتيوبي الولوي

🎙 በታላቁ ኢትዮጵያዊ ዓሊም ሙሐዲስ አሽ‐ሸይኽ ሙሐመድ ብን ዓልይ ብን አደም ረሂመሁሏህ

በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3946

❼ኛ መውሊድ ቢድዓ ሊሆን እንዴት ቻለ?
➺ መውሊድን የጀመሩት እነማን ነበሩ?
➺ ሶሃቦችስ መውሊድን አክብረዋልን?

🎙 الإمام الفقيه العلامة محمد بن آمان بن علي الجامي رحمه الله تعالى
🎙 በታላቁ ኢማም ሙሀመድ ቢን አማን አልጃሚ ረሂመሁሏህ

በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3951

➑ኛ በመውሊድ ዙሪያ ጥሩ ግንዛቤ የሚያስጨብጥ ወሳኝ ሙሐደራ ነው።
➽ በምርጥ አገላለፅ አቅርበውልናል።

🎙 الشيخ محمد بن صالح العثيمين رحمه الله تعالى
🎙 በሸይኽ ኢብኑ ኡሰይሚን
ረሂመሁሏህ

በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3953

❾ኛ ለመውሊድ የአቡ ለሃብን መናም መረጃ ለሚያደርጉ ምላሽ
↩️ الرد على من يستدل بمنام أبي لهب في جواز الاحتفال بالمولد
🎙 الشيخ محمد بن علي بن آدم الإتيوبي الولوي

🎙 በታላቁ ኢትዮጵያዊ ዓሊም ሙሐዲስ አሽ‐ሸይኽ ሙሐመድ ብን ዓልይ ብን አደም ረሂመሁሏህ

በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3955

❿ኛ ጥሩ ቢድዓ አለን? ለመውሊድ መሰባሰብስ ፍርዱ ምንድን ነው?
↩️ هل هناك بدعة حسنة؟ وحكم الإحتفال بالمولد؟
🎙 الشيخ العلامة الإمام عبد العزيز بن عبد الله بن باز رحمه الله تعالى


በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3958

⓫ኛ ስለ መውሊድ ሁክም በተለያዩ ታላላቅ ዓሊሞች
↩️ حكم الإحتفال بالمولد النبوي
✅ لمجموعة من العلماء الأكابر:
🎙 الإمام مقبل الوادعي
🎙 الإمام ابن عثيمين
🎙 الإمام الألباني
🎙 الإمام ابن باز
رحمهم الله جميعًا

በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3960

⓬ኛ እጅግ በጣም #ማራኪ አገላለፅ በመውሊድ ዙሪያ
🎙 الشيخ محمد بن صالح العثيمين رحمه الله تعالى
🎙 በሸይኽ ኢብኑ ኡሰይሚን ረሂመሁሏህ

በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3966

⓭ኛ የነብዩ ﷺ መውሊድ በሚከበርበት ቦታ መገኝት ፍርዱ ምን ይሁን?
🎙 العلامة الإمام : مقبل بن هادي الوادعي ـ رحمه الله تعالى
🎙️ በሸይኽ ሙቅቢል ኢብኑ ሃዲ አል-ዋዲዒ
ረሒመሁሏህ

በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3970

⓮ኛ ነብያችን ከመውሊድና መውሊድ ላይ ከሚፈፀመው ጥፋት የጠሩ ናቸው።

➡️ ሰኢድ አልኩመልይ ለተባለው ሱፍይ የተሰጠ መልስ

🎙 العلامة الإمام : صالح بن فوزان الفوزن  حفظه الله
🎙️ ሸይኽ ሷሊህ ፈውዛን አልፈውዛን ሐፊዘሁሏህ።


በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3973

⓯ኛ መውሊድ ሲደርስ ስለ ረሱላችን ﷺ የሕይወት ታሪክ፣ ባህሪያት ማውራት ይቻላል?
🎙 العلامة الإمام : صالح بن فوزان الفوزن  حفظه الله
🎙️ ሸይኽ ሷሊህ ፈውዛን አልፈውዛን ሐፊዘሁሏህ።

በዚህ ያገኙታል ⬇️⬇️⬇️⬇️
https://t.me/AbuImranAselefy/3977


~

~ ቆይ አንተ የቢድዓ ሰው ካልሆንክ የቢድዓን ሰው 100 ግዜ ብናሰጠነቅቅ ምን አቅለሸለሸህ ?
ያንተ ወቀሳ አያስቆመን ልክ ያንተ ውዳሴ እንደማያሰደንቀን
ሽሮ ቢደነፋ እንጀራ እስኪቀርብ !
ለባጢል በመታገል ወገባችሁ ቢጎብጥ ቢቆረጥ ሀቅን ማለፍ አትችሉም ይቅርባችሁ

ግርም ይላል የኢኽዋን የሂዝቢይ የአህባሽ የሱፊይ ልጆች ሳይደንቃችሁ ገና ሀ ብለን ኢኽዋን ስንል ልክፍት እንዳለበት የሚያንቀጠቅጥህ ለምንድን ነው እስቲ ከራስህ ጋር ሆነህ ባንተ እና በአሏህ መካከል እራስህን ጠይቅ ለሀቅ ክፍት ሁን ፀሃይ ከወጣች በኃላ የሚጠራጠር ሳይተኛ የሚቃዥ ሁሉ በሰለፊያ ሊያደናግር ይፈልጋል !
ዝንቦቹ ቢሄዱ ንቦች አሉ!

