🗣 ወቅታዊ_መረጃ 🇪🇹


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


This is national and international News and advertising channel
🇪🇹🇪🇹🇪🇹"ስለኢትዮጲያ ሳትሰማ ያሳለፍከው ቀን እንደባከነ ይቆጠራል" 🇪🇹🇪🇹🇪🇹
⏭▶️➡️ ሀገራዊና አለም አቀፋዊ ዜናዎችን በፍጥነት ይደርሶታል።🔚

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций



10.7k 0 19 18 151

ያሳዝናል‼ ገላን ኮንዶሚኒየም ተገድለው ተገኙ።

ሲሉ ቤተሰቦቻቸው አፋልጉኝ ሲያስነግሩ ነበር።

በሚያሳዝን ሁኔታ እኝህ አባት አቶ ከበደ በለው ገላን ኮንዶሚኒየም ተገድለው መገኘታቸው ተሰምቷል።ቤተሰቦቻቸው ከምንሊክ ሆስፒታል አስክሬን ተቀብለን ነገ 6 ሰአት ሳሪስ ዮሴፍ ስርዓተ ቀብራቸው ይፈፀማል በማለት መናገራቸውን የሾፌሮች አንደበት አስነብቧል።

መኪናውም እንደጠፋ ነው።ኢትዮጵያ ሰዎች በጠራራ ፀሐይ የሚታፈኑባትና የሚገደሉባት እየሆነች ነው።ፍትህ ብሎ መጠየቅ ፌዝ ይሆንብናል። መንግስት አሽከርካሪዎች ላይ የሚደርስን መታፈንና ግድያ እንዲቆም ኃላፊነቱን መወጣት አለበት።ለአቶ ከበደ በለው ቤተሰቦች መፅናናቱን ይስጥልን።

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማየት የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!👇
https://t.me/wektawi1mereja


ሰሞኑን በቋሪት ወረዳ በተደረገው ውጊያ
እስከ መቼ…?

"…እንዴት ነው የሰዉ ሞት እንደዚህ የረከሰው…? እርስ በራስ እየተበላላን፣ እየበጣጠሰው ደሙን እያፈሰሰ፣  የሚኖረውስ እስከመቼ ድረስ ነው?   ይሄ ሁላ ግፍ ሲፈጸም እንዲህ ዝም፣ ጭጭ ብለው የሚቀመጡት ዝምታቸው እስከመቼ ነው…?

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማየት የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!👇
https://t.me/wektawi1mereja




አቶ ደመቀ መኮንን ከብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳትነት ለቀቁ‼️

አቶ ደመቀ መኮንን ከብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳትነት መልቀቃቸውን ፓርቲው አስታወቀ።የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

የብልጽግና ማዕከላዊ ኮሚቴ የፓርቲውን የአመራር የመተካካት መርህንና የአሰራር ስርዓት በመከተል ዛሬ ባካሄደው ማጠቃለያ ስብሰባ በሙሉ ድምፅ አቶ ደመቀ መኮንን መሸኘቱን አስታውቋል።

በምትካቸውም የፓርቲው ስራ አስፈጻሚ የነበሩትን አቶ ተመስጌን ጥሩነህን ምክትል ፕሬዝዳንት አድርጎ በአብላጫ ድምጽ መርጧል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማየት የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!👇
https://t.me/wektawi1mereja




#Update

ራስ ገዟ ሶማሊላንድ የሶማሊያ መንግሥትን አስጠነቀቀች።

ከኢትዮጵያ ጋር የተፈረመውን የመግባቢያ ስምምነት ለማደናቀፍም ይሁን ለመቃረን የሚሞክር ማንኛውም ግለሰብ ይሁን አካል ላይ እርምጃ ወስዳለሁ ብላለች።

የራስ ገዟ ሶማሌላንድ" የሚኒስትሮች ምክር ቤት " ዛሬ አስቸኳይ ስብሰባ አድርጎ ነበር።

ከስብሰባው በኃላ ባወጣው ባለ 8 ነጥብ የአቋም መግለጫ ፦

- ምክር ቤቱ እ.ኤ.አ. ጥር 1/2024 በአዲስ አበባ የተፈርመውን የመግባቢያ ስምምነት በሙሉ ድጋፍ አፅድቆ እንደተቀበለውና እንደሚያደንቅ ገልጿል።