በመጨረሻም ለሰለፊዮች አሏህ ልባቸውን አንደከፈተው ልባችሁን አሏህ ይክፈትላችሁ

https://t.me/abuabdurahmen


🎧አቂቃን በተመለከተ ወሳኝ ሙሐደራ
🎙በሸይኹና ሸይኽ አቡዘር አቡ ጦለሃ(ሀፊዘሁሏህ)

🎙أحكام العقيقة🎧

ከተዘረዘሩ ዋና ዋና አንኳር ነጥቦች በጥቂቱ➘➘

➔አቂቃ ሁክሙ ምንድን ነው?

➔አቂቃ ወቅቱ መቸ ነው?

➔ወድቆ የተገኘ አቂቃ ማነው የሚያወጣለት?

➔በዝሙት የተወለደ አቂቃ ማነው የሚያወጣለት?

➔ከ4 ወር በታች ሆኖ ውርጃ ከተከሰተ አቂቃ አለው ወይ?

➔ከ4 ወር በላይ ያለውስ አቂቃ አለው ወይ?

➔አቂቃ የሚወጣበት ምክናየት ምንድን ነው?

➔አቂቃና ኡዱህያ አንድ ላይ ቢከሰቱ በአንዱ መብቃቃት ይቻላል ወይ?

➔ለአንድ ወንድ ልጅ አቂቃ ስንት በግ ወይም ስንት ፍየል ነው መታረድ ያለበት? ለሴትስ?

➔አቂቃን ማከፍፈል ይቻላል ወይ?
➔ ለሁለት ለሶስት...ልጆች በአንድ ቀን ማውጣት ይቻላል ወይ?

➔አንድን አቂቃ ለብዙ ልጆች ማረድ ይቻላል ወይ?

➔አቂቃን ማረድ ነው የሚበልጠው በደረጃ ወይንስ በግ የሚገዛበትን ገንዘብ በሶደቃ መልኩ መስጠት?

➔አንድ ካፊር ቢስልም ለራሱም ለልጆቹም አቂቃን ማውጣት አለበት ወይ?

➔አባትና ልጅ የተለያየ ቦታ ከሆኑ አቂቃው የት ነው መታረድ ያለበት አባቱ አለበት ወይንስ ልጁ የለበት?

እነዚህና ሌሎችም ብዙ ጠቃሚ ነጥቦች ተዘርዝረዋል በማዳመጥ ተጠቃሚ ሁኑ!!!
➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘➘
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha
href='' rel='nofollow'>


⚠️ የተምዪዕ ጅብ በላው ⚠️

ፈፅሞ አንድ አልሆንም - ጫከ እገባለው፤
የሚቀብረኝ ባጣ - አንድ አልሆንም ያለው፤
አሞራ ይብላኝ ብሎ - የተናዘዘው ሰው፤
እንዳወራው መሆን - አልቻለም አቀተው፤
በሰለፎች መንገድ - መታገስ ከበደው፤
የትናንቱን መንሀጅ - አሽቀንጥሮ ጣለው፤
በእውቀት ላይ ላልሆነ - እንደ እሱ ላለ ሰው፤

በእርግጥ ይከብዳል - ሀቅ መራራ ነው፤
ወኔ ብቻ አይበቃም - እውቀት የግድ ነው፤
እውቀትም አያብቃቃም - ሂዳያ በአላህ ነው፡፡

ወንድሞች እያሉት - የሚቀብረው ሰያጣ፤
በቁሙ እያለ - አሞራውም ሳይመጠ፤
እንዳወራው አልሆነም - አቋሙን ለወጠ፤
ወደ ስምጡ ባህር
- በቶሎ ሰመጠ፤
ማገዶም ሳይፈጅ - በፍጥነት ቀለጠ፤
ለኢክዋን የበኩር ልጅ - አምኖ እጁን ሰጠ፡፡

ትናንት በወኔ - ሱና እንዳለገሰ፤
የበሰለ መስሎት - ዛሬ በሰበሰ፡፡
ትናንት ባህርዳር ላይ - ልብስ እንዳልቀደደ፤
በተምዪዕ መሰላል - ቀስ ብሎ ወረደ፡፡
ጫከ እገባለሁ ብሎ - እንዳልደነፋ፤
ከተማ ውስጥ ሆኖ - በአፍጢሙ ተደፋ፡፡
ፈፅሞ አንድ አልሆንም - ጫከ እገባለው፤
አሞራ ይብላኝ ብሎ - የተናዘዘው ሰው፤
እንዳወራው መሆን - አልቻለም አቀተው፤
ፈተናው እንደመጣ - ከጅምር ከበደው፤
ጥርት ባለው ሀቅ - የእሱ ጉልበት ከዳው፤
ወደ ተምዪዕ ሄደ - ትርምስምስ ወደለው፤
ፈፅሞ አንድ አልሆንም - ጫከ እገባለው፤
አሞራ ይብላኝ ብሎ - የተናዘዘው ሰው፤
ሞቶ ሬሳ ሳይሆን - በቁሙ እያየነው፤
አሞራው ጋ ሳይደርስ - ሞቶ ሳንቀብረው፤
በህይወት እያለ - የተምዪዕ ጅብ በላው፡፡


✍️ (ኢብኑ ኑሪ) ሐምሌ 15/2016
ስልጤ (ሳንኩራ)

ተጨማሪ ትምህርቶችን ለማግኘት ወደ ቻናላችን #ጆይን ይበሉ 👇👇👇
https://t.me/Ibnushaffi
https://t.me/Ibnushaffi
https://t.me/Ibnushaffi




.
⚠️ ማስታወሻ!

🔘 ዓሹራን ለመፆም ያቀዳችሁ!

🗓 መጪው #ሰኞ ሙሐረም 9ኛው እና #ማክሰኞ ደግሞ ሙሐረም 10ኛው [ዓሹራ] ነው።

የዓሹራ ቀን ፆም በሐዲስ እንደመጣው ያለፈውን አንድ ዓመት ወንጀል ያሰርዛል።  አሏህ ይወፍቀን።

📨 ሌሎችን በማስታወስ በአጅሩ ተካፋይ ይሁኑ!

https://t.me/menhajaselefiyaa




ጋብቻ

🎤 በሸይኽ ሙሐመድ ወሌ ረሒመሁላህ
t.me/Abdurhman_oumer/8553


ልዩ እና ገራሚ ሙሐደራ
🔍🔍🔍🔍🔍🔍

✅ እያንዳንዱ ሰው ስ
ላለበት አማና
✅ አደራን የመወጣት አስፈላጊነት
➜ ይህ ሙሐደራ
   ➧ ኡስታዝ ያለበት አደራ
   ➧ ሚስት
ያለባት አማና
   ➧ ዶክተር ስላለበት አማና
   ➧ ተማሪ
ስላለበት አደራ
   ➧ ሰራተኞች ስላለባቸው አማና
   ➧ የሀገር አስተዳዳሪ ስላለበት አማና
   ➧ በየትኛውም ሙያ፤ እድሜ ሁኔታ ወዘተ ያለ ማንኛውም ሰው ስላለበት ሀላፊነት በዝርዝር ተዳሷል።
   ➹ ሌሎችም በሚገርም አቀራረብ ተካተዋል።

🎙 በተከበሩ ሸይኽ አቡ ዐብዱልሃሊም ዐብዱልሐሚድ ብን  ያሲን አል'ለተሚይ አሱኒይ አስሰ'ለፊይ አላህ ይጠብቃቸው

🏝 ይሄን ሁሉ ትንታኔ ያቀረቡት ሸይኹ በሂፍዛቸው ነው። በጣም ትልቅ ብቃት አላህ ሰጥቷቸዋል። በጣም አስገራሚ አሊም ናቸው።

▵▮▱▰▱▰▱▰▱▰▱▰▯▴
⚙ 📝 أَبُـــو عِـمْــرَان ❨𝕒𝕓𝕦 𝕚𝕞𝕣𝕒𝕟❩

🏝 ••⇣⇣.  🏖   ••⇣⇣ 
╰𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞.   ╰𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞

🖥️ በ 𝐓𝐞𝐥𝐞𝐠𝐫𝐚𝐦~𝐂𝐡𝐚𝐧𝐧𝐞𝐥
🏝 ⇣⇣⇣🍭⇣⇣⇣📲 ⇣⇣⇣↙️
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy
https://t.me/AbuImranAselefy

ሀሳብ  ካለዎ 
⤵️⤵️⤵️⤵️
https://t.me/AbuImranAselefybot


የሙሃመድ ስራጅ ተልቢስ


ባጠል ላይ ያለ ሰወሰ ብዙ ግዜ ነገሮችን በግልፅ አያብራራም፣በድፍኑ እየተናገረ ተከታዮችን ያደነዝዛል።ተከታዮችም አይጠይቁም።
ሰዎች ነገሮችን በድፍኑ ሚነገሩት ባንዱ ሲቲዛቸው በሌላው ለማምለጥ ነው።እንዲህ ምትሆነው ደሞ ባጢል ላይ ስትሆን ብቻ ነው፤ሀቅን የያዙ ሰዎች ንግግራቸው ሁሌም ግልፅ ነው፤አውቀው ምንም ኣይነት አሻሚ ንግግር አይናገሩም።

ወደ ሙሀመድ ስራጅ ስመለስ አንዲት ከደርስ የተቆረጠች ድምፅ ለቆ ነበር፤እሱም እንደ ጓደኛው ተልቢስ አድርጎ ወጥቶዋል።ድምፁ ላይ የሆነ ኪታብ ሚያስቀራ ይመስላል።

እንዲህ ይላል"የቢደኣ ባለ ቤቶችን አትቀላቀሏቸው አትቀማመጧቸው"ይላል
ኢሄ የኪታቡ ባለ ቤት ንግግር ነው።ከዛ እሱ እንዲህ ብሎ ተእሊቅ አደረገ"ጠይብ ኣንድ ኣንድ ኡለሞች ግን ኣንድ ኣንድ ስራዎችን በተመለከተ ከአህሉል ቢደዓ ጋር መተባበር እንደሚቻል ጠቅሰዋል"።

↪️ኢሄ የመጨረሻው ንግግር ኪታቡ ላይ ዬለም።እንጊዲህ ሙሃመድ ስራጅ በኪታቡ ባለቤት ላይ ረድ እያደረገ ነው ማለት ነው።የሰለፊይ ኡለሞች የፃፏቸውን ኪታቦች እንዲህ እያደረጉ ነው ሚበርዟቸው።ስለዚህ ኣንድ ሂዝቢይ የሰለፊያ ኡለሞች የፃፏቸውን የመንሃጅ ኪታብ ስላስቀራ ብቻ እንዳትሸወድ።አላማው ኪታቦቹን መበረዝ ነው።
ሌላው" ኣንድ ኣንድ ኡለሞች ፈቅደዋል" ያልከውን ብትጠቅሰው ጥሩ ነበረ፣እነዚህ ኡለሞች ኣንተ እንደምትለው ነው የፈቀዱት?
ሌሎች ኡለሞችስ ንግግራቸውን እንዴት ነው የተረዱት?