- ምክር ቤቱ ኢትዮጵያ " ለሶማሌላንድ ሪፐብሊክ " ሉዓላዊነት እውቅና የሰጠች የመጀመሪያ ሀገር በመሆኗ ምስጋናውን አቅርቧል።

NB. (የኢትዮጵያ መንግሥት ባወጣው መግለጫ ፤ ስምምነቱ በሂደት ሶማሌላንድ ዕውቅና ለማግኘት የምታደርገውን ጥረት በተመለከተ የኢትዮጵያ መንግስት በጥልቀት አጢኖ አቋም እንደሚወስድበት መግለፁ ይታወቃል)

- ምክር ቤቱ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ  ሶማሌላንድ ምድሯን፣ አየሯን እና ባህሯን ሙሉ በሙሉ የምትቆጣጠር ነፃ ሀገር ናት ብሏል። በተጨማሪም " በሶማሌላንድ ሪፐብሊክ " ሕገ መንግሥት መሠረት " የሶማሌላንድ ሪፐብሊክ " ከማንኛውም ብሔራዊ ጥቅሟን ከሚያስጠብቅና ከሚጣጣም አካል ጋር ስምምነት የማድረግ ሥልጣን አላት ብሏል።

- ምክር ቤቱ ፤ " በሶማሌላንድ ሪፐብሊክ " እና በኢትዮጵያ ፌደራላዊ መንግስት መካከል የተደረገውን የመግባቢያ ስምምነት አስመልክቶ የሶማሊያ መንግስት የሰጠውን መግለጫ እና ድርጊት በጽኑ አውግዟል። የሶማሊያ መንግስት በመሰል ጉዳዮች ከመሳተፍ እንዲቆጠብ አስጠንቅቋል።

- ምክር ቤቱ  ከሶማሊያ የወጡት መግለጫዎች " በሶማሌላንድ ሪፐብሊክ " እና በሶማሊያ መንግስት መካከል ከዚህ ቀደም የተደረጉ ስምምነቶችን የሚጻረር መሆኑን ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ይወቅልኝ ብሏል።

- ምክር ቤቱ ፤ " በሶማሌላንድ ሪፐብሊክ " እና በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ሪፐብሊክ መንግስታት መካከል የተፈረመውን የመግባቢያ ስምምነት ለማደናቀፍ ወይም ለመቃወም ለሚሞክር ማንኛውም ግለሰብ ወይም አካል ላይ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወስድ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል።

- ምክር ቤቱ የሶማሌላንድ ህዝብ  ለተፈረመው የመግባቢያ ሰነድ ላደረገው ደማቅ አቀባበል እና ድጋፍ ያለውን አድናቆት ገልጿል።

- ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክን አርአያነት በመከተል በዓለም ዙሪያ ያሉ መንግስታት " ለሶማሌላንድ ሪፐብሊክ " እውቅና ለመስጠት ድፍረት እና ጥበብ እንዲያሳዩ አሳስቧል። ይህን መሰሉ ዕውቅና ለአህጉራዊ መረጋጋት፣ ለደህንነት እና ለአፍሪካ ቀንድ የዴሞክራሲ መርሆች መሻሻል አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ አጽንኦት ሰጥቷል።

ℹ ሶማሊላንድ ላለፉት ሶስት አስርት ዓመታት እራሷን እንደ አንድ ነፃ ሀገር የምትቆጥር ሲሆን የራሷ ህገመንግስት፣ የመገበያያ ገንዘብ፣ የፀጥታ ኃይል፣ ራሱን የቻለ የፖለቲካ ስርዓት አላት። እስከዛሬ ግን ዓለም አቀፍ እውቅና ማግኘት አልቻለም። ሶማሊያ እንደ አንድ የራሷ ግዛት ነው የምታያት።
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማየት የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!👇
https://t.me/wektawi1mereja




ሰበር
ሶማሊያ በኢትዮጵያ የሾመችውን  አምባሳደሯን ከኢትዮጵያ ጠራች።

ማንም ሀይል የሶማሊያን ሉአላዊነት መድፈር የለበትም የሚል ውሳኔ የሚንስትሮች ምክርቤት ወስኗል።

የሶማሊያና የኢትዮጵያ ግኑኝነት ወዳልተፈለገ መቋሰል የሚያመራ ይመስላል።

ሶማሊያ፣ ሶማሊላንድ ግዛቴ ናት ብላ ነው የምታምነው። ልክ ቻይና በታይዋን ላይ እንዳላት አይነት።

ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር ያደረገችው ስምምነት ውስጥ እንደ ሀገር "እውቅና" መስጠቷ ብስጭት ፈጥሯል።

2024

አዲስ ውዝግብ በአፍሪካ ቀንድ አከባቢ ሊከሰት ይመስላል።

ያሳዝናል 😢


ኢትዮጵያ የወደብ ባለቤት ሆነች‼️

ኢትዮጵያ የቀይ ባሕር በር ለማግኘት እና ለማልማት የሚያስችላትን ስምምነት ከሶማሊ ላንድ ጋር ፈፅማለች።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማሊ ላንድ ፕሬዚዳንት ሙሴ ባሂ ሁሉን አካታች የሆነውን የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል።

በዚሁ መሠረት ለብዙ ዘመናት ወደብ አልባ ሆና የቆየችው ሀገራችን ከሶማሊ ላንድ ጋር ባደረገችው ስምምነት በሊዝ የወደብ ባለቤት መሆን ችላለች።

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማየት የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!👇
https://t.me/wektawi1mereja


አዲስ አበባ


ከመጪው የመስቀል በዓል ጋር ተያይዞ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ቲሸርት ታስትማላችሁ፣ግጭት ቀስቃሽ ፅሁፎች ታዘጋጃላችሁ በሚል ህትመት ቤቶች ከፍተኛ ቁጥጥር እየደረገባቸው መሆኑን ከህትመት ቤት ሃላፊዎች የደረሰኝ መረጃ ይጠቁማል። ሽሮሜዳ አካባቢ አንድ በህትመት ስራ ላይ የተሰማሩ የህትመት ባለሙያ እንደገለፁልኝ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ያለው ቲሸርት በህትመት ቤቴ በመገኘቱ  አሽግተውታል ብሏል(አዩዘሀበሻ)።
👉መረጃ ለሚፈልጉ ብቻ ከስር ባለው ሊንክ ለሌሎች በመጋበዝ መረጃ በቀላሉ እንዲያገኙ ያድርጉ(ከአክብሮት ጋር)"መረጃ ህይወት ነው"
በርካታ ሀሰተኛ አካውንቶች ስላሉ ትክክለኛው ሊንክ👇👇

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማየት የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!👇
https://t.me/wektawi1mereja


ኢሰመጉ ፤ በአዲስ አበባ በህገወጥ የሚታሰሩ ሰዎችን የመንግሥት ትምህርት ቤቶች በማቆያነት ያገለግላሉ መባሉን ለማረጋገጥ የሚመለከታቸውን አካላት ብጠይቅም ምላሽ አልሰጡኝም አለ

👉🏼 በአዲስአበባ ሕጋዊ ሥርዓትን ያልተከተሉ የጅምላ እስሮች አሁንም ቀጥለዋል ብሏል

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) በአዲስ አበባ ከተማ እና በአማራ ክልል በንጹሀን ላይ እየተፈጸሙ ያሉ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ተባብሰዋል ሲል በትናንትናዉ እለት ባወጣዉ መግለጫ አሳዉቋል።

ኢሰመጉ በአዲስ አበባ ከተማ ሕጋዊ ሥርዓትን ያልተከተሉ እና አንዳንዶቹም አስገድዶ የመሰወር ባህርይ ያላቸው የጅምላ እስሮች መፈፀም መቀጠላቸውንም ተናግሯል። የሚታሰሩ ሰዎችም በተገቢው ጊዜ ፍርድ ቤት እንደማይቀርቡ ፣ የታሰሩ ሰዎች የት እንዳሉ በቤተሰቦቻቸው እንደማይታወቅ አረጋግጫለሁ ብሏል።

ለእነዚህ እስሮች በከተማዋ የሚገኙ የመንግሥት ትምህርት ቤቶች እንደማቆያነት እንደሚያገለግሉ የደረሳቸውን መረጃ ለማረጋገጥም አዲስ አበባ ትምህርት ቢሮን ፣ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽንን ፣ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንን በደብዳቤ ቢጠይቅም ሪፖርቱን እስካወጣበት መስከረም 12/ 2016 ዓ.ም. ድረስ ምላሽ አለማግኘቱን ዳጉ ጆርናል ከመግለጫው ተመልክቷል።

በተጨማሪም አንዳንድ የእስረኞች ማቆያዎች ለዚህ ተግባር ያልተቋቋሙ እና በንጽሕና ያልተያዙ በመሆናቸው ታሳሪዎች ለከፍተኛ የጤና ቀውስ መዳረጋቸውንም ኢሰመጉ በሪፖርቱ ገልጿል።