እነዚህ አሁን ያነሳሃቸው ነገሮች ለምንድነው በግልፅ ማታወራቸው?
እነዚህ "ተገደው የተባበሩ"ያልካቸው ሰዎች እነማን ናቸው?።ኣንተ ባትገልፃቸውም እኛ ግን እናቃቸዋልን፣የፈለከው ኢብን መስዑዶችን ነው።ሙሪዶችህ ባይጠይቁህም እኛ ግን እንጠይቅሃልን።
በመጀመሪያ እብን መስዑዶች ከቢደዓ ባለቤቶች ጋር ሲተባበሩ በምንድነው የተገደዱት?።ማነውስ ያስገደዳቸው?፤እስቲ ለተከታዮችህ አብራራላቸው።እነሱም እኮ ተገደን ነው ሲሉ አይሰሙም ኣንተ ኬት አምጥተህ ነው ኡዝር ምትደረድረው።

ሲቀጥል ኣንተ ፈቅደዋሉ ምትላቸው ኡለሞች ያስቀመጧቸውን ሸርጦችን አሟልተዋል?።

ለመተባበር እንደምሳሌነት የጠቀስከው ደሞ የሀጅን ጉዳይ ነው፣ኢሄ እውነት ለመናገር አህያ ያስቃል።ተከታዮችህንም ምን ያህል እንደምትንቃቸው ነው ሚያሳየው።
ቆይ ኢብን መስዑዶች ከሙብተዲዖች ጋር የተባበሩት በሀጅ ጉዳይ ነው?።
ኡለሞችስ ረድ ያረጉባቸው በሀጅ ጉዳይ ተባብራቹሃል ብለው ነው?።ለምንድነው ሰዎችን ኢሄን ያህል ምትንቁት?።እንደዚህ አይነት ድፍረትን ኬት ነው ምታመጡት።

ሱፊይ ሰለፊይ ሚባል ነገር ካሁን ቦሃላ ዬለም፣ሰለፊያን ቀብረናታል ብለው እጃቸውን ወደላይ አንስተው አጨብጭበው ፎቶ ተነስተው የመጡ ሰዎች ላይ እንዴት ትዋሽባቸዋልህ።እነሱ ራሱ ይታዘቡሃል እኮ።

ሌሎችም ጉዳዮች ኣሉ ብለሃል ብትጠቅሳቸው ጥሩ ነበር።
ደሞ" በልኩ ሊሆን ይገባል በልቁ መደበላለቁ አይቻልም"ትላልህ።
ለተከታዮችህ የቸገራቸው ግን ኢሄ አይደለም እነሱን የቸገራቸው የኢብን መስዑዶች መተባበር በልቁ ነው ወይስ አይደለም ሚለው ነው።ሚቻለው ነው ወይም ከማይቻለው ነው ብለህ ብታብራራላቸው የሰላም እንቅልፍ በተኙ ነበር።ኣንተ ግን ማሀል ሰፋሪ አድርገህ ነው የተውካቸው።

t.me/ibnawolllll
t.me/ibnawolllll


🔹 ሸይኽ ዐ/ሐሚድ መጅሊስ ገብቷል ተብሎ ለሚናፈሰው ውዥንብር ከራሳቸው የተሰጠ ምላሽ ።

https://t.me/bahruteka


[‏لا تجامل صاحبك إن كنت تحبه بحق]

قال العلامة زيد المدخلي رحمه الله:

" ليس من مقتضى الصحبة السكوت عن الخطأ الذي يقع من الصاحب والأخ.

بل عليه أن ينبه فوراً؛ وهذا هو الأخ الحقيقي، والصاحب الصادق في صحبته " .

عون الأحد الصمد ١/ ٢٧١.📒.


"‏يا مَن بِدُنياهُ اِشتَغَل، وَغَرّهُ طولُ الأَمَل
المَوتُ يَأتـي بَغتَـةً، والقبـرُ صندوقُ العَمَل"


👉 የጭቅጭቅ ርእስ አለማንሳት !!!

የአዲሶቹና የቀድሞ ኢኽዋኖችና እንዲሁም እንባ ጠባቂዎቻቸው የማስተኛ አዲስ ፋሽን በየመስጂዶቹና መድረሳዎች አጨቃጫቂ ርእሶች ማንሳት አያስፈልግም ሁሉም በጋራ ተስማምቶ ማስተማር አለበት የሚል ነው ። ‼
ይህ " መልከ ጥፉን በስም ይደግፉ " እንደሚሉት የነሲሓዎች ኢኽዋኖችና አሕባሾች እንዲሁም ሱፍዮችን ከእግዲህ ተስኒፍ ( እገሌ እንዲህ ነው ) ማለት የለም የሚለውን የባጢል ስምምነት መሬት ላይ ለማውረድና ስራ ላይ ለማዋል የሚጠቀሙበት ስልት ነው ።
ለመሆኑ አጨቃጫቂ ርእስ የሚባሉት ምንድናቸው ? አጨቃጫቂ ርእስ የሚባሉት ሽርክን በዝርዝር ማስተማር ፣ ቢዳዓን በዝርዝር ማስተማርና የመሳሰሉት ናቸው ። ይህ ማለት ሽርክን በጥቅሉ ቢዳዓም በጥቅሉ ማስተማር ይቻላል ማለት ነው ።
↪️ ሽርክን በጥቅል ማስተማር ማለት አንድ ኡስታዝ ወይም ሸይኽ