በተመሳሳይ በአማራ ክልል የተፈጠረውን ግጭት ተከትሎ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከታወጀ በኋላም ጋዜጠኞችንና ያለመከሰስ መብት ያላቸውን የምክር ቤት አባላት ጨምሮ መጠነ ሰፊ የጅምላ እስሮች መፈፀማቸውን አስታውሶ፣ የሚመለከታቸው አካላት እነዚህን ከሕግ አግባብ ውጭ የተፈፀሙ እስሮች ለማስቆም እርምጃ ባለመውሰዳቸው አሁንም የጅምላ እስሮች ቀጥለዋል ሲል በመግለጫው ጠቅሷል። ከታሳሪ ቤተሰቦች አገኘኋቸው ባላቸው መረጃዎች በመዲናዋ በርካታ ሰዎች ያለአግባብ እንደታሰሩም አሳዉቋል።

https://t.me/wektawi1mereja


‹‹ በቅፅል ስሙ ልጅ ያሬድ በሚል የሚታወቀው ያሬድ ዘላለም ላይ የማድረገውን ምርመራ አጠናክሬ እቀጥላለሁ ›› - ፌደራል ፖሊስ

የፌደራል ፖሊስ የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ ጄይላን አብዲ ‹‹ በመታወቂያ ስሙ ያሬድ ዘላለም በቅፅል ስሙ ደግሞ ልጅ ያሬድ በሚል የሚታወቀው ግለሰብ ላይ የማድረገውን ምርመራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ›› ለአሻም ነግረዋታል፡፡ከሰሞኑ ‹‹ ልጅ ያሬድ ›› በሚል ቅፅል ስም የሚጠራዉ የቀድሞ ኮሜዲያን ያሬድ ዘላለም  በተረጋገጥ የፌስቡክ ገፁ ‹‹ የአንድ ትልቅ የእምነት ተቋምን ክብር በሚያጎድፍ መልኩ ባስተላለፈዉ ጸያፍና ማንንም ብሄር በማይወክል መልዕክት ምክንያት የፌደራል ፖሊስ ነሐሴ 26 ቀን 2015 ዓ.ም በቁጥጥር ስር እንዳዋለው ›› የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊው ተናግረዋል፡፡

‹‹ ግለሰቡ ተሰውሯራል፣ጠፍቷል እያሉ ያልተጣራና ትክክለኛ ያልሆነ መረጃ የሚነዙና ኅብረተሰቡ ላይ ዉዥንብር የሚነዙ ›› ያሏቸው ‹‹ አካላት ከድርጊታቸዉ እንዲቆጠቡም ›› አሳስበዋል፡፡

ጄይላን ሲቀጥሉ ‹‹ ይህን ከኢትጵያዊነት ያፈነገጠ ተግባር የፈጸመዉ ልጅ ያሬድ( ያሬድ ዘላለም) የተባለ ግለሰብ ከ3ቀናት በፊት የፌደራል ፖሊስ በቁጥጥሩ ስር አውሎት እንደሚገኝ ›› ጠቅሰው ‹‹ ህብረተሰቡ ግንዛቤ እንዲኖረው እንወዳለን ›› ሲሉ አክለዋል፡፡

‹‹ ግለሰቡ በማህበራዊ ሚዲያ ወጥቶ የአንድ ብሄር ተወካይ በሚመስል መልኩ ያስተላለፈው ግብረገብነት የጎደለው፣ የተወደደና የተከበረ የእምነት ተቋም ላይ ያስተላለፈው ጸያፍ ቃላቶች ታላቁን የኦሮሞ ህዝብም ሆነ የአማራን ህዝብ የሚወክል አይደልም ›› ሲሉም ነቅፈዋል፡፡

‹‹ ማንም ደግሞ ለዚህ ግለሰብ የሠጠዉ የእምነትም ሆነ የብሔር ውክልና የለም ›› በማለት  ፌደራል ፖሊስ የጀመረውን ምርመራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቁዋል፡፡

‹‹ ሌሎችም ከእንዲህ ዓይነት ከኢትጵያዊነት ከወረደና የእምነት ተቋማትን በመሳደብ ህዝብን ለቁጣ የምታነሳሱና፣ አንድን ብሄረሰብ ከሌላዉ ለማጋጨት በተለያየ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች የምትቀሳቀሱ ከድርጊታቸዉ እንዲታቀቡ ›› አሳስበዋል፡፡

በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ‹‹ ልጅ ያሬድ የተባለውን ግለሰብ እና ተባባሪዎቹ ላይ ክስ እንዲመሠረት የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ቢሮን ›› ጠይቃለች፡፡

‹‹ በግለሰቡ እና ተባባሪዎቹ ድፍረት የተሞላበት  ድርጊት በርካታ ኦርቶዶክሳዊያንም ኢትዮጵያውያንም ላይ ከፍተኛ ቁጣን በመቀስቀሱን እና  ከፍትህ አደባባይ ፍርድን ስለሚጠብቁ ፖሊስን ለማገዝ ይሔን አቤቱታ አቅርቤያለሁ ›› ብላለች።

ቤተ ክርስቲያኗ አክላም ‹‹ የተከሳሹ ድርጊት በዋናነት የቤተ ክርስቲያኗን መልካም ስም የሚያጎድፍ ድርጊት፤ ለቤተ ክርስቲያን ያለውን ጥላቻ በመግለጽ ሰዎችን ለአመጽ እና ብጥብጥ የሚያነሳሳ፤ የቤተክርስቲያንን የአምልኮ ቦታ ያራከሰ ፤ የምዕመናኑን ስሜት የሚነካ በመሆኑ ፣ በሚያዋርድ እና ቤተክርስቲያንን በሚያናንቅ መልኩ የተፈጸመ በመሆኑ በግለሰቡ እና  በተባባሪዎቹም ላይ ጭምር ፖሊስ ተገቢውን ምርመራ በማድረግ ክስ እንዲመሠርት ለአቃቤ ሕግም እንዲልክ ›› ጠይቃለች።

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማየት የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!👇
https://t.me/wektawi1mereja


የአቡሽ ዘለቀ አልበም በአዲስ አበባ እንደይሸጥ መከልከሉን አርቲስቱ በማህበራዊ ሚዲያ ገፁ አሳወቀ።

የሚከተለው የአቡሽ ዘለቀ መልዕክት ነው 👇

"ሰላም ሰላም እንዴት ናችሁ! በትናትናው እለት እንደ አባቴ እወድሻለሁ የተሰኜው አዲሱ አልበሜ በአዲስ አበባ እንዳይሸጥ በፖሊስ ተከልክሏል እንዲህ ስለሆነ ለሀገሬ እና ለህዝቦቿ ያለኝ ፍቅር አይቀንስም እንደ አባቴ እወድሻለሁ።"

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማየት የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!👇
https://t.me/wektawi1mereja


የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ አስቸኳይ ስብሰባውን ያደርጋል። ከእረፍት የተጠራው ምክር ቤት በዚኹ ስብሰባው፣ መንግሥት በግጭት ሲታመስ በሰነበተው አማራ ክልል ለስድስት ወራት ባወጀውና "እንዳስፈላጊነቱ" በሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች ይተገበራል በተባለው አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ላይ ውሳኔ ያሳልፋል። ኢሰመኮ ቅዳሜ'ለት ባወጣው መግለጫ፣ ምክር ቤቱ አዋጁን ካጸደቀው የጊዜ ቆይታውን በአንድ ወር ብቻ እንዲወስነውና ከአማራ ክልል ውጭ ተግባራዊ እንዳይኾን መጠየቁ ይታወሳል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማየት የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!👇
https://t.me/wektawi1mereja


“አማራ ክልል ጅኖሳይድ ተፈፅሟል!”

በባህር ዳር የጅምላ ግድያ ተፈጽሟል። እየተፈጸመም ነው። አገዛዙ ባለፉት ሶስት ቀናት በወሰደው እርምጃ ከ2ሺህ በላይ ሰላማዊ ዜጎች ተጨፍጭፈዋል። አሁንም የቀጠለ በመሆኑ ቁጥሩ ሊጨምር ይችላል። ከአንድ ቤት አምስት የአንድ ቤተሰብ አባላት ተገድለዋል። የአራት አመት ህጻን ልጅ ትገኝበታለች። ይህ የጦር ወንጀል ነው። አገዛዙ ንጹሃንን እየጨፈጨፈ ከተሞችን በማስጨነቅ ለመቆጣጠር መጠነ ሰፊ ዘመቻ ከፍቷል። በጎንደርም ቤት ለቤት ግድያ ተጀምሯል። ምህረት የለም። ህጻናትና አዛውንቶች እየተጨፈጨፉ ነው። በሸዋ ሮቢት ይኸው እርምጃ መወሰድ ከተጀመረ ቆይቷል።