« ذَٰلِكَ وَمَن يُعَظِّمْ حُرُمَاتِ اللَّهِ فَهُوَ خَيْرٌ لَّهُ عِندَ رَبِّهِ ۗ وَأُحِلَّتْ لَكُمُ الْأَنْعَامُ إِلَّا مَا يُتْلَىٰ عَلَيْكُمْ ۖ فَاجْتَنِبُوا الرِّجْسَ مِنَ الْأَوْثَانِ وَاجْتَنِبُوا قَوْلَ الزُّورِ »

الحج ( 30 )

(ነገሩ) ይህ ነው ፡፡ የአላህንም ሕግጋት የሚያከብር ሰው እርሱ ጌታው ዘንድ ለእርሱ በጣም የተሻለ ነው ፡፡ የቤት እንስሳትም (ግመል ከብት በግና ፍየል) በናንተ ላይ (እርም መሆኑ) ከሚነበብላችሁ በስተቀር ለእናንተ ተፈቅዳላችኋለች ፡፡ ከጣዖታትም ርክሰት ተጠንቀቁ፡፡ ሐሰትንም ቃል ራቁ ፡፡ "

« حُنَفَاءَ لِلَّهِ غَيْرَ مُشْرِكِينَ بِهِ ۚ وَمَن يُشْرِكْ بِاللَّهِ فَكَأَنَّمَا خَرَّ مِنَ السَّمَاءِ فَتَخْطَفُهُ الطَّيْرُ أَوْ تَهْوِي بِهِ الرِّيحُ فِي مَكَانٍ سَحِيقٍ »

الحج (31 )

" ለአላህ ታዛዦች በእርሱ የማታገሩ ሆናችሁ (ከሐሰት ራቁ) ፡፡ በአላህም የሚያጋራ ሰው ፤ ከሰማይ እንደ ወደቀና በራሪ እንደምትነጥቀው ፣ ወይም ነፋስ እርሱን በሩቅ ስፍራ እንደምትጥለው ብጤ ነው ፡፡"

« إِنَّ اللَّهَ لَا يَغْفِرُ أَن يُشْرَكَ بِهِ وَيَغْفِرُ مَا دُونَ ذَٰلِكَ لِمَن يَشَاءُ ۚ وَمَن يُشْرِكْ بِاللَّهِ فَقَدِ افْتَرَىٰ إِثْمًا عَظِيمًا »
النساء ( 48 )

" አላህ በእርሱ ማጋራትን በፍጹም አይምርም፡፡ ከዚህ ሌላ ያለውንም (ኀጢአት) ለሚሻው ሰው ይምራል ፡፡ በአላህም የሚያጋራ ሰው ታላቅን ኀጢአት በእርግጥ ቀጠፈ ፡፡"

እነዚህና የመሳሰሉ አንቀፆችን ቀርቶ ሽርክን ማውገዝ ይችላል ። ነገር ግን መሬት ላይ ያሉትን የሽርክ ተግባራትን መዘርዘር አይቻልል ። ‼

ለምሳሌ : – ያብሬት ፣ የቃጥባሬ ፣ ያልከሶ ፣ የዳና ፣ የከረም ፣ የጀማ ኑጉስ ፣ የሸኸና ሑሰይን ፣ ያባድርንና የመሳሰሉትን የሙታን ቀብሮችን በዙሪያቸው ጠዋፋ ማድረግ ፣ የቀብራቸውን አፈር በጥብጦ መጠጣት ፣ እርዱኝ ፣ ድረሱልኝ ፣ እጄን ያዙኝ ፣ አክብሩኝ ፣ አሽሩኝ ፣ ጠብቁኝ ፣ ዘር ስጡኝ ማለትና የመሳሰሉት ተግባራትና ንግግሮች ከእስልምና የሚያወጡ ሽርኮች ናቸው ማለት አይፈቀድም ።
ምክንያቱም የጭቅጭቅ ርእስ ስለሆነኑ ‼ ሱብሓነላህ መቼ ነው ይህ ርእስ በሙስሊች መካከል የጭቅጭቅ ርእስ የሆነው ? ይህ ርእስ የጭቅጭቅ ርእስ የሚሆነው በሙስሊሞችና በሙሽሪኮች መካከል ነው ። ነገር ግን አዲሶቹ ኢኽዋኖችና እንባ ጠባቂዮቻቸው ከቀብር አምላኪ ሱፍይና አሕባሾች ጋር አንድ ነን ሲሉ የጭቅጭቅ ርእስ ሆነና በዚህ መልኩ ሽርክን በዝርዝር ማውገዝ አይቻልም ተባለ ። ‼

እንዲሁም ቢዳዓን የሚያወግዙ የተለያዩ የቁርኣን አንቀፆችን ለምሳሌ : —

« وَأَنَّ هَٰذَا صِرَاطِي مُسْتَقِيمًا فَاتَّبِعُوهُ ۖ وَلَا تَتَّبِعُوا السُّبُلَ فَتَفَرَّقَ بِكُمْ عَن سَبِيلِهِ ۚ ذَٰلِكُمْ وَصَّاكُم بِهِ لَعَلَّكُمْ تَتَّقُونَ »
الأنعام ( 153)

«ይህም ቀጥተኛ ሲኾን መንገዴ ነው፤ ተከተሉትም፡፡ (የጥመት) መንገዶችንም አትከተሉ፡፡ ከ(ቀጥተኛው) መንገዱ እናንተን ይለያዩዋችኋልና፡፡እነሆ ትጠነቀቁ ዘንድ በርሱ አዘዛችሁ፡፡»