የአገዛዙ ኮማንድ ፖስት ይመጣና ''ጽንፈኞችን ደምስሼ ከተሞቹን አጽድቼአለሁ'' የሚል መግለጪያ ይሰጣል። ኢትዮጵያ ውስጥ የዘር ማጥፋት በሉት የጅምላ ፍጀት በአሁኑ ሰዓት እየተፈጸመ ነው። ይሄን እንደ ወታደራዊ ድል ቆጥሮ አገዛዙ ደጋፊዎቹን እያስፈነጠዛቸው ነው። ባለኝ መረጃ ከፋኖ ህዝባዊ ሃይል አባላት በእነዚህ ጦርነቶች የተገደሉት ከ30 አይበልጡም። በአገዛዙ ቁጥጥር ስር የሚገኝ የፋኖ አባል ካለ እስከአሁን አልሰማሁም። በቃ! ድል የተባለው የንጹሃን እልቂት ነው።

በድንጋጤ የሰነበተውን የአገዛዙን መንደር ለማረጋጋት በሚል በንጹሃን ፍጅትና እልቂት ከተሞቹን መልሶ መቆጣጠር እንደ መፍትሄ ተወስዶ ተግባራዊ እየተደረገ ነው። ሃላፊነት የማይሰማው ጨካኝ አገዛዝ ማድረግ የሚችለውን አድርጓል። የህዝቡ ሰላምና ደህንነት የሚያስጨንቀው የፋኖ ሃይል ስልታዊ በሆነ መልኩ ከከተሞቹ ወጥቷል። የበለጠ እልቂት እንዳይፈጸም በሚል ያደረገውን ይህን የስትራቴጂ ለውጥ ከሽንፈት የቆጠረው አገዛዙ ከበሮ እየደለቀ ይገኛል።

የቀናት ጉዳይ ነገሮችን እንደሚለውጥ እርግጠኛ ነኝ። ቀድሞውኑ የትግሉ አላማ ከተሞችን ይዞ መቆየትም አልነበረም። ጨካኙ አገዛዝ ድሮን ጭምር በመታጠቅ፡ በየድንበሩ የሰፈረውን ሰራዊት ነቅሎ በማምጣት ህዝብ ላይ የጅምላ ጭፍጨፋ ሲያውጅ ፋኖዎች ማድረግ የነበረባቸው ዞር ማለትን ነበር። አደረጉት። ይህ የጦርነት ባህሪ ነው። ለማንኛውም የባህርዳሩ ጭፍጨፋ እየተሰነደ ነው። የሚመክለከታቸው አካላት ማስረጃውን አጠናቅረው በዓለም ዓቀፍ የጦር ወንጀሎች ፍርድ ቤት እንዲታይ ማድረጋቸው አይቀርም። በግንባር ስላለው ሁኔታ ቀናትን መጠበቅ ነው። የሚሆነውን አብረን የምናየው ይሆናል።

መረጃው የጋዜጠኛ መሳይ መኮንን ነው!

ተጨማሪ ትኩስ መረጃዎችን በቴሌግራም ገፃችን ይመልከቱ!👇
https://t.me/wektawi1mereja


አቶ ክርስቲያን ታደለ እና ዶ/ር ካሳ ተሻገር “አካልን ነጻ የማውጣት” አቤቱታ ለፍርድ ቤት አቀረቡ!

በፖሊስ ቁጥጥር ስር የሚገኙት የፓርላማ አባሉ አቶ ክርስቲያን ታደለ እና የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባሉ ዶ/ር ካሳ ተሻገር በጠበቆቻቸው አማካኝነት “አካልን ነጻ የማውጣት” (habeas corpus) አቤቱታ ለፍርድ ቤት አቀረቡ። አቤቱታው የቀረበለት ፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ችሎት፤ የፌደራል ፖሊስ በጽሁፍ ምላሽ እንዲሰጥ አዝዟል።

የአቶ ክርስቲያን እና ዶ/ር ካሳ ጠበቆች አቤቱታቸውን ዛሬ ማክሰኞ ነሐሴ 2፤ 2015 ያቀረቡት፤ የፌደራል ፖሊስ ያለመከሰስ መብት ያላቸው ደንበኞቻቸውን ካለፈው ሳምንት መጨረሻ ጀምሮ “ያለምንም ፍርድ በእስር ላይ ያቆያቸው” መሆኑን በመጥቀስ ነው። በጠበቃ ሄኖክ አክሊሉ እና ሰለሞን ገዛኸኝ አማካኝነት የቀረበው አቤቱታ፤ በምክር ቤት የህዝብ ተወካዮቹ የተያዙበትን መንገድ ለፍርድ ቤቱ አብራርቷል።

በአንድ ገጽ የተዘጋጀው ይህ አቤቱታ፤ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ክርስቲያን ታደለ ባለፈው ሳምንት አርብ ከመኖሪያ ቤታቸው “እየተደበደቡ ተይዘው” በፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ መታሰራቸውን አትቷል። ዶ/ር ካሳ ተሻገርም በዚሁ ቀን ከለሊቱ ስድስት ሰዓት ገደማ በፌደራል ፖሊስ ተይዘው፤ በተመሳሳይ ቦታ ታስረው እንደሚገኙ በአቤቱታው ላይ ሰፍሯል። የፌደራል ፖሊስ ሁለቱንም ግለሰቦች የያዛቸው “ለጥያቄ እፈልጋቸዋለሁ” በሚል መሆኑንም በአቤቱታው ተመላክቷል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማየት የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!👇
https://t.me/wektawi1mereja


በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በ2015 በጀት ዓመት በትራፊክ አደጋ የ91 ሰዎች ህይወት አልፏል

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በተጠናቀቀው የ2015 በጀት ዓመት ባለፉት 12 ወራት 362 የትራፊክ አደጋዎች የተከሰቱ ሲሆን በሰው ህይወት ፣ አካልና ንብረት ላይ ጉዳት መድረሱ ተነግሯል ፡፡

በትራፊክ አደጋዎች 91 የሞት ፣ 219 ከባድ የአካል ጉዳት ፣ 39 ቀላል የአካል ጉዳት እና 13 የንብረት ውድመት አደጋ መድረሱን በክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት እና ገፅታ ግንባታ ሀላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለብስራት ራዲዮና ቲቪ ተናግረዋል ፡፡

በእነዚህ አደጋዎች ምክንያት 321 ተሳፋሪዎች ፣171 እግረኞች ፣ 117 አሽከርካሪዎች ለሞት ፣ለከባድና ቀላል አካል ጉዳት ሲዳረጉ ከ17 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ላይ ኪሳራ መድረሱ ተገልጿል ።

የትራፊክ አደጋዎች መንስኤ ከፍጥነት ወሰን በላይ ማሽከርከር ፣ ለእግረኛ ቅድሚያ አለመስጠት ፣ ቀኝን ለቆ ማሽከርከር ፣ አለአግባብ መጫን እና ለተሸከርካሪ ቅድሚያ አለመስጠት ምክንያት መሆናቸውን አንስተዋል ።

በ2015 በጀት አመት የደረሰው የትራፊክ አደጋ ከ2014 በጀት አመት ጋር ሲነፃፀር 68 የአካል ጉዳት አደጋና 4 የንብረት ውድመት አደጋ ሲጨምር የሞት አደጋ ቀንሷል ብለዋል ።

https://t.me/wektawi1mereja


መረጃ!

የብር አድማ ፋኖ እና የቋሪት ፋኖዎች ትብብር እና መናበብ አጀብ ያሰኝ ነበር። ከአዴት ወደ ደጋ ዳሞት ለመሄድ ጉዞ ላይ የነበረን መከላከያ ከብር አድማ ወጣ ብላ በምትገኝ ቦታ ላይ በጥምረት ቀለበት ውስጥ ከተው ዋጋውን ሰጥተውታል። ህዝቡ ግልብጥ ብሎ ከፋኖ ጋር ተሰልፎ ውጊያውን ሲያካሂድ ውሏል።

በተመሳሳይ ቡሬ ላይ አንድ ፋኖ አሰሳ ላይ የነበሩ 4 መከላከያዎችን ገድሎ ሁለቱን አቁስሎ ምንም ሳይሆን አምልጧል። ለመግደል የተረባረቡ ቢሆንም ምንም ሳይሆን ጥቃቱን አድርሶ ተሰውሯል። መከላከያው ከፍተኛ መደናገጥ ውስጥ ገብቷል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማየት የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!👇
https://t.me/wektawi1mereja