« إِنَّ الَّذِينَ فَرَّقُوا دِينَهُمْ وَكَانُوا شِيَعًا لَّسْتَ مِنْهُمْ فِي شَيْءٍ ۚ إِنَّمَا أَمْرُهُمْ إِلَى اللَّهِ ثُمَّ يُنَبِّئُهُم بِمَا كَانُوا يَفْعَلُونَ »
الأنعام ( 159 )

" እነዚያ ሃይማኖታቸውን የለያዩ አሕዛብም የኾኑ በምንም ከእነሱ አይደለህም ፡፡ ነገራቸው ወደ አላህ ብቻ ነው ፡፡ ከዚያም ይሠሩት የነበሩትን ሁሉ ይነገራቸዋል ፡፡

የሚሉና ሌሎችም የተለያዩ የሐዲስ መረጃዎችን በጥቅሉ እየጠቀሰ ቢዳዓን ማውገዝ ይችላል ። ነገር ግን በናኢዮች ፣ ቁጥቢዮች ፣ ሱሩርዮች ፣ ሙመዪዓዎች ፣ ሱፍዮች ፣ ተብሊጞች ፣ አሕባሾች እያለ በዝርዝር የቢዳዓ አራማጆችን መጥቀስ አይችልም ። ‼ ምክንያቱም የጭቅጭቅ ርእስ ስለሆነ ።
እንዲሁም ቁርኣንን ፣ ሐዲስንና የቀደምት የኢስላም ሊቃውንቶች ( ሰለፎች) በአንድ ድምፅ ያፀደቋቸውን መርሆችን የጣሱ የቢዳዓ ባልተቤቶችን በስም እየጠቀሱ ማስጠንቀቅ አይቻልም ።
ለምሳሌ : – የሀገራችን የቀድሞ የኢኽዋን መሪዮችን እንደ ዶ/ር ጀይላን ፣ ሙሐመድ ሓሚዲን ፣ ሓሚድ ሙሳ ፣ ካሚል ሸምሱ ፣ አቡበከር አሕመድ ፣ አሕመዲን ጀበል ፣ ራያ አባመንጫ ፣ በድሩ ሑሴንና የመሳሰሉት
የአዲሶቹ ኢኽዋን መሪዮች እንደ :– ኢልያስ አሕመድ ፣ ሳሊሕ አሕመድ ፣ አዩብ ደርባቸው ፣ ኢልያስ አወልና ቡሽራ የመሳሰሉት
የእነርሱ እንባ ጠባቂ የሆኑት እንደ ኢብኑ ሙነወርና ግብረአበሮቹ ስም አንስቶ ማስጠንቀቅ አይፈቀድም ። ምክንያቱ ደግሞ የጭቅጭቅ ርእስ ስለሆነ ።
የዚህ ተልቢስ ሽፋኑ አጨቃጫቂ ርእሶችን አለማንሳት የሚል ሲሆን በሰፊው ዘመቻ እየተደረገበት ይገኛል ። ከላይ እንዳልኩት በዚህ ሽፋን በተለይ ዩንቨርሲቲ አካባቢ ለየት ያለ ትኩረት ሰጥተውት እየሰሩበት ሲሆን አብዛኛው ጠንካራ ሰለፍይ የነበሩ ወጣቶች በዚህ ምክንያት ከአቋማቸው እንዲወርዱ ተደርጓል ።
ልክ እንደዚሁ ጠንካራ አቋም የነበራቸው ሰለፍይ ወጣቶች የነበሩባቸው መስጂዶችም ከምንም አይነት እንቅስቃሴ እንዲቋረጡ ተደርገው ከቆዩ በኋላ ሰለፍዮች የሚወነጀሉባቸው ለሙብተዲዖች ጥብቅና የሚቆምባቸው ቦታዎች ተደርገዋል ።
በመሆኑም በምንም መልኩ ሰለፍዮች የትም ቦታ የጭቅጭቅ ርእስ አለማንሳት የሚል ማስተኛ እንዳይቀበሉ መጠንቀቅና ተመዩዝ ማድረግ ይኖርባቸዋል ።
አላህ ተውሒድና ሱናን ባለቤቶቹንም የበላይ አድርጎ እንዲሁም ሽርክና ቢዳዐን ባለቤቶቹንም የበታች ያድርግልን ።

https://t.me/bahruteka


እኛም እንጠይቅ፣ ከቢድዐህ ባለ ቤቶች ጋር ልዩነታችሁ ምንድነው??!!