​​ቅዱስ ሲኖዶስ በትግራይ የተፈፀመውን የዶግማ፣ የቀኖና እና አስተዳደራዊ ጥሰት አስመልክቶ ተወያይቶ ተገቢውን ለመወሰን ለሐምሌ 25 ቀን 2015 ዓ.ም. አስቸኳይ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ጥሪ አስተላለፈ‼️

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን  ቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት የተሰጠ መግለጫ

  1. በክልል ትግራይ በተከሰተው ጦርነት ምክንያት በክልሉ ከሚገኙት አህጉረ ስብከት ጋር ተቋርጦ የነበረውን መዋቅራዊ ግንኙነት ችግር በውይይት እንዲፈታ ቅዱስ ሲኖዶስ ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪና ልዑካኑን በአካል ልኮ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ባለበት ወቅት በክልሉ የሚገኙ ብፁዓን አባቶች ሕገ ቤተ ክርስቲያንንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን በመጣስ ቅዱስ ፓትርያርኩ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ተብለው በሚጠሩበት በማዕከላዊ ትግራይ ዞን አክሱም ሀገረ ስብከት በርእሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ቤተ ክርስቲያን ሐምሌ 15 እና 16 ቀን 2015 ዓ.ም. በተከናወነ ሕገ ወጥ ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳት መፈጸሙን በመገናኛ ብዙኃን ለማወቅ ችለናል፡፡ በመሆኑም በዚህ የዶግማና የቀኖና ጥሰት ተግባር የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት በእጅጉ አዝኗል፡፡ 

2. በመሆኑም የተከሰተው የዶግማ፣ የቀኖና እና አስተዳደራዊ ጥሰት አስመልክቶ ተወያይቶ ተገቢውን ለመወሰን ለሐምሌ 25 ቀን 2015 ዓ.ም. አስቸኳይ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ጥሪ ተላልፏል፡፡

3. የስብሰባው ቀን ሊራዘም የቻለው በውጭው ክፍለ ዓለማት ያሉት ሊቃነ ጳጳሳት መገኘት ስላለባቸው የጉዞ ቀኑ እንዳያጥር እና በሀገር ውስጥ የሚገኙትም ሊቃነ ጳጳሳት ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል ምክንያት ለአገልግሎት ወደ አህጉረ ስብከታቸው የሄዱ በመሆኑ ለመመለሻ የሚያስፈልገውን ጊዜ ታሳቢ በማድረግ ነው፡፡

4. በየደረጃ ያሉ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የሥራ ኃላፊዎች እና ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንዲሁም ምዕመናን ከአሁን ቀደም በቤተ ክርስቲያናችን ላይ በደረሰው ፈተና በሐዘንና በጸሎት ከቤተ ክርስቲያናችን ጎን በመቆም ላሳያችሁት ጽናት እያመሰገንን አሁንም በደረሰው ፈተና እንዳሁን ቀደሙ ሁሉ በሐዘንና በጸሎት ከቤተ ክርስቲያናችን ጎን ጸንታችሁ እንድትቆሙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡

5. በመላው ዓለም የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮች የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በጉዳዩ ላይ ተወያይቶ ተገቢውን ውሳኔ እስከሚሰጥ ድረስ በትግዕስት እንድትጠብቁ እናሳስባለን፡፡

6. ምንም እንኳን ለቅዱስ ሲኖዶስ አባላት በሙሉ ጥሪው በደብዳቤ የተላለፈ ቢሆንም የመልእክቱ በፍጥነት መድረስ ካለው ስጋት አንጻር የችግሩን ተደጋጋሚነትና አሳሳቢነት ከግምት ውስጥ በማስገባት በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭው ክፍለ ዓለማት የምትገኙ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት በሙሉ እስከ ሐምሌ 24 ቀን 2015 ዓ.ም. ድረስ ተጠቃላችሁ ወደ ጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ እንድትመጡ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡

7. ሁሉም የቤተ ክርስቲያናችን ሚዲያዎችና ሌሎች መገናኛ ብዙኃን ይህን መልዕክት ለሁሉም ተደራሽ እንዲሆን መልእክቱን በማስተላለፍ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ በቤተ ክርስቲያናችን ስም እንጠይቃለን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ሐምሌ 17 ቀን 2015 ዓ.ም.

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማየት የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!👇
https://t.me/wektawi1mereja

Показано 20 последних публикаций.

8 640

подписчиков
Статистика канала