————— ልብ ያለው ልብ ይበል!!
የሙነወር ልጅ ሆይ!፣ ሳዳት ከማል፣ ኸድር ከሚሴ፣ ሙሀመድ ሲራጅ… ያቺ በባጢል ባለ ቤቶች ላይ ብርቱ የነበረችውን አንደበታችሁን ምን ለጎማት? ከዚህ ቀደም ከ4/5 አመታት በፊት በቢድዐህ ባለ ቤቶች ላይ ከሰልላ ሰይፍ የበለጠ የቢድዐህ ባለ ቤቶችን ወገብ የሚበጥስ የነበረው ብዕራችሁን አሁን ላይ ለቢድዐህ ባለ ቤቶች ጊዜ ምን አደለዶመው??
ይሀው "ነጭ ነጩን እንናገራለን" ስትሉባቸው የነበሩት የመርከዙ አመራሮች ትላንት ኢኽዋን ሲሏቸው ከነበሩት ከነ ሙሀመድ ሃሚዲን ከነ ጀይላንና… መሰል ከሌሎችም የመጅሊሱ ሰዎች መደመራቸውን እናንተ ዑዝር ብትደረድሩላቸውም "ካፈርኩ አይመልሰኝ" ብለው በግልፅ በአደባባይ እያሳዩዋችሁ ነው። ታዲያ የናንተ ዝምታ እስከ መቼ ነው? ወይስ እናንተም ሳዳት ከማል የመጅሊሱን ሰዎች "በእድሜ የጠገቡ ናቸው፣ ልጅና ጅል አይደሉም" ብሎ ማወዳደስ እንደጀመረው በሂደት መደመራችሁን ለቴፎዞዋችሁ ግልፅ እስክታደርጉ ነው የጠበቃችሁት?? ከእነዚህ የመርከዝ ኢብኑ መስዑድ ሰዎችና ከቢድዐህ ባለ ቤቶች ጋር ያላችሁ ልዩነት ምንድነው? ለቲፎዞዎቻችሁ መደመራችሁን በአደባባይ ግልፅ ማድረግ የቀራችሁ ቢሆን እንጂ ምን ልዩነት አላችሁ? በቢድዐህ ባለ ቤቶች ላይ የተለጎመው አንደበታችሁና የደሎደመው ብዕራችሁ በሰለፊይ መሻይኾችና በሰለፊይ ወንድሞች ላይ በርትቷል!! ሰለፊይ መሻይኾችን "የረድ ጉረኛ፣ በእንጨት የበቀለ ሽበት…" መሰል ቃላቶችን ተጠቅማችሁ እየወረፋችሁና ረድን እያጣጣላችሁ የመጅሊስ ሰዎችን "እድሜ የጠገቡ…" ምናምን እያላችሁ ታወድሳላችሁ!! ታዲያ ምኑ ጋ ነው ልዩነታችሁ?!
ይልቅ እናንተም ለቲፎዞዎቻችሁ መደመራችሁን ቶሎ ግልፅ አድርጋችሁ ገላግሏቸው። በእርግጥ በርካታ እህትና ወንድሞች ነቅተው በጊዜ ቢርቋችሁም አንዳንድ በእናንተ ጭፍን ተከታይነት የሚሰቃዩ አሉና በቃችሁ አትሰቃዩ እኛም ከነዛ ሰዎች ልዩነት የለንም ብላችሁ ገላግሏቸው!!

የጀርህና ተዕዲል ባንድራ ተሸካሚና በሂዝቢዮች ላይ ጥልቅ እውቀት ያላቸው ታላቁ ዓሊም ሸይኽ ዶ/ር ረቢዕ ቢን ሓዲ'ል መድኸሊይ (ሀፊዘሁላህ) በቢድዐህ ባለ ቤቶች ላይ ምላሽ ከመስጠት የተለጎሙ ሰዎችን እንዲህ ሲሉ ይጠይቃሉ:-

ቢድዓንና የጥመት ባለ ቤቶችን የማትዋጋና በስሜት ባለ ቤቶች ላይ ምላሽ የማትሰጥ ከሆንክ በአንተና በነዚያ መካከል ያለው ልዩነት ምንድነው?!፣ በእነሱና በአንተ መካከል ያለው ልዩነት ምንድነው? በጥፋታቸው ላይ እየተመለከትካቸው ዝም የምትል ከሆነ አንተ የጥመት ባለ ቤቶችን ቁጥር እያበዛህ ነው ማለት ነው። በምድር ላይ ብልሽትን እያዳረሱ እየተመለከትክ ዝም የምትል ከሆነ አንተ እነሱን እያገዝካቸውና እያጀገንካቸው ነው። ሌባ ወደ ሰዎች ግቢ ሊገባ ሲዘል አይተህ ማሻአላህ ዝም ትላለህ? ይሄ ምን ማለት ነው? ይህ ነው እንዴ በመልካም ማዘዝ ከመጥፎ መከልከል?

ወደ ቢድዐህ ተጣሪዎች ከሌባና መንገድ ከሚቆርጡ ሽፍቶች የበለጠ ሸረኛ ናቸው። ኢብኑ አቢ ዘይድና ኢብኑ ዐብዱልበር እንዲህ ብለዋል:- "እነሱ እኮ መንገድ ከሚቆርጡ ሙጅሪም የሆኑ ሽፍቶች የበለጠ ሸረኞች ናቸውና ከእነሱ ሁልጊዜም ማስጠንቀቅ ግዴታ ይሆናል። ሰዎች እስከሚጠነቀቋቸው ድረስ እነሱን ማጋለጥ፣ገመናቸውን ማውጣትና ሰዎች ፊት እርቃናቸውን ማስቀረት ግዴታ ነው።"

ለዚህም ነው የደጋግ ቀደምቶች ኪታቦች የቢድዐህ ባለ ቤቶችን በመቃረን ቢድዓቸውን (በማፍረስ)፣ ከእነሱ በማስጠንቀቅና ከመቀማመጥ… መሰል ነገሮች በማስጠንቀቅ የተሞላ ሆኖ ታገኘዋለህ። ብዙ ሙስሊሞች በቢድዐህ ባለ ቤቶች ጥመት አልጠፉም ምክንያቱ ይህን "በቢድዐህ ባለ ቤቶች ላይ ምላሽ የመስጠትና የማስጠንቀቅን" መሰረት በመተዋቸው ቢሆን እንጂ።
ለዚያም ነው በሙስሊሙ ማህበረሰብ ላይ ጥመት የተሰባሰበበት። ከጥመታቸው ነጃ የሚወጣ የለም ጥቂት ብልሃትም ሆነ አቅም የሌላቸው ሚስኪኖች ቢሆኑ እንጂ። እነዚያ ረድ ረድ… እያሉ ረድን የሚያጣጥሉ ሰዎች ጠማሞች ናቸው። ውዳቂ ተግባራቸውን ነው የሚያሰራጩት፣ አንድም ሰው ምላሽ እንዲሰጥባቸው አይፈልጉም። ተገንዘቡ አላማቸው ይህ ነው። ለዚያም ነው በተሳሳተ ሰው ላይ ረድ ማድረግን (ምላሽ መስጠትን) የረድ ኪታቦች ልብ ያደርቃሉ… መሰል ቃላትን በመጠቀም የሚያጠለሹት። ይህ ማለት እንግዲህ ግሳንግሱ ተግባራቸውና ቢድዓቸው ልብ ያረጥባል እያሉ ነው ማለት ነው። ከተንኮላቸውና ከሴራቸው ቢድዓንና ጥመትን ያሰራጫሉ። አህሉሱንናዎችንና መንገዳቸውን በተቀማመጡበት፣ በሙሃዶራቸውና በመፅሃፎቻቸው… በሁሉም ነገራቸው ይዋጋሉ። ከመሆኑም ጋር ግን በቢድዐህ ሰዎች ላይ ሲሆን ምላሽ አትስጥ ምላሽ መስጠት ልብ ያደርቃል ይላሉ። ሐቅንና የሐቅ ባለ ቤቶችን መተቸት ግን እነሱ ዘንድ ማሻአላህ ችግር የለውም¡¡። ሐቅንና ባለ ቤቱን መዋጋትም ማሻአላህ እነሱ ዘንድ ልብ ያረጥባል¡¡።”
[አል መጅሙዕ 14/280]
ይሄው ነው ተጨባጩ!። ቅንና ሚዛናዊ ልቦና ያለው ሰው ከጭፍን ተከታይነት ወጥቶ ይመከርበት!!
✍🏻ኢብን ሽፋ (t.me/ibnshifa)
የተለያዩ ት/ቶችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችን ⤵️ #join በማድረግ ይቀላቀሉ
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa


ላታመልጪኝ አታሩጪኝ፣ የሚባል ነገር አለ
———ለአልከሶ ወንድሞች…
ለማንኛውም የሱንና ሰዎች ድል እየፈጠነ ነው። አምላካችን አላህ ከጭንቅ ከመከራ በኋላ ድል እንዳለ በቁርኣኑ ተናግሯል። ይህ ለሀቅ ተከታዮች የተገባ ቃል ነው። የባጢል ሰዎች ግን በተቃራኒው ሲጨነቁ ተስፋቸው ይመነምናል!፣ የሙመይዓና የሱሩሪዮች በዲን ስም የደበቁት የፖለቲካ ጥማት አደባባይ እየወጣ እነሱ የደበቁት ሐቅ በሱንና ሰዎች አንደበት ሲገለጥ የጭንቀታቸውን ውሃ እየጨበጡ ነው። ምን ዋጋ አለው? ውሃ እየወሰደ ውሃ ቢጨበጥ አያድን!፣ ሐቁ ግልፅ እየወጣ ህዝብ እየከዳቸው ነው!፣ ወጣቱን እንዳለ አጣን እያሉ ነው። ምክንያቱም እነሱ የሚያምኑት በብዛት ነው እንጂ በማስረጃ በሀቅ ሀይል አይደለም። ኢንሻአላህ የባጢል አንድነታቸውም ይፈራርሳል። የትም አታመልጡም! ሰለፊዮች ከባለ ስልጣን ጋር ጥገኝነት ባይኖራቸውም የፈለገውን ከፍ ያልፈለገውን ዝቅ የሚያደርገው ስልጣን ሁሉ በእጁ የሆነው የዓለም አስተናባሪው አምላካቸው አላህ አላቸው!!። ከእርሱ ጋር ጦርነቱን ከቻላችሁ የምናየው ይሆናል። ግን በየትኛውም ዘመን ከእናንተ በላይ ግፈኞችና ጥጋብ ያሰከራቸው አንባገነኖችን እንዳላዋጣቸው ታሪክ ይመስክር!!

ውድ ሠለፊዮች ሆይ! እድለኞች ናችሁ! ለሰለፊያ መንሀጅ ለሐቁ መንገድ ለተውሒድ ለሱንና አንድ ብላችሁ ዋጋ መክፈል ጀምራችኋልና አላህ ኢኽላሱንም ፅናቱንም ይስጣችሁ!! በሀቅ መንገድ ላይ ለሚደረግ ትግል ኢኽላስና ፅናት ወሳኝ ናቸው!!። ሶስትና አራት ሆናችሁ እንኳን ብትቀሩ በፅናት ታገሉ! ጉዳዩ የብዛት አይደለም! ፀንታችሁ ሀቁን አብራሩ! ተከባበሩ አንድነት ይኖራችሁ!።

የወራቤ ወንድሞች በምትችሉት ሁሉ ከጎናቸው ሁኑ!! ቁስላቸው የእናንተም ቁስል ነው!! የህግ ባለ ሞያዎች እንዳላችሁ አውቃለሁ የምትችሉትን ሁሉ ሰበብ ሳትተኙ ሌት ከቀን አድርሱ!! ጠላት አይተኛም እናንተ እንዴት ትተኛላችሁ?! እየተወያያችሁ ጥበብ የተሞላበትን አካሄድ ተጠቀሙ!! አላህ ይጠብቃችሁ!! ስኬታችሁን ያሳየን!!

በመጨረሻም ድል ለሙተቆች ለሐቅ ሰዎች ነው!!

የተለያዩ ት/ቶችን ለማግኘት የቴሌግራም 👇👇 ቻናላችን #join በማድረግ ይቀላቀሉ
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa

Показано 20 последних публикаций